በሁመራና በአማህጅር የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከሕወሃት ታማኞች ጋር መዋጋታቸው ታውቋል

በልኡል አለሜ
በሁመራና በአማህጅር እንዲሁም በአርማጭሆ የተሰማራዉ የመከላከያ ሰራዊት በጀግናዉ የአማራ ገበሬ ህዝብ ላይ አንተኩስም በማለት እርስ በእርሱ ጦር መስበቁን የዉስጥ አርበኞች አስታወቁ!
ትናንት አንድ የኦሮሞ ብሄር የመከላከያ ሰራዊት በግንባር ላይ በግዳጅ በተሰማራበት ሁኔታ እጅግ ያስቸገረ የህወሃት አመራር የሆነ መቶ አለቃን ከገደለ ወዲህ እራሱን በማጥፋቱ የተነሳ የኡማህጅር የጠረፍ ጥበቃ እና ጸረ ሽምቅ ዉጊያ ተዉጣጪ ቡድን አፈ ሙዙን በማዞር ከደጀን ጦር ጋር ተፋልሞአል።
በዚህ ድንገተኛ እልህ የተሞላበት ዉጊያ የተነሳ የህወሃት ሄሊኮፍተሮች ሳይቀሩ የተሳተፉ ሲሆን የአማራና የኦሮሞ ተወላጅ የመከላከያ ሰራዊት አባላት በተደጋጋሚ ፊታቸዉን በማዞር ካደረጉት ዉጊያ ይህኛዉ ከበድ ያለ መሆኑና ከሁለቱም ወገን 102 ወታደሮች መሰዋታቸዉንና 41 መቁሰላቸዉን 1 ታንክ መቃጠሉን መረጃችን ጠቁሞአል፤
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !!

ተጨማሪ ያንብቡ:  የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አማሮቹን ያፈናቀልነው በስህተት ነው አሉ
Share