ቴዲ አፍሮ በአዲስ አበባ ሊያደርገው የነበረው የሙዚቃ ኮንሰርት ፈቃድ ተከለከለ

/

(ዘ-ሐበሻ) ‘ኢትዮጵያ’ የተሰኘውን አዲሱን አልበሙን ለሕዝብ አቅርቦ ተወዳጅነቱን የጨመረው ቴዲ አፍሮ ለአዲሱ ዓመት በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ ሊያደርገው የነበረው ኮንሰርት ፈቃድ እንደተከለከለ ተሰማ::

ለኢትዮጵያ አዲስ ዓመት ዋዜማ በሚኒሊኒየም አዳራሽ ይደረጋል ተብሎ ሲጠበቅ ለነበረው ለዚሁ ኮንሰርት ቴዲ አፍሮ ፈቃድ ያስገባው ከሁለት ወር በፊት ሲሆን በተለያዩ ምክንያቶች ሲስተጓጎል ቆይቷል:: ቴዲ ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባ ከተማ ሊያደርጋቸው የነበሩ ኮንሰርቶች አስተዳደሩ በቂ ጥበቃ ኃይል የለኝም በሚል ምክንያት ሲከለክለው ቆይቷል::

የቴዲ አፍሮ ኮንሰርቶች ሲከለከሉ የሚሰጠው ምክንያት የጥበቃ ኃይል እጥረት ይሁን እንጂ ትክክለኛው ምክንያት ይህ አይደለም የሚሉት አስተያየት ሰጪዎች ጉዳዩን ከፖለቲካ ጋር ያያዙታል::

 

በአዲስ አበባ ከተማ ሌሎች ድምጻውያን ካለምንም እክል ኮንሰርቶችን እንደሚሰሩ ይታወቃል::

ቴዲ አፍሮ ለአዲሱ ዓመት ኮንሰርት ባንዱን ከአሜሪካ አስገብቶ የአዲሱን አልበም ዘፈኖች ሲያጠኑ የቆዩ መሆኑን የሚገልጹት ምንጮች ከመጪው ሴፕቴምበር መጨረሻ ጀምሮ በሰሜን አሜሪካ እየተዟዟረ ሥራውን ያቀርባል ብለውናል:: አትላንታ ውስጥ የሚኖር አንድ ፕሮሞተር የቴዲ የሰሜን አሜሪካ ኮንሰርቶችን በአጠቃላይ እንደገዛቸው የዘ-ሐበሻ ምንጮች አረጋግጠዋል::

ተጨማሪ ያንብቡ:  አንዳርጋቸው ጽጌና የግንቦት 7 ኃይል አመራሮች ላይ የተቀናበረው የግድያ ሙከራ ከሸፈ

4 Comments

  1. “With approximately 142 Americans dying every day in USA, America is enduring a HUMAN death toll equal to Sept. 11,2001’S ATTACK every three weeks,”
    Concerts are for junkies in Addis Ababa.I was in Addis Ababa, Ethiopia for an extended vacation and noticed that in Addis Ababa , Ethiopia people tend to escape the doctor visitation fees and spend their scarce money on the medicines buying them directly from pharmacy employees without prescriptions .when people get sick since most already know what they are going to be prescribed from past experiences they escape the doctor visit or they forge the doctor’s signatures and go to the pharmacists directly. At the same time some are using these illegally purchased pills solely for recreational purposes.Returnee diasporas and foreign nationals are giving Medications bought at black market as birthday presents to the young college students regularly in Ethiopia .Especially those that go to Ethiopia from USA had introduced a culture of using opioid medication pills for recreational purposes to locals . Currently you find drop out college students and other people prostituting themselves allover Addis just to get a fix to satisfy their opioid addictions.
    The opioid epidemic that took USA by storm is drizzling in Ethiopia as well. The storm in USA is about to force President Donald Trump to declare a national emergency in response to the nearly 142 Americans killed each day by the opioid crisis gripping the United States, a bipartisan White House panel has found. “With approximately 142 Americans dying every day, America is enduring a death toll equal to Sept. 11 every three weeks,” wrote members of Trump’s bipartisan committee, referring to the 9/11 terrorist attacks on the American homeland that killed nearly 3,000 people. “Your declaration would empower your cabinet to take bold steps and would force Congress to focus on funding and empowering the executive branch even further to deal with this loss of life.”

    http://www.breitbart.com/national-security/2017/08/01/white-house-on-opioids-overdoses-u-s-enduring-a-death-toll-equal-to-911-every-3-weeks/

  2. ***ቴዲ አፍሮ ለአዲሱ ዓመት በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ ሊያደርገው የነበረው ኮንሰርት ፈቃድ እንደተከለከለ:: በአዲስ አበባ ከተማ ሌሎች ድምጻውያን ካለምንም እክል ኮንሰርቶችን እንደሚሰሩ ይታወቃል!?
    — ቦይ ኮት! የልዩ ጥቅማጥቅመኞች ሕገ መንግስታዊ መብት ኳስ አብሮ አያጫውት፡ አብሮ ሙዝቃ አያጫውት፡ አስለምኖና አስፈቅዶ የሚንቀሳቀስ ቦርቃቃ ብሔር ብሔረሰብ እና ሕዝብ ምሊነየም አዳራሽ የፈጣሪው ህወኣት አደለምን? አሁን የሙስና መር ሀዘን ላይ ጭፈራ አለን? ኢንቨስተሮቻቸው የተነኩ እንኳን ጭፈራ ቀብር ያስተጓጉላሉ። ልዩ መንግስት አደሉምን!?

  3. በጣም የሚያሳዝን የሚያሳፍር ነው ህዋቶች የሚያደርጉት፡፡ ቆይ ከሀገሩ ውጪ ከህዝቡ ውጪ የት ሄዶ ያቅርብ ለራሳቸው የአሸንዳ በአል ሲሆን ግን በቂ ጥበቃ አላቸው ብቻ የቴደዲና የኢትዮጵያ አምላክ ፍርዱን ይስጥ

Comments are closed.

Share