ሰለኮሎኔል ታደሰ ጥቂት ልበል፡

ከፍል2
ይታያል የሩቅሰው
ወደ እለቱ ተግባራዊ ቅኝቴ ለመግባት፡ ባለፈው ሳምንት በዚህ አርእዕስት የከተብሗትን፡ ጦማሪን ስደመድም፡ ኮሎኔል ታደሰ ሙሉነህ፡ ወደአሜሪካን ባቀናበት ወቅት፡ በዚያው እንዲቀር ለቀረበለት ጥያቄ፡ የሰጠው መልስ፡ወያኔ ውሎ ካደረ ኢትዮጵያ የምትባል ሃአገር አትኖርም፡ እናም ቢሆን ከጥፋት አድናታለሁ፡ ካልሆነም ጥፋቷን ሳላይ ማንም ያጥፋኝ ማን ስከላከልላት እኔ ቀድሜያት፡ እጠፋለሁ፡ ሞት እንደሁ ፈራንም ደፈርን፡ የማይቀር የተፈጥሮ እዳችን ነው። የሚል እንደነበር በመጥቀስ ነበር፡፡ ወደዛሪው የምገባው ደግሞ የሚከተለውን ጥያቄ ለመመለስ በመሞከር ነው።
2.1.የመሰወሩ ምክናያቶችስ ምንና እነማን ናቸው?
ነገሩ እንዲህ ነው፣በኮሎኔል ታደሰ ሙሉነህ፡ የሰከነና፡ በእውቀት ላይ የተመሰረተ አመራር፡ በእነ ቱሗት፣ በእነ ጁማ፣ በእነ ዮሴፍ፣ በእነተ ስፋዬ፡ ትጋትና የዓላማ ጽናት፡ ያልተለየው የሌት ከቀን እንቅስቃሴ፡ በክፍል አንድ ማብራሪያዬ፡ እንደጠቀስሁት፡ የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር፡ በአጭር ጊዜ ተጠናክሮ፡ ጥቃት መሰንዘር ከሚያስችለው ደረጃ ላይ እየደረሰ ሲመጣ፡ በውጭ ሀገራት የሚኖሩ በርካታ፡ ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን፡ እቦታው ድረስ በመሄድ ጎብኝተው፡ ትግሉን በማበረታታት ወደ እየመጡበት ሲመለሱ፡ ፕ/ር ሙሴ ተገኝ ግን፡ ጓዙን ጠቅልሎ አስመራ በመግባት፡ አይዟችሁ በማለት ፋንታ፡ ከተማ ቁጭ ብሎ፡ የግንባሩ መሪ ለመሆን ባለው ህልም፡ ይሁን በሌላ ልዩ ተልዕኮ፡ ባለየለት ምክናያት፡ በኤርትራ ባለስልጣናት ቢሮዎች እየዞረ፡ እነኮሎኔል ታደሰን፡ እነዚህን ደርጎች፡ እንዴት ታምኗቸውአላችሁ፡ በማለት ማጥላላትን ስራየ ብሎ ይይዛል፡ አመራሩ ግን፡ ከሗላው እየተለቀለቀበት ያለውን ጥላሽት፡ በማያውቅበት ሁኔታ ላይ ሆኖ፡ ብዙ ኩነቶችን ከዳሰሰና፡ ካጠና በሗላ የውጊያ እቅድ ሲነድፍ፡ አንድ መደምደሚያላይ ይደርሳል። እሱም የትግሉ መሰረት የጎረቤት ሀገር ሳይሆን ሃገር ቤት መሆን አለበት። የወደቀው ወድቆና ያለቀው አልቆ፡ ሀገራችን ላይ ነጻመሪት ሊኖረን ይገባል፡ የሚለው ተወስኖ ጠቅልሎ ለመግባት የ6ወር ጊዜ ገደብ ተቀምጦለት፡ ዝግጅት ይጀመራል፡ ጉዳዩም በሚስጥር እንዲያዝና ከስራ አመራሩ በቀር ለማንም እንዳይወራ፡ ተስማምተው በእየተመደቡበት የስራ ዘርፍ ደፋቀና በማለት ላይ እንዳሉ፡ ከ7ቱ አመራር አባለት መካከል አንዱና በገንዘብ ያዥነት፡ የተመደበው አበሩ አታላይ ማለት ዛሪ ስሙን ቀይሮ መስከረም ነኝ ያለውና፡ ጀርመን ሃገር የሚኖረው፡ ለህክምና ብሎ አስመራ በሄደበት ከፕ/ር ሙሴ ተገኝ ጋር ተገናኘቶ 2ቱ የተንኮል ሴራ ሽርበው፡ በጋራ ከአንድ የሻብያ ቱባ ባለስልጣን ቢሮ ቀጠሮ አስይዘው በመግባት፡ እነዚህ ደርጎች እነ ኮሎኔል ታደሰን ማለት ነው፡ ጓዛቸውን ጠቅልለው ሀገራቸው ሊገቡ ወስነው እየተዘጋጁ ነው ያሉት፡ እንዲያውም፡ በመጀሪያ፡ ወያኔን ቀጥለን ሻብያን፡ እንደመስሳለን፡ ሀገራችን ወደብ አልባ ሆና አትቀርም ነው የሚሉት፡ በማለትና ሌሎች ሻብያን ሊያበሳጭ ይችላል ያሉትን ውሽት በመደርደር፡ መረጃ ሰጥተውና ለቀጣይ መመሪያ ተቀብለው ይወጣሉ። ከዚያች እለት ጀምሮ እነ ኮሎኔል ታደሰ በሻብያ አይነ ቁራኛ መጠበቅ ይጀምራሉ፡፡ አበሩ አታላይም ወደግንባር ተመልሶ፡ የጎንደር አካባቢ ተወላጅ ሲያገኝ፡ ጎነደሬ፡ የትግራይ ካባቢ ተወላጅ ሲያገኝ፡ ትግሬ ነኝ በማለት፡አቅሙ በፈቀደ መጠን ሰራዊቱን፡ በመንደር መከፋፈሉን ያጧጡፋል።
ነገር ከስሩ ውሃ ከጥሩ እንዲሉ፡ ለአነባብያን፡ የበለጠ ግልጽ እንዲሆን፡ ትንሽ ወደሗላ ሄጄ፡ ሰለ አበሩ አታላይ፡ ማንነት በአጭሩ፡ አንድ ሁለት ልበል፡ ተጠቃሹ፡ ወልቃይት ውስጥ ነው ተወልዶ ያደገው፡ ትምህርት፣ የሚሉት ነገር ባህላዊዩም ሆነ ዘመናዊዩ አልነኩትም በፍጹም አይተዋወቁም፡ በማህበራዊ ኑሮውም በአካባቢው የተጠላ ነበር፡ ያነን ማንነቱን የፋቀልኝ መስሎት ሳይሆን አይቀርም ስሙን መቀየር ያስፈለገው። ይህ ግለሰብ የሚኖርባት መንደር የጎንደር ክፍለሀገር ክልል ሆና፡ የትግራይንና የኤርትራን ክፍላት ሀገራት በቅርብ እርቀት የምታዋስን በመሆኗ፡ በደርግ ዘመን፡ በሚፈጽማቸው አስነዋሪ ተግባራት፡ ምክናያት በፖሊስ፡ ጎንደር ሲፈለግ ትግራይ፣ ትግራይ ሲፈለግ ኤርትራ፡ እያለ በማስቸገር ሲኖር፡ በአንድ ወቅት ብልሁ የሀገሪ ሰው በዘዴ ለመገላገል፡ሲል ለአካባቢ ህዝባዊ ሰራዊትነት መልምሎ እንዲሰለጥን ይልከዋል፡ አበሩ ከተላከበት ጠፍቶ ወደመንደሩ ሲገሰግስ አዘዞ ላይ ተይዞ፡ በሀገር ክህዕደት ወንጀል ተፈርዶበት እስር ቤት ይገባል፡ ጨርሶ ሲወጣ፡ ወደመንደሩ ሄዶ የተለመደ ስራውን ሲያከናውን፡ ወያኔ ሀገሪቷን ይቆጣጠራል፡ ወያኔዎች እንደገቡ ሌባ ይገድሉ ስለነበር እንዳይገደል ፈርቶ፡ ወደሱዳን ይሸሻል፡ እዚያም ከፋኝን ተቀላቅሎ፡ እያለ የከፋኝ መስራችና ነባር አባላቱም ሆኑ መሪዎቹ በዩ.ኤ.ን. አማካኝነት፡ ወደተለያዩ ምእዕራባውያን ሀገራት ሲሄዱ፡ እሱ በመቀረቱ፡ በአቶ ዮሴፍ ያዘው የሚመራውን፡ የኢትዮጵያ ህዝቦች ዲሞክራሴያዊ ግንባርን፡ተቀላቅሎ ኤርትራ ይገባና፡ የትግሪኛ ቋንቋ ተናጋሪነቱን፡ እንደ ማንነት መገለጫ በማቅረብ፡ በድብቅ በአካባቢው፡ ላገኛቸው የኤርትራ ባለስልጣናት ኤርትራዊ እነቱን በመንገር፡ የሻብያ አባል ይሆንና፡ አብረውት የተሰደዱ ኢትዮጵያንን፡ እንዲሰልል ግዳጅ ተሰጥቶት እያለ ነው ተጨማሪ ሐይል ሙሴ ተገኝን ያገኘ።
ስለ መስከረም አታላይ፡ ከብዙው በጥቂቱ፡ ይህነን ያህል ካልሁ ወደ ኮሎኔል ታደሰ ልመለስ፡ እነኮሎኔል ታደሰ ባላወቁት ነገር በሻብያ ጥርስ ተነክሰው፡ የሚደነቀርባቸውን ሁሉ መሰናክል በትግስት እያለፉ፡ ስራቸውን በማፋጠን ላይ እንዳሉ፡ ከእለታት አንድ ቀን በሻብያ ሰራዊት ተከብበው፡ አመራሩ እንዲበተን ይደረጋል፡ ከዚህ በሗላ ኮሎኔል ታደሰ፡ ከአስመራ እንዳይወጣ ሲደረግ ቱሗት ፖልና ጁማ እሩፋኤል፡ ከኤርትራ እንዲወጡ፡ ዮሴፍ ያዘው ከተሰኔይ ከተማ እንዳይወጣ፡ ሲደረግ ተስፋዬ ጌታቸው፡ አዚያው ሃሪና በርሀውስጥ እንዲታሰር ተወሰነበት፡፡ይህ ከመከናወኑ ቀደም ብሎ ግን የግንባሩ አመራር ከነደፈው፡ መርሃግብር አንዱ የሆነውን አርበኛው፡ ከኤርትራ ነቅሎ ሲወጣ፡ መሰረቱን የሚጥልበትን ቦታ፡ አጥንቶ እንዲመለስ የተመደበውን ቃኝ ሃይል፡ በሃላፊነት መርቶ የሚሄድ አንድ ሰው ለመምረጥ፡ በተደረገ ውይይት ላይ፡ አበሩ ወይንም መስከረም አታላይ፡ በእራሱ ፈቃድ እኔ ልሂድ ስለአለ፡ በሃላፊነት መርቶ እንዲሄድ ይደረጋል፡ አበሩ ከፊሉን አስገድሎና ከፊሉን፡አስማርኮ፡ እሱ ብቻውን፡ ጥይት አይደለም እንቅፋት ሳይመታው፡ ከመመለሱም በላይ ኪሱ ውስጥ በርካታ ዶላር በመገኘቱ፡ ጉዳዩ አጠራጣሪ ሆኖ ስለተገኘ፡ እስኪጣራ አመራሩ አስሮት ከነበረበት፡ በሻብያ ትእዕዛዝ ተፈትቶ፡ አሁንም ያለምርጫ፡ በሻብያ ትእዛዝ የግንባሩ፡ አዛዥ እንዲሆን ሲመደብ፡ በአንድ በኩል የፕ/ር ሙሴ ተገኝ የመሪነት ህልምን ሲያከስም፡፡ በሌላበኩል ሰራዊቱን፡ አስቆጥቶ፡ ከመበታተን፡ ደረጃ አደረሰውና፡ የተበተነው የሰው ሐይል፡ ከፊሉ ሱዳን ሲገባ ከፊሉ ደግሞ ወደሀገሩ የተመለሰ ሲሆን፡ ሁለቱንም ማድረግ ያልቻለው፡ መሀይም አይመራንም፡ አበሩ አታላይ፡ ታደሰ ሙሉነህን ሊተካ አይችልም፡ በማለት፡ የደቡብ ህዝቦች፡ የሲዳማ ህዝቦች፣ የጋቤላ፣ የቤንሻንጉል ወ.ዘ.ተ. በሚል ተከፋፍሎ፡ እነሆ ዛሪ የምንሰማውን 8 የብሄረሰብና የቋንቋ ድርጅት አቋቁሞ፡ እዚያው ኤርትራ ውስጥ እየኖረ ይገኛል። አበሩ አታላይም፡ በጣም ጥቂትና በግንዛቤም ሆነ በአቅም የሚመሳሰሉተን፡ የመንደሩን ልጆች አሰባስቦ፡ የአርበኛ ግንባር የሚለውን ስም፡ እንደያዘ አዛዥ ነኝ በማለት፡ ተስፋዬ ጌታቸውን ጉድጓድ ውስጥ አስሮ እንደውሻ በዱላ ደብድቦ ገደለው። በዚያን ጊዜ በአበሩ አታላይ፡ የተጀመረው፡ ወያኔን የምንጠላበት፡ የመንደርተኝነት፡ አባዜ እረ ወያኔስ ቢያንስ ከፍ አድርጎ፡ በቋንቋ ነው የከፋፈለን፡ አበሩ ግን አውርዶ፡በቀበሌ ገነጣጥሎን፡ አርበኛ ግንባር ውስጥ አሁንም ድረስ ተጠናክሮ እየሰራ ሲሆን፡ አመራር አይደለም፡ የአርበኛ ግንባር ታማኝ አባል ለመሆን፡ ቢሆን ወልቃይት፣ ካልሆነም ጎንደር መወለድ የግድ ይላል፡፡ ባልተጻፈው በእነ መስከረም፣ ማእዛው መመሪያና ደንብ፡ መሰረት፡፡ ለዚህም ነው አረበኛ ግንባር በተለያየ ጊዜ ከገደላቸው፡ ሁሉ ምሁራን፡ መካከል ከካሳሁን ወንዴ በቀር ጎንደር ክፍለሀገር የተወለደ፡ ሌላ2ኛ ሰው የማይገኝበት።
ከእነ ታደሰ ሙሉነህ፡ በሗላ ያለው አርበኛ ግንባር፡ ተስፋዬ ጌታቸውን ብቻ አይደለም የገደለው ወደፊት ታሪክ የሚያወጣቸው፡ ለመታገል የገቡ በመቶወች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ምሁራንን፡ እንክት አድርጎ በልቷል፡ ለዚህ ድርጅት አመራር አካላት ፊደል የቆጠረ ሰው፡ ከወያኔ በላይ ያስፈራቸዋል፡፡
መስከረም አታላይ፡ እሱ በሻብያ እንደተሾመ ሁሉ ከ3 አመት ቆይታ በሗላ፡ ወደጀርመን ሲጓዝ በተራው ደገሞ፡ መጻፍና ማንበብ የማይችለውን፡ የታላቅ እሀቱን ልጅ፡ ማእዛው ጌቱን፡ ሾሞት ስለሄደ 9 አመት ሙሉ አርበኛ ግንባር፡ የሚመራው በእሱ ነው፡ ያሳያችሁ እንግዴህ በተራቀቀ ሳይንስና ቴክኖለጅ፡ የሚጠቀምን ጠላት ለማስወገድ እታገላለሁ የሚል ጦር አዛዡ፡ ይህ ሰው ነው፡ ታዲያ፡ ለምን አይዳከም? ለምንስ አይክሰም? በእውቀት የበሰሉ፣ በሙያው የተካኑ፣ ኢትዮጵያውያን ሲቀላቀሉት፡ ፈጥኖ
ይበላቸዋል፡ ለእነማዛው ስልጣን ስለሚያሰጉ። የኮሎኔል ታደሰ መሰወር መንስኤው ሌላ ምንም ሳይሆን ይኸው ነው፡ ለእነማእዛው ስልጣን እንዳያሰጋ ገለል ማለት አለበት። ኮሎኔል ታደሰ ሙሉነህ፡ ከአስመራ እንዳይወጣ ተወስኖበት ሲኖር፡ ከዲያስፖራ አርበኛውን ለመጎብኘት የሚሄድ፡ ሁሉ ኢትዮጵያዊ የአመራሩን ደካማነት ሲያይ፡ በማዘንና ተስፋ በመቁረጥ፡ ምናለ ኮሎኔል ታደሰ አመራሩን እንዲረከባችሁ ብታደርጉ የሚል ከቅንነትና ከመቆርቆር የመነጨ፡ አስተያይት፡ ተደጋግሞ እየተሰነዘረ ስላስቸገራቸውና፡ኮሎኔል ታደሰ አመራሩን ተረክበ ማለት ደግሞ፡ በምርጫ የማይቀየረውና፡ በማእዛው፡ የሚመራው 7ቱ የስራአመራር፡ ኮሚቴ ከዲያስፖራ እየተዋጣ፡ የሚላክላቸውን ዶላር በማዘርዘር፡ ተሰነይና ጉልሽ ከተሞች ላስቀመጧቸው የኤርትራ ቆነጃጅት፡ አልባሳትና ከእግር ጥፍራቸው እስከ እራስ ጸጉራቸው፡ የሚንቀለቀሉበት ወርቅ፡ መግዛቱ የሚቆም ከመሆኑም በላይ፡ ያመራር ቦታው፡ ወልቃይት በመወለድ ሳይሆን፡ በብቃት በሹመት ሳይሆን በሰራዊቱ የተመረጡ ሰዎች የሚይዙት ስለሆነ፡ ከአዛዥነት ወደታዛዥነት ሊወርዱ ነው፡፡ ይህ እንዳይሆን ዘላቂ መፍትሄና፡ ስጋትን አስወጋጅ ነው ብለው ያሰቡት፡ ኮሎኔል ታደሰን፡ ወንጅሎ ቢሆን ተላልፎ ለእነሱ ተሰጥቷቸው፡ እንደተስፋዬ ጌታቸው፣ እንደ ካሳሁን ወንዴ እንደ ጌታቸው ብርሃኑ እንደ ወርቅነህ መበሩ፡ ወ.ዘ.ተ.ጉርጓድ ውስጥ አስረው በውሃጥምና በእራብ አሰቃይተው፣እንደውሻ ዱላ ደብድበው በመግደል፡ አለዚየም፡ እንደ ሌሎች በመቶ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን፡ ታጋዮች በጥይት መረሸን፡ ካልሆነም በማሳሰር፡ ብቻ በሆነ ነገር ኮሎኔሉን ከአካባቢው፡ በማጥፋት እሱ ይምራችሁ የሚለውን ጥያቄ፡ ማንም እንዳያነሳባቸው ማድረግ ስለሆነ፡ ለዚህ ግባቸው መሳካት ደግሞ ውሸት ፈብርኮ ለኤርትራ መንግስት ታደሰ ሊያሰራን አልቻለም፡ በማለት የማያቋርጥ አቤቱታ ማቅረብ፡ ስለነበረባቸው፡ ከእረጅም ጊዜ ጥረት በሗላ እርኩስ ዓላማቸው ተሳክቶላቸዋል።
እስካሁን ግልጽ ያልሆነው ግን ኮሎኔል ታደሰን፡ የኤርትራ መንግስት እራሱ አስሮታል? ወይንስ አሳልፎ ለዚህ ወልዶበላ ድርጅትና፡ ግብዝና መሀይም መሪዎች ሰጥቶታል? የሚለው ነው። ይህነን እርዕስ ለማጠቃለል መነሻዬን ማስታወሱ ተገቢ ይመስለኛልና፡ የመሰወሩ ምክናያቶችስ ምንና እነማን ናቸው፡ የሚለውን ከዚህ በላይ በዝርዝር ለማሳየት ሞክሪያለሁ፡ ጠቅለል አድርጌ ለማስቀመጥ፡ ደግሞ ለዚህ ጀግና እና እውነተኛ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ መሰወር፡ መነሻውም መድረሻውም፡ አንድና አንድ ብቻ ነው፡ እሱም በስሟ እየነገደ ከወያኔ ባልተናነሰ ሁኔታ ብርቅዬ ልጆቿን እንደምስጥ እንክት አድርጎ የበላውና እየበላ ያለው፡ ካልተነቃበት ለወደፊትም ከመብላት የማይገታው የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ነው።
ለዛሬ በዚህ ላብቃ ቀሪውን ሳምንት በክፍል3 እመለስበታለሁ ለዚያ ሰው ይበለን ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን ይጠብቅ አሜን

ተጨማሪ ያንብቡ:  ልብን የሚነካዉ የኢትዮጵያዉያን ጉዞ በሳዑዲ አረቢያ

3 Comments

  1. ስለ ኮነሪል ታደሰ የጻፍክበትን ብስማበበትም ዲስፖራው የሚጠበቅበትን አላደረገም ማለት ለማስፈታት የተደረገ ጥረት የለም በተወሰነ መልኩ ታማኝ በየነ የሻብያውን መሪ እንዳነጋገር ወይም መልክት እንዳስተላለፈ ሰምተናል ። አሚሪካ ውስጥ እራሱን የቻለ የ ኢትዮጵያ አየር ሃይሎች ማህበር እንዳለም እንሰማለን ለምን በነሱ በኩል ለቀይ መስቀል እና ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት በማስታወቅ ኮነሪል ታደስና ኮነሪል በዛብይ ከሻብያ ጥርስ የሚወጡበትን መንገድ አያፈላልጉም። ጽሁፍህ ላይ ግን የአንድ አካባቢ ልጆች ላይ የሃገር ስም እየጠራይ ያደረከውን ወቀሳና ውግዘት አልደገፍኩትም ። ሁሉም ኢትዮጵያው የሚስማማበት ጉዳይ አለ እሱም ኢትዮጵያን ከውያኔ ነጻ ለማውጣት ከሻብያ ጎን ሆኖ መዋጋቱ ግን ምንም ትርፍ እንደለለው የታወቀ ነው። እንደምነሰማው በስማቸው ካልታደለው ዲስፖራ ገንዘብ የሰበሰባል ለሻብያ የጽጥታ ባለስልጣኖች መፈንጠዣ ይሆናል ተራው ሃገሩን ሊታደግ የሂደው ወጣት ግን ሻብያ ምሽግ በማስቆፈር እንጨት ባስፈለጥ ችግኝ በዘራት መንገድ በማስጠረግ እንድሚጠቀምባቸው ነው የምንሰማ ። በእውነቱ በጣም የሚያዛን ነው። እና ወንድሜ ጽሁፍህ ውህደት ያለው ቢሆን መልካም ነው ያንድን አካባቢ ተወላጆችና ሃገር እየጠራህ ይምተውነጅለውን ነገር እረም።

  2. Much,
    I support your comment and it is true. So let all work with wise vision instead of following EPRDF’s path – divide and rule.
    Let’s work our part to free those Ethiopians in Eritrea.
    Lega

  3. ante ahya angethe lay yale bila teteh ye shabia taweraleh mot atwedm yale meswat dill yelem beweree menem aygegnem weyane gena letwld yketlal ant fri slehonk

Comments are closed.

Share