February 26, 2019
2 mins read

የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ኤጀንሲ የፊታችን አርብ በሼራተን አዲስ ሆቴል በይፋ ስራ ሊጀምር መሆኑ ተነገረ

94276

የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ኤጀንሲ የፊታችን አርብ በሼራተን አዲስ ሆቴል በይፋ ስራ ሊጀምር መሆኑ ተነገረ፡፡ ተጠሪነቱ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሆነው ይህ የፌደራል መስሪያ ቤት በዋና ዳይሬክተሯ ወይዘሮ ሰላማዊት ዳዊት አማካኝነት ዛሬ መግለጫ ሰጥቷል፡፡

https://www.youtube.com/watch?v=14ql5rq_pMI

በመግለጫው ኤጀንሲው በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የውጭ ዜጎች መብትና ጥቅም የማስጠበቅ ተልዕኮ እንዳለው የጠናገሩ ወ/ሮ ሰላማዊት በየትኛውም ዓለም የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ያለምንም ልዩነት በሀገራቸው ጉዳይ በንቃት እንዲሳተፉ ማድረግ እንዳሰበ ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም ዲያስፖራውን የማስተባበርና የመምራት እንዲሁም የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች በተቀላጠፈ መንገድ ለማድረስ ዝግጅታቸውን እንደጨረሱ ገልጸዋል። የኤጀንሲው ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ መሀመድ እንድሪስ በበኩላቸው ዲያስፖራውን ንቁ ተሳታፊ በማድረግ በሀገሩ ገብቶ መስራት የሚችልበትን እድል የማመቻቸት ተግባር ይከናወናል ብለዋል። በውጭ የሚኖረው ኢትዮጵያዊያና ትውልደ ኢትዮጵያዊ ቁጥር በሚሊዮኖች የሚገመት ቢሆንም ኤጀንሲው በቅድሚያ ከሚያከናውናቸው ተግባራት መካከል ቁጥሩን በውል ማረጋገጥን ጨምሮ አጠቃላይ የዲያስፖራውን መረጃ ማሰባሰብ እንደሚሆን ተገልጿል።

94272
Previous Story

“ለውጡን ለመቀልበስ ከሚሰሩ ወገኖች በላይ እርስ በእርሳችን የምናደርገው ፍትጊያ የመጣውን ለውጥ ወደ ኋላ ይጎትታል” አቶ ለማ

94279
Next Story

ዛሬ በአርባምንጭ ከባድ የመኪና አደጋ ተከሰተ፣ አደጋውን ያደረሰው አሽከርካሪ በፀፀት ህይወቱን አጠፋ!

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop