23/45….የምድር ሲኦል!

“የአማራ ክልል ልጆች የሚሰቃዩበት ልዩ ቦታ…2345-ሃያሶስትአርባምስት!” ታውቋል። 2345 ቁጥር አይደለም። በዚህ ልዩ የኮድ ስም የሚታወቀው ቦታ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ፓዊ ከተማ መንደር 7 የሚባለዉ አካባቢ ከመድረሳችን በፊት በስተቀኝ በመታጠፍ ወደ ዉስጥ 25 ኪሎ ሜትር አካባቢ ገባ ብሎ ገደል ዉስጥ የሚገኝና በሀገራችን ከሚገኙት ማሰቃያ ቦታዎች መካከል የመጨረሻ አስከፊው ቦታ ነው።
ይህ የመጨረሻ አረመኒያዊ ተግባራት የሚፈፀሙበት ቦታ ዙሪያ ገባዉን ግራርን በመሰሉ ዛፎች ጥቅጥቅ ደን የታጠረ፤ የደገላ ሳር በሚባሉት ረጃጅም የበረሃ ሳሮች የተከበበ በዉስጡ ለሰው ልጅ አደገኛ የሆኑ አዉሬዎች የሞሉበት፤ በአለም ላይ እጅግ መርዛማ የሆኑ እባብና ጊንጦች የሞሉበት፤ እንስሳትን ሳይቀር በጥቂት ደቂቃዎች የሚውጡ ዘንዶዎች የተከማቹበት፤ ከአካባቢው ከፍተኛ ሙቀት የተነሳ እዚህ ጉድጓድ ማሰቃያ ቦታ ውስጥ ለተወሰነ ጊዜ የሚቆይ ሰዉ የቆዳ ቀለሙ በራሱ ተጠብሶ ወደ ካርቦናማነት እንደሚለወጥና የአካባቢው ሰዉ እራሱ አካባቢው ላይ ከአደገኛነቱ ባሻገር ለሚስጥራዊነቱ ሲባል ወደዛ አካባቢ እንዲቀርብ የማይፈለግበት ከአለም የተገለለ እጅግ አሰቃቂ የበረሃ ጉድጓድ ማሰቃያ ቦታ ነዉ።
ከዚህ የምድር ሲኦል ለማምለጥ የሚሞክር ግለሰብ ካለም የምን ሰለባ ሊሆን እንደሚችልና ምን እንሚያጋጥመው መገመት አይከብድም። እዛ አካባቢ በሕይወት አጋጣሚ ደርሶ የመጣ ግለሰብ እንዳስረዳኝ ከሆነ እዛ የበረሃ ሲኦል ዉስጥ የገባ ሰው የት እንዳለ በምንም መንገድ የሚያውቅበት ሁኔታ የለም ብሎኛል። ይህ አካባቢም ከሃገራችን ማህበረሰብ የተሰወረና በሃገራችን ዉስጥ ከሚገኙ እንደ ብርሸለቆ፤ ሽዋሮቢት፤ ዴዴሳ አይነት ታዋቂ ማሰቃያ ቦታዎች ስም ዝርዝር ዉጭ የሚገኝ በስዉር ለሺዎች ኢትዮጽያዊያን በማሰቃያነት በወያኔ አማካኝነት ለአመታት አገልግሎት ላይ እየዋለ የሚገኝ ሚስጥራዊ ቦታ ነው። እንግዲህ በዚህ ቦታ ነው ከ2ሺ ያላነሱ የባህር ዳርና የጎንደር ወጣቶች ስቃይ ላይ ናቸዉ የተባለው።
2345….የምድር ሲኦል! በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል!

ተጨማሪ ያንብቡ:  “ከሃገሬ የወጣሁበት ቀን በረዘመ ቁጥር፣ ሀገሬ ላይ በጣም ክህደት የፈፀምኩ ያህል ይሰማኛል” - ታማኝ በየነ (ቃለ ምልልስ ከተመስገን ደሳለኝ ጋር)

አበራ አየለ

Share