በአማራ ክልል ሰርጎ የገባው የአሸባሪው ህወሀት ሀይል መደምሰሱን በሰሜን ወሎ ግንባር የተሰማራው የሰራዊት ክፍል አስታወቀ

236244955 3007732859469173 1442007123964492267 n
236244955 3007732859469173 1442007123964492267 n

ነሀሴ 14 -2013 (ኢዜአ)በአማራ ክልል ሰርጎ የገባው የአሸባሪው ህወሀት ሀይል መደምሰሱን በሰሜን ወሎ ግንባር የተሰማራው የሰራዊት ክፍል አስታውቋል ።

ጀግናው የመከላከያ ሰራዊት ዋድላ ወረዳ ፣ ኮን ከተማ እንዲሁም በጋሸና አካባቢ የሚገኘውን የአሸባሪ የህወሀት ቡድን በመምታት አኩሪ የጀግንነት ተግባር መፈጸሙን አዛዥ አረጋግጠዋል ፡፡
ጀግኖቹ የሰራዊት አባላት በአካባቢው የሚገኝ የጠላት ፣
የሰውና የመሳሪያ ሀይል በየትኛውም አቅጣጫ እንዳይወጣ በማድረግና በመደምሰስ ከዋድላ ወረዳ እስከ ጋሸና ከተማ በመቆጣጠር ታሪካዊ ድል መፈፀማቸውን አመልክተዋል፡፡
ሠራዊቱ ከወልዲያ አምልጦ የመጣውን ጠላት
በመከታተል ፣ በዋድላ ወረዳና አካባቢ የመሸገውን የጠላት ሀይል እና መሳሪያ በመደምሰስ በከፍተኛ ድል ጋሸና ከተማን መቆጣጠሩን ከመከላከያ ሰራዊት ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል፡፡
የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት የኢዜአ ን የዩቲዩብ ቻናል ሰብስክራይብ ያድርጉ
ኢዜአ
ተጨማሪ ያንብቡ:  Hiber Radio: "ቦሌ ኤርፖርት ፓስትፖርቴን የሰጠሁት ሰራተኛ አለቃዬን ላነጋግር ብሎ ገብቶ የፓስፖርቴን አንድ ገጽ ቀዶ በመጣል አንድ ገጽ ጎሎታል አለኝ፤ ቀረሁ" - ኢንጂነር ይልቃል

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share