በትላንትናው እለት በምስራቅ ጎጃም ዞን በእነማይ ወረዳ አንዲት እናት አራት ሴት ልጆችን መገላገሏ ተሰማ፡፡
https://www.youtube.com/watch?v=yJGl1PI8qiY
ወ/ሮ ላቀች መዋህኝ የተባለችው የእነማይ ወረዳ ፈለገ ሰላም ነዋሪ ትላንት ታህሳስ 24 ከሌሊቱ 11፡30 ወደ የትመን ጤና ጣቢያ በመሄድ እስከ ጥዋቱ 12፡30 ድረስ 4 ሴት ህጻናትን በሰላም መገላገሏን አብመድ ዘግቧል፡፡
ወ/ሮ ላቀች መዋህኝ ከዚህ በፊት 4 ልጆችን እንደወለደችም ዘገባው አስረድቷል፡፡ እንደዘገባው ህጻናቱ በቢቸና የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሲሆኑ እናትዬዋ ሙሉ ጤነኛ ብትሆንም እስካሁን አይነት ክስተት በተቋሙ ተከስቶ የማያውቅ በመሆኑ በከፍተኛ ባለሙያ እንድትታይ ወደ ደብረ ማርቆስ ሪፈራል ሆስፒታል ተልካለች፡፡ ያዋለዷት የህክምና ባለሙያ አቶ አባይነህ ሙላት ሲናገሩ ‹‹በህክምና ስራየ አንዲት እናት አራት ልጆችን ስትወልድ የመጀመሪያዬ ነዉ፡፡ ነገር ግን ቀድሞ አስፈላጊዉን ቅድመ ዝግጅት በማድረጌ ያለምንም ችግር አንዲት እናት አራት ሴት ልጆችን ወልዳለች፡፡ እንደዚህ አይነቱ ክስተት የመፈጠር ሁኔታዉ 0 ነጥብ 01 ከመቶ በመሆኑ ብዙም የተለመደ አይደለም›› ብለዋል፡፡
ከሰሞኑ ሰሜን ወሎ ዞን አካባቢ በተመሳሳይ አንዲት እናት አራት ልጆችን ተገላግላለች፡፡