January 26, 2019
2 mins read

ለምግብነት ሊውል የማይችል 55,000 ቶን የተበላሸ ስንዴ የጫነች መርከብ..

55000

ለምግብነት ሊውል የማይችል 55,000 ቶን የተበላሸ ስንዴ የጫነች መርከብ ጅቡቲ ላይ ቆማ ሶስት ወር ድርድር ከተደረገበት በሁዋላ ስንዴው ወደ ሀገር ውስጥ እየገባ ነው ሲሉ አምባሳደር ሱለይማን ደደፎ አጋለጡ::

https://www.youtube.com/watch?v=p8iBU5RCUVc&t=50s

‘አምባሳደሩ በፌስቡክ ገጾች እንዳሰፈሩት “ፕሮሚስንግ በተባለ አቅራቢ ድርጅት አማካይነት የቀረበው ይህ ስንዴ በስብሶ ለምግብነት ሊውል ስለማይችል ወደመጣበት እንዲመለስ የተወሰነ ቢሆንም የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ከአስመጭው ድርጅት ጋር ባደረገው ድርድር ስንዴው ታክሞአል በሚል ምክንያት ተጭኖ ወደ ሀገር ቤት እንዲገባ ተደርጎአል።” ያሉት አምባሳደሩ :ስንዴው የበሰበሰው አንሶ መታከሚያ ኬሚካል ተጨምሮበት ሊያስከትለው ስለሚችለው የጤና ጠንቅ የታሰበበት ነገር ይኖር ይሆን?

ታክሞ መግባት የሚችል ከሆነ ከመጀመሪያው ወደ መጣበት እንዲመለስ ለምን ተወሰነ?

የተወሰነው ውሳኔ እንዴት በድርድር ሊሻር ቻለ?” ሲሉ ጥያቄዎቻቸውን አቅርበው “እንደኔ እምነት ድሮ በነበረው አሰራር ውሳኔው ተሽሮ ስንዴው እንዲገባ የተደረገው ጉቦ ተበልቶበት ብቻ ነው ሊሆን የሚችለው። ስለዚህ ለምግብነት በሚውሉ ገቢ ምርቶች ጥራት ላይ መንግስት በቂ ቁጥጥር ማድረግ ይኖርበታል። ፕሮሚስንግ የተባለ የስንዴ አቅራቢ ድርጅት ከ20 ዓመታት በላይ ከጨረታ ውጭ በብቸኝነት ስንዴ አቅራቢ የነበረ ከባለሥልጣኖች ጋር ጥብቅ ትሥሥር የነበረው ድርጅት ነው። ” ብለዋል::

በዚህ ጉዳይ የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ወደ ስቱዲዩ እስከገባንበት ጊዜ  የሰጠውን ምላሽ የለም::

93882
Previous Story

“በቤተክርስቲያን ውስጥ አፈና አለ” – አቡነ መቃርዮስ

93888
Next Story

በጎንደር ዩኒቨርሲቲ በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ በተማሪዋች መኖሪያ ክፍሎች ጩቤ፣ ድንጋይ፣ ብረት እና ዱላ ተገኘ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop