December 31, 2018
1 min read

በኢትዮጵያ ለሁለት ወራት የሚዘልቅ ጾም፣ ጸሎትና ምሕላ ታወጀ

93446

የሀይማኖት አባቶች በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ አማኞች በሙሉ እንደየእምነታቸው ለሁለት ወራት የሚዘልቅ ጾም፣ ጸሎትና ምሕላ እንዲያደርጉ አወጁ፡፡ የኢትዮጵያ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ የበላይ አባቶች እና የኢትዮጵያ የሀገር ሽማግሌዎች አሁን በሀገሪቱ ያለውን ወቅታዊ የሰላም ሁኔታ በተመለከተ በዛሬው እለት መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ የኢትዮጵያ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤው ሁሉም ወገን ቅድሚያ ለሀገራዊ አንድነት፣ ለሰብአዊ ክብርና ሰላም በመትጋት የወገኖቻችን ሞት፣ መፈናቀልና ጉዳት በአፋጣኝ ማቆም ይገባዋል ሲል የተማጽዕኖ ጥሪም አቅርቧል፡፡ ከዚህ በኋላ በሀገሪቱ በየትኛውም አካባቢ ምንም አይነት ግጭት እና የሚተኮስ ጥይት ሊኖር እንደማይገባ አሳሰበው ጉባኤው ለመላው ሰላም ወዳድ ኢትዮጵያውያን ሁሉ ባለአስር ነጥብ የሰላም መልዕክት እና የተማጽዕኖ ጥሪ አቅርቧል፡፡

ግጭቱ ተወግዶ የታሰበው ሰላም እውን እንዲሆንም በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ አማኞች በሙሉ እንደየ ዕምነታቸው ለሁለት ወራት የሚዘልቅ ጾም ጸሎትና ምሕላ ታውጇል ብሏል ጉባኤው፡፡

https://www.youtube.com/watch?v=Pe4vPoSA5JM&t=223s

cnn
Previous Story

ሲኤንኤን (CNN) ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የአፍሪካን ቀልብ መሳብ የቻሉ መሪ ናቸው ሲል አሞካሸ

93454
Next Story

ኢትዮጵያና ሱዳን በሶስት ሳምንት ውስጥ ለሶስተኛ ጊዜ ተገናኙ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop