አዲስ ለሚዋቀረው ለኢትዮጵያ ብልጽግና ፓርቲ አማራጭ ሀሳብ ጠቁዋሚ – ይድረስ ለሚመለከታችሁ ሁሉ

እንዲህ ነው ጉዳዩ። አካሄዳችን ስላላማረኝ ምናልባት አገራችንን ወደሰላም ያመጣል ብዬ መፍትሄ ሀሳብ ነውና እንደፈለጋችሁ እዩት። አንድ ጃንሆይ ካደረጉት ነገር ይቺን በብዙ ጎሳዎች የታጠረችን አገር በዘዴ ነበር ያስተዳድሩ የነበረው። ያለንበት ሁኔታ ዘዴን ይፈልጋል ይመስለኛል። አይተናት ያደግናት ኢትዮጵያ መልኳን ቀይራ ሁሉ ጫፍ ይዞ እርስበራሱ የሚጓተትበት ዘመን ላይ ስለሆን የአቢይ መንግስት ይህን ከግንዛቤ አስገብቶ አሁን የሚዋቀረውን ፓርቲ እንዲህ ቢያደርግ ጊዜያዊ መፍትሄ ይሆናል ብዬ አስባለሁ።
፩) ሙስጠፌን የአዲሱ ፓርቲ  ሊቀመንበር አድርጋችሁ እስከ ምርጫው ጠ/ሚር ሆነው እንዲሾሙ አመቻቹላቸው። ለምን? ከተቀራችሁ ኢሀዴጎች በሙሉ ልክ ሁሉን ግዛት እንደራሳቸው ሱማሌ ግዛት በማየት ፍጹም ኢትዮጵያዊነት ተመልሶ እንዲያብብ ተስፋ ይሆናሉ ብዬ አስባለሁ። ማለፍያ አለምአቀፍ ተሞክሮም አላቸው። የካድሬነት ባህሪ አልነካቸውም። የወያኔ ተንኮል ሰለባ ባለመሆናቸው በሀቅ ሁሉን ጎሳ በኩልነትና ፍትሃዊነት ይመራሉ ብዬ አስባለሁ። ሱማሌ ልጆቻችን ቃልኪዳናቸው አስደማሚ ነው። ቆራጥም ናቸው። የሙስጠፌ ጠ/ሚር መሆን የዖነግን ጎማ ያስተነፍሳል። የ አክራሪ አማሮቹንም ጫፍ ረገጥነት ልክ ያስገባል። የሌሎች በቁጥር ያልደመቁ ግን በኢትዮጵያዊነት የደመቁ  ብሄር ብሄረሰቦችም ተስፋ ይሆናሉ። ይህ ከሆነ ሊበጠስ የሳሳው የኢትዮጵያዊነት ገመድ ቀስ እያለ ይጠብቃል። ልብ በሉ ወገኖቼ። የዖነግና ወያኔ አላቻ ጋብቻ ለተንኮል ካልሆነ በቀር ለአገር ምንም የሚፈይደው የለም። አቢይና ደመቀ የሙስጠፌ ምክትል ሆነው ይስሩ። ሌላ ምክትል ካስፈለገ አንዱን የአረና ወይም ህወሃት ያልሆነ ተወካይ ጨምሩ። ያገራችን ችግር ከ 50 አመታት ወዲህ ከ ዖሮሞ፣ አማራና ትግራይ ከበቀሉ ምሁራን ተብዬ ነውና እስቲ ለለውጥ ያህል የሱማሌ ልጆቻችን አስተዳደሩን ይረከቡና ያስተዳድሩን። የህዝብን ቁጥር ያማከለ ውክልና ዴሞክራሲው ሲደራ ይደርሳል። ከ ፫ አመት በሁዋላ በትንሹ።
፪) የታቀደውን የቅርብ ምርጫ እንዲተላለፍ በአንድ ድምጽ ለፓርላማ አስቀርባችሁ አጸድቁ። የ28 አመታት ያለቁት ወገኖቻችን “ቢረሱ” እንኩዋ በቅርቡ ያለቁት ወገኖቻችን ከአይምሯችን እስቲ ከሰም ይበል። ደሞስ ዬትኛው የፖሊሲ ውይይት ተጀመረናስ ምርጫ ይታሰባል? ለመምረጥስ አድራሻ አያስፈልገውም  ነዋሪው? ሰው እየተፈናቀለ ከፊሉ ቤቱ እየፈረሰበት አስመራጩስ ማ ቤት ሄዶ ነው ተመራጩን የሚመዘግበው? ወይስ የደቦ ምርጫ ሊሆን ነው? ምርጫው ጭራሽ መተላለቂያ እንዳይሆን እሰጋለሁ። ምርጫ በ ፫ አመታት ውስጥም ከሆነም እሰየው። እናም ምርጫ አለመኖሩ በግልጽ ለህዝቡ ይነገረው። በየቤቱ እልል ቢል እንጂ የሚከፋው አይኖርም ብዬ አስባለሁ። የሚከፋቸው የታወቁት የጽልመት ሀይላት ናቸው። እነሱ ደሞ በቁጥር እጅግ አናሳ ናቸው። በየ ማስሚዲያው  ፊሽካ ስለነፉ ብዙ መስለውን ሊታዩ  ግን ይችላሉ። አይደሉም።
፫) እዚህ አዲሱ ሸንጎ የተዋቀራችሁ ፓርቲዎች በጥቂት ቀናት ልዩ ሀይሎቻችሁን አንድ እዝ ስር አድርጉና ወደር የማይገኝለት ጦር ሰራዊት ይመስረት። ታያላችሁ ይህ የአንድነት መንፈስ ሃያሉዋን ኢትዮጵያን እንዴት እንደሚመሰርት። በነ አክራሪያን ሰበካ አትሸወዱ። አንድነት ወጥነት አይደለም። ህብረብሄራዊነት እንጂ ። አማራ፣ ዖሮሞ፣ ትግሬ ሊውጠን ነው፣ አሃዳዊ ስርአት ሊመጣ ነው ለሚለው ሰበካ ሙስጠፌ አይመቹም። ለዚህም ነው የኝህ ሰውዬ ጠቅላይ አስተዳዳሪ መሆን የያንዳንዱዋን አክራሪ ጎማ አስተንፋሽ ወስፌ የሚሆነው። በአገራችን ብዙ ነገራችን ምስቅልቅሉ ለ ብዙ አስርተ አመታት ስለወጣ ይህ አስታራቂ ይሆናል ብዬ አስባለሁ።
፬) ክብርት ፕሬዚደንቱዋን የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና የተባበሩት መንግስታት ዋና ተጠሪ ማድረግ። እኒህን ሰው የይስሙላ እንደራሴ ማድረግ ክህሎታቸውን በትክክል አለመጠቀም ነው። በአለም አቀፍ ጉዳይ ጥርሳቸውን የነቀሉ ብርቱ ሴት ናቸውና ኢትዮጵያችንን ወደልዩ ከፍታ ያመጡልናል ብዬ አስባለሁ። ፕሬዚደንትነት እስከ ምርጫው ይቅር። በአንድ ፓርላማ ስብሰባ ማፍረስ ነው። ፕሮፌሽናል ስለሆኑም ቅር ይላቸው አይመስለኝም። አቶ ገዱን የ interregional affairs ሊቀመንበርና የአዲሱ ፓርቲ ልዩ አማካሪ አድርጎ መሾም።
፭) አምባሳደሮቻችንን በሙሉ እንዳሉ ብቃታቸውን መፈተሽ። ክብርት ፕሬዚደንቱዋ የውጭ ጉዳይ ከሆኑ ይህ በጣም ይቀላል። በብቃት ከሆነ አገራችን በማንም ካድሬ ብቃት መመዘኑዋ ይቀርና ወደ ቀድሞዋ ከፍታ ታመራለች። እነ ከተማ ይፍሩ፣ ይልማ ዴ’ሬሳ፣  አክሊሉን ያፈራች ኢትዮጵያ ፣ እንኩዋንስ ባገራቸው ጉዳይ ቀርቶ የአፍሪካ ሀገራትን አምባሳደሮች ሀሁ ያስተማሩ ልሂቃን ነበሩን። ቅንነቱ ካለና በደንብ ቢፈለጉ ዛሬም ይኖራሉ። ሙያውን ከባለሙያው ካዛመድን ይቺ አገር ከፍ ያለ ቦታ ትደርሳለች። ለምሳሌ የአዲሱ ኢሰመጉ ሊቀመንበር ወጣቱ ሰውዬ ምደባ ግሩም ድንቅ ነው።
ማሳሰብያ!
መፍትሄ የምትሉትን ከመጨመር ሌላ ጉዳይ ላይ ጊዜአችሁን አታጥፉ። የአገራችን ሁኔታ አደገኛ መስመር ላይ ነው። እስቲ ብሶታችሁን ብቻ ማመልከቻ የምትጽፉ ሰዋች መፍትሄ ውለዱ። መደማመጥ ቀርቶ መወነጃጀል ብቻ ከሆነ ዬትም አንደርስም። እንደ ህዝብ እንጠፋፋ ይሆናል እንጂ ኢትዮጵያ እንደአገር ትቀጥላለች። በኢትዮጵያችን ውስጥ ሌላ አገር እንፈለስፋለን የምትሉ እንኩዋ ከልባችሁ እንዳልሆነ  አጥታችሁ ሳይሆን በውስጣችሁ ያለው አምቃችሁ የያዛችሁት ሰልፊሽነት እየገነፈለባችሁ ተቸግራችሁ ነው። ተረጋጉ። ግራና ቀኙን የሚያለቅሰውን አቅመደካማ፣ የሚሳቀቀውን ታዳጊ አስተውሉ። ግፍ ሲበዛ በጎ አይደለም። ብዙ በሙያ የተራቀቁ አስደማሚ ልጆችና የልጅ ልጆች  በአለም ተበትነው አሉን። እነሱን እንዴት አርገን በፍቅር ሀርቨስት እናርግ ብለን እናስብ። ይህው ነው።
የበኩሌን ለግሻለሁ። እናንተስ?
ከምስጋና ጋር
አባዊርቱ
ተጨማሪ ያንብቡ:  በዘንድው ሃጅ ጸሎት የተወገዱት ሰው ሰራሽ አደጋዎች !

5 Comments

  1. Brilliant suggestion I can not disagree. as for the election I would suggest if it has to be conducted for know with international, African Union and other organization who have extensive experience start for now with three cosmopolitan cities.
    FIRST and most*** ADDISABABA***
    SECOND *** DIREDAWA***
    THIRD ***AWASSA***
    IT CAN BE WELL CONTROLLED, CAN EASLY DEPLOY THE MILLITARY AND THE INTERNATIONAL OBSERVERS CAN WITNESS IT IS TRANSPARENT AND THE FACT THAT WHO OPPOSES THIS SUGGESTION IN THE PARTIES WILL SHOW THEY ARE THERE FOR POWER NOT FOR UNITY AND INTEGRETY.
    THANK YOU PLEASE POST YOUR COMMENTS THERE IS NOTHING MORE IMPORTANT THAN THIS.
    MESFIN ABBBAI KASAA
    OTTAWA, CANADA.

  2. “አንድ ጃንሆይ ካደረጉት ነገር ይቺን በብዙ ጎሳዎች የታጠረችን አገር በዘዴ ነበር ያስተዳድሩ የነበረው። ያለንበት ሁኔታ ዘዴን ይፈልጋል ይመስለኛል” በዘዴ ነበር አልከኝ- ምን ነበር ዘዴዉ?
    አሳቸዉ በዘዴ አስተዳድረዉ ቢሆን ኖር ይህ ሁሉ ችግር ከየት ይመጣ ነበር? የተለያዩ ማንነቶችን ጨፍልቆ ወደ አማራ ማንነት ማምጣትና ሁሉንም ኢትዮጵያዊ ኦርቶዶክስ ለማድረግ መሞከር ነበር ዘዴዉ? ምነዉ የቆየ መንግስቱ ኃ/ማሪያም የዘጋዉን ታሪክ ባትቆሰቁስብን?

  3. It is time for the SEPDM to take out the P from it’s name.

    Sidama people are not represented by Southern Ethiopian People’s Democratic Movement party (SEPDM) or EPRDF.

    Sidama is not governed by the SNNP regional government.

    That means EPRDF got no authority over the Sidama people, only the federal government does .

  4. ዘዴው ንገረኝ ካልክ የጠቅላይ ግዛት ወይም የ አስራአራቱ ክፍላተሀገራት ቢሆን ኖሮ ለዚህ ሁሉ የጎሳ ቅዠት ባልተዳረግን ነበር። የክፍለሀገር አስተዳደር መኖሩ እኮ እጅግ ዘመናዊነት ነበር ልክ እንደአሜሪካው የስቴትና ፌዴራል አወቃቀር አይነት። የጃንሆይ ዘመን ችግር አስተዳዳሪዎቹ በዴሞክራሲ አለመመረጥና ወይም በአብላጫው ከኖቤልቲ ሆነና ነው። ያንን አዘምነን ቁጥሩንም አንድ ሁለት ጨምረን በትክክለኛ ዜግነትና ብቃት ላይ ቢሰራ ዛሬ ካለንብት ውጥቅንቅጥ አይሻል ብለህ ነው። እንደው አሮጌ አስተዳደር ስለሆነ ባንኮንነው። የዛሬን የደቡብ ወንድሞቻችንን ችግር ይህ የክፍለሀገር አስተዳደር ይፈታ ነበር። ይህን ዘዴ ማለቴ ነው አቶ ጎዳናው።

Comments are closed.

Share