December 31, 2018
2 mins read

ሲኤንኤን (CNN) ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የአፍሪካን ቀልብ መሳብ የቻሉ መሪ ናቸው ሲል አሞካሸ

cnn

የአሜሪካው ትልቁ የሚዲያ ተቋም ሲኤን ኤን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ የመላው አፍሪካን ቀልብ መሳብ ችለዋል ሲል አሞካሸ::

ዶ/ር አብይ ኢትዮጵያ ከገባችበት የብሔር ግጭትና ውጥረት እንድትወጣና ብሔራዊ መግባባት እንዲፈጠር ማድረግ መቻላቸውን የገለጸው ሲኤንኤን በኢትዮጵያ የታሰሩ ፖለቲከኞችና ጋዜጠኞች ከእስር እንዲፈቱ ብሎም በውጭ የሚኖሩ የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ወደ አገር ቤት እንዲመለሱ ማድረጋቸውን ጠቅሶላቸዋል::

“በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል የነበረው የረጅም ጊዜ ውጥረት ወጥተው ወደ ሰላም እንዲገቡ ማድረጋቸውን” የጠቀሰው ሲኤንኤን በምስራቅ አፍሪካ የሚታየውን ግጭት ለማስወገድ ሶማሊያ፣ ኤርትራ እና ጅቡቲን ያካተተ የጋራ ውይይት በማድረግ የተጫወቱት ሚናም ቀላል የሚባል እንዳልሆነ አስረድቶ በዚህም፣ የአፍሪካ አገራት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ለአፍሪካ ተስፋ ሰጪ የሆነ ተግባር እያከናወኑ እንደሚገኙ ያምኑባቸዋል ሲል ሲ ኤኤን ዘግቧል::

የዶ/ር አብይ የፈረንጆቹ 2019 ዓመት ዋና ስራም በኢትዮጵያ በ2020 የሚደረገው ምርጫ ነው ሲል ሲኤን ኤን ጠቅሷል::

https://www.youtube.com/watch?v=Pe4vPoSA5JM&t=223s

93437
Previous Story

ጥብቅ መረጃ – በብሔራዊ መረጃና ደህንነት የተገኘው መርዝ

93446
Next Story

በኢትዮጵያ ለሁለት ወራት የሚዘልቅ ጾም፣ ጸሎትና ምሕላ ታወጀ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop