January 4, 2019
4 mins read

በአቶ ለማ መገርሳ የሚመራው የኦሮሚያ ክልልላዊ መንግስት “የህግ የበላይነት ተከብሮ ሰላም እንዲሰፍን እየሰራሁ ነው; የሕዝቡ ድጋፍ ያስፈልገኛል” አለ

93526

በአቶ ለማ መገርሳ የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት “የህግ የበላይነት ተከብሮ ሰላም እንዲሰፍን እየሰራሁ ነው; የህግ የበላይነት ተከብሮ ሰላም እንዲረጋገጥ የህዝቡ ተሳትፎ መጠናከር አለበት” ሲል በክልሉ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ በኩል ባወጣው መግለጫው አስታወቀ::
https://www.youtube.com/watch?v=aVUdalQQ5Mk&t=54s
“የመልካም አስተዳደር ችግርን መነሻ በማድረግ በተደረገ ትግል ከፍተኛ መሰዋዕትነት ተከፍሎ የኦሮሞ ህዝብ መብት መረጋገጥ ጀምሯል:: በአሁኑ ወቅትም የህዝቡ ተስፋ እየለመለመ መጥቷል” ያለው የክልሉ መንግስት፥ “ይሁን እንጂ ስልጣን ከእጃቸው የወጣ አካላት በየስፍራው ሴራ በመሸረብ አሁን የተጀመረው ለውጥ እንዲደናቀፍ ሌት ተቀን እየሰሩ ነው:: የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ከመንግስት ጋር የደረሰው ስምምነት ሙሉ በሙሉ ባለመተግበሩም የኦሮሚያ ክልል ሰላም እየደፈረሰ ነው” ብሏል::

“በተለይም በአራቱ የወለጋ ዞኖች እና በምእራብ ጉጂ ዞን ውስጥ በየእለቱ የሰው ህይወት እያለፈና ንብረት እየወደመ ነው ያለው የክልሉ መንግስት፥ መንገዶች በመዘጋታቸውና የንግድ እንቅስቃሴ በመቆሙ ህዝቡ ለከፍተኛ ችግር እየተጋለጠ ነው በማለት አስረድቷል::

“ወቅቱ ስልጣንን ማእከል በማድረግ እርስ በእርስ ድንጋይ የምንወራወርበት አይደለም ያለው የክልሉ መንግስት፥ ከሁሉም በፊት የህዝቡን ሰላም በማስቀደም ችግሮቻችንን የምንቀርፍበት ጊዜ ላይ ነን:: ለአንድነት እና ለሰላም ያለው አማራጭ ህግን ማክበር እና ማስከበር ነው፤ ለዚህ ደግሞ መንግስት ግዳጅ ስላለበት የህግ የበላይነት ተከብሮ ሰላም እንዲሰፍን እየሰራ ነው::ችለዚህም ህዝቡ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያደርግ ጥሪዬን አቀርባለሁ” ብሏል;;

ይህ በ እንዲህ እንዳለ በነቀምቴ፣ ጊምቢና ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ሰዎች በኮማንድ ፖስት ቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገለጸ፡፡ ቁጥጥር ስር የዋሉ ግለሰቦች ቤተሰቦች እንደሚሉት ከሆነ ቁጥጥር ስር የዋሉት ከኦነግ ጋር ተያያዥነት አላቸው ተብሎ በመጠርጠሩ ነው፡፡
የአካባቢው ኮማንድ ፖስት በበኩሉ ከአባ ቶርቤ ውጭ ማንንም አልያዝንም ብሏል፡

በሌላ በኩል የአማራ ክልል ምክር ቤት እና የጨፌ ኦሮሚያ ምክር ቤት አባላት በደብረዘይት ቢሾፍቱ ከተማ ባደረጉት የልምድ ልውውጥ ስብሰባ የሁለቱን ክልሎች ሕዝብለሕዝብ ግንኝኙነት አጠናክሮ ለማስቀጠል እንደሚሰሩ መናገራቸውን በኦሮሞ ብሮድካስት ኔትወርክ ላይ ተዘግቦ አይተናል::

93554
Previous Story

በቅርቡ የተቋቋመው የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጀንሲ በይፋ ስራ ሊጀምር መሆኑን ገለጸ

93529
Next Story

የዛሬው የአዲስ አበባ ንፋስ መብራትና ውሃ አቋረጠ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop