በእነ ደብረጽዮን ገብረሚካኤል የክስ መዝገብ ፍርድ ቤት የቀረቡ 21 ተከሳሾች የጠየቁት የዋስትና መብት ውድቅ ተደረገ August 19, 2021 ዜና Facebook X Linkedin Pinterest Telegram Whatsapp Email የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 1ኛ የፀረ ሽብር እና ህገ መንግስታዊ ጉዳዮች ችሎት በእነ ደብረጽዮን ገብረሚካኤል የክስ መዝገብ ፍርድ ቤት የቀረቡ 21 ተከሳሾች የጠየቁትን የዋስትና መብት ውድቅ አደረገ፡፡ ችሎቱ በእነ ደብረጽዮን ገብረ ሚካኤል የክስ መዝገብ ለዛሬ ይዞት በነበረው ቀጠሮ ላይ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡ በደብረጽዮን ገብረ ሚካኤል የክስ መዝገብ 58 ግለሰቦች እና አራት ድርጅቶች በሽብር ወንጀል መከሰሳቸው ይታወሳል፡፡ከእነዚህ መካከል ነሐሴ 11 ቀን 2013 ዓ.ም በነበረው ችሎት ከተከሳሾቹ 21ዱ በአካል ቀርበው ክስ የተነበበላቸው ሲሆን የዋስትና መብት እንዲጠበቅላቸውም አመልክተዋል፡፡ በተከሾቹ ላይ የተመሰረተባቸው ክስ ዋስትና የሚያስከለክል በመሆኑ ዐቃቤ ሕግ የተለያዩ ዝርዝር ሀሳቦችን በማንሳት መከራከሩም መዘገባችን ይታወሳል፡፡ ችሎቱ በሁለቱ ወገኖች ክርክር ላይ ለዛሬ ትዕዛዝ ለመስጠት በያዘው ቀጠሮ መሰረት ተከሳሾች ችሎት መምጣት ሳይጠበቅባቸው በቃሊቲ ማረሚያ ቤት ሆነው ትዕዛዙን እንዲጠብቁ በማለት ነበር ችሎቱ ለዛሬ የቀጠረው፡፡ ፍርድ ቤቱ የሁለቱንም ወገኖች የዋስትና ጥያቄ ክርክር መርምሮ ዋስትና ጥያቄውን ውድቅ አድርጎታል፡፡ የፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ በማረሚያ ቤት በኩል ለተከሳሾች እንዲደርሳቸው ሲል ችሎቱ አዟል፡፡ በችሎቱ በአካል ያልተገኙት እነ ደብረጽዮን ገብረሚካኤል፣ ጌታቸው ረዳ፣ ሊያ ካሳ እና ሌሎች ተከሳሾች እንዲሁም የአራቱ ድርጅቶች ተወካዮች የፌዴራል ፖሊስ ባሉበት ይዞ እንዲያቀርብ እና ውጤቱንም ለመጠባበቅ ለጥቅምት 22 ቀን 2014 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ መያዙ ይታወሳል፡፡ በጥላሁን ካሣ EBC Facebook X Linkedin Pinterest Telegram Whatsapp Email Leave a Reply Cancel replyYour email address will not be published. Δ Previous Story ጠላትን በአጭር ጊዜ ለማጥፋት በቅንጅት እየተሰራ ነው፡- ብ/ጄ ተፈራ ማሞ Next Story በአማራ ክልል ሰርጎ የገባው የአሸባሪው ህወሀት ሀይል መደምሰሱን በሰሜን ወሎ ግንባር የተሰማራው የሰራዊት ክፍል አስታወቀ