December 21, 2018
2 mins read

ኤርትራዊው ፕሮፌሰር አስመሮም ለገሰ ከኢትዮጵያው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ ጋር ዛሬ ተነጋገሩ፡

93310

ኤርትራዊው ፕሮፌሰር አስመሮም ለገሰ ከኢትዮጵያው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ ጋር ዛሬ ተነጋገሩ፡፡ ዶ/ር ወርቅነህ በፌስ ቡክ ገፃቸው ስለዚህ ጉዳይ ሲገልፁ ‹‹የኦሮሞ ጥናትን መሰረት የጣሉ ብቻ ሳይሆን በገዳ ስርዓት ለማጣቀሻ የበቁ አያሌ መፅሀፍቶችን የፃፉ እና ጥናቶችን ያደረጉ የገዳ ስርአት በዩኒስኮ እንዲመዘገብ ከፍተኛ ኣስተዋፅኦ የነበራቸውን ፕሮፌሰር አስመሮም ለገሰ ዛሬ በፅ/ቤት ተቀብለን አነጋግረናቸዋል።›› ብለዋል፡፡

ዶ/ር ወርቅነህ ጨምረውም የገዳ ስርአት አባት ያሉዋቸው ፕ/ር አስመሮም ለኦሮሞ ጥናት ላደረጉት አስተዋፅኦ ከፍተኛ ምስጋና እንዳቀረቡላቸው አስረድተዋል፡፡ ፕሮፌሰር አስምሮም በኤርትራና የኦሮሞ ህዝብ መሀከል ድልድይ መሆናቸውን የገለጹት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ ለቀጣይ ጥናቶቻቸው በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል ድጋፍ እንደሚደረግላቸው ገልጸዋል።

በዚህም ፕሮፌሰር አስምሮም ለገሰ በበኩላቸው ኤርትራዊ ይሁኑ እንጂ ልባቸውና ቀልባቸው ከቦረና ኦሮሞዎች ጋር ሆኖ እንደቆየ ተናግረዋል፡፡ ‹‹የቦረና ህዝብ ባህል መዋሸት፣ መስረቅና መግደልን ነውር ያደረገ ነው›› ያሉት ፕሮፌሰሩ ህብረተሰቡ ስለገዳ የበለጠ ዕውቀት እንዲኖረው በሌሎች ቋንቋዎች የተፃፉት ስራዎችም መተርጎም ይገባል ብለዋል፡፡ ፕሮፌሰር አስምሮም የኦሮሞ ጥናትን መሰረት የጣሉ ብቻ ሳይሆን፥ በገዳ ስርዓት ለማጣቀሻ የበቁ አያሌ መፅሀፍቶችን የፃፉና ጥናቶችን ያደረጉ መሆናቸውን ከዚህ ቀደም መዘገባችን ይታወሳል፡፡

https://www.youtube.com/watch?v=s58PBvypjSM

7
Previous Story

አርበኞች ግንቦት 7 በአዲስ አበባ ዋና ዋና አደባባዮች ቅስቀሳ ሲያደርግ ውሏል

30
Next Story

ደምስ በለጠ ከአገሩ ከወጣ ከ30 አመታት በኋላ ዛሬ ወደ ኢትዮጵያ በገባ በ21 ቀኑ በተኛበት አርፎ ተገኘ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop