የውሃና መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴሩ ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጅነር ስለሺ ዛሬ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ያለበትን ወቅታዊ የግንባታ ደረጃ ይፋ አደረጉ።
https://www.youtube.com/watch?v=yJGl1PI8qiY
በዚህም መሰረት በአሁኑ ወቅት ዋናው ግድብ የሲቪል ስራ 80 በመቶ መጠናቀቁንና የኃይል ማመንጫዎች የሲቪል ስራ በአማካይ 66 በመቶ ተማለቁን አስረድተዋል፡፡ የጎርፍ ማስተንፈሻ የሲቪል ስራዎች ደግሞ 99 በመቶ፣የኮርቻው ግድብ ስራዎች 93 በመቶ፣ የስዊችያርድ የሲቪል ስራዎች 33 በመቶ መጠናቀቁን ገልፀው በአጠቃላይ የሲቪል ስራው 82 በመቶ ያህሉ መጠናቀቁን አስረድተዋል፡፡
በሜቴክ ተይዞ የነበረውን የኤሌክትሮሜካኒካል ስራዎችን በተመለከተ ሲያስረዱ ደግሞ ‹‹የዘጠኝ ተርባይን እና ጄኔሬተር በአብዛኛው የተከናወነ ቢሆንም የተወሰኑት የተርባይንና ጄኔሬተር አካላት በሀገር ውስጥ ይመረታሉ ተብለው የታሰቡት አልተመረቱም›› ብለዋል፡፡ አጠቃላይ የኤሌክትሮ መካኒካል ስራዎች አፈጻጸም 25 በመቶ መሆኑን የገለፁት ሚኒስትሩ የሃይድሮሊክስ ስቲል እስትራክቸር ስራዎች አፈጻጸም 13 በመቶ ብቻ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ በሜቴክ የተሰራው ስራ 23 በመቶ ብቻ ሲሆን ፕሮጀክቱ አሁን የደረሰበት የግንባታ ደረጃም 65 በመቶ መሆኑን ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጅነር ስለሺ አብራርተዋል።