ግልጽ ደብዳቤ ለሃይሌ ገብረሥላሴ (ከአበበ ገላው)

ውድ አትሌት ሃይሌ፣ ከነመላው ቤተሰብህ እንደምን ከርመሃል? ልጆቹ እንዴት ናቸው፣ አለምስ እንዴት ሰንብታለች?
ሰሞኑን የወዳጅ የዘመድ ምክር አላዳምጥ ብለህ እንደነ ጋሼ ግርማና ጋሼ ሃይለማርያም ደሳለኝ የህወሃቶች አሻንጉሊት መሆን እንዳማረህ ስሰማ በጣም ተገረምኩ። በመላው አለም ዝና ያተረፍክበትን እሩጫ ትተህ “ቤተመንግስት” ወይንም “ፓርላማ” ቁጭ ብለህ ዝንብ ማባረር ምን ይጠቅመኛል ብለህ ነው? አንተም እንደነጋሼ ግርማና ሀይለማሪያም በቁምህ ከመሞትህ በፊት ምክሬን ባትሰማ እንኳን ለማንኛውም ይቺን አጠር ያለች ጦማር ልጽፍልህ ወሰንኩ።
እኔ ያቺን “ሪከርድ” የሰበርክባትን ቲሸርት ነፍሳቸውን ይማርና ለዛ ህዝብ ላፈኑ፣ ላሰቃዩ፣ ለረገጡና ለጨረሱ፣ እንኳን በቁማቸው ሞተውም ላስመረሩን የሂትለርና የሞሶሊኒ ግልባጭ በአደባባይ ስትሸልም መካሪ ማጣትህን ገምቻለሁ። ግለሰቡ መሸለም ሳይሆን ተይዘው እንደ ናዚዎቹ ኑረንበርግ ለፍርድ መቅረብ ይገባቸው እንደነበር ጠፍቶህ ነበር ማለት አይቻለኝም። ግን ሃያሉ ፈጣሪ ፍርዱን እንደማያዘገይ አሳየን።

ከሁሉ የገረመኝ ደግሞ ልክ እንደ ህወሃት ካድሬዎች በኢቲቪ ቀርበህ “ታላቅ መሪ” አጣን እንባ አዋጡ እያልክ ካሜራ ፊት እንባ ስትጨምቅ ማየቴ ነበር። ያቺን የዋህ ደራርቱ “ለኛ ብሎ ታገለ፣ መስዋት ሆነ፣” ምናም እያለች ስታነባ በኢቲቪ ሳይ አንተ ሳታሳስታት እንዳልቀረህ በልቤ ገምትኩ። ከተሳሳትኩ ይቅርታ!
ውድ ሀይሌ፣ በህዝብ ዘንድ መከበርና መወደድ በቢሊዮን ዶላር እንኳን እንደማይገዛ ከቱጃሩ አላሙዲን መማር ይቻላል። ቱጃሩ አላሙዲን ሰሞኑን ወደ ዋሽንግተን ከአስር አመት በሁዋላ ሲመጡ የተከራዮት ታላቅ እስታዲየም በህዝብ ይጨናነቃል ብለው ጠብቀው ነበር። ይሁንና ነበር ባይሰበር ሆነና ነገሩ ያን ያሚያህል ስታዲየም እንኳን ሰው ወፍ ዝር ሳይልበት እንደሰማነው ከሆነ አራት ሚሊዮን ዶላር የፈሰሰበት ድግስ ከንቱ ቀርቶ የሚበላው ጠፍቶ ተደፋ:: ቱጃሩም በሃፍረት ተሸማቀው መሰወራቸውን ስነግርህ በታላቅ ሃዘን ነው። ይህ ቱጃር በህዝብ ዘንድ ምን ያህል የተከበሩና የተወደዱ እንደነበር፣ የዛሬን አያድርገውና፣ ሁሉም የሚያውቀው ጉዳይ ነው። ሁሉ አልሳካ ቢላቸው ምስኪኑ ቱጃር ከሩቅ ሆነው አፋችንን ለማዘጋት እየዛቱ ነው። ዝርዝሩን ሰሞኑን አጫውትሃለሁ::
2
ቱጃሩ ድንገት በምርጫ 97 (ዝ)ንባቸውን በኩራት ደረታቸው ላይ ለጥፈው “ለህወሃት እሞታለሁ እያሉ ያዙኝ ልቀቁኝ” አበዙ። አስተዋዩ ህዝባችን ፊቱን አዞረባቸው። በቃ፣ ያሁሉ ቢሊዮን ከንቱ መሆኑ ታየ። ገንዘባቸውም አድናቂ አጣ፣ እርሳችውም ክብር እና ፍቅር በገንዘብ እንደማይሸመት ተረዱት። ዛሬ የሚያጅቧቸውም ጥቂት ግለሰቦች እርሳቸውን ሳይሆን ገንዘባቸውን ያፈቀሩ መሆኑ ያደባባይ ሚስጥር ነው። በዚህ በክፉ ቀን ህዝብን ከከዳህ ቀባሪህ ጅብ እንጂ ሰው አይሆንም።
ወደ ተነሳሁበት ቁም ነገር ልመለስና ስለምኞትህ ትንሽ አስተያየት ልሰንዝር። ከሚድያ መረዳት እንደቻልነው ሁለት ምኞቶች አሉህ። አንደኛው የመቶ አለቃ ግርማን መቀመጫ መረከብ ሲሆን ሌላው ደግሞ የፓርላማ አባል ለመሆን ነው። እኔንም የገረመኝ የምኞቶችህ ከንቱነት ነው።
እንደምታውቀው “ፕሬዚዳንት” ተብሎ የሚሰየመው ሰው የህወሃቶች አሻንጉሊት ሆኖ ዋና ስራው እንግዶች መቀበልና መሸኘት ነው። ዶሮን ሲያታልሏት ሆነና ነገሩ አቶ መለስ ይህ “ስልጣን” የሚገባው ኦሮሞ ለሆነ ሰው ነው ብለው ባደባባይ ወስነው ስለነበር ቦታውን ሁለት የኦህዴድ አባላት ይዘውት ቆይተዋል። ኦህዴድ እንደሚታወቀው የፈጣሪው የህወሃት ሎሌ እንጂ ታላቁን የኦሮሞን ህዝብ ፈጽሞ አይወክልም። ኦሮሞ ኢትዮጵያዊያን የጠየቁት እውነተኛ እኩልነት እንጂ አሻንጉሊት እንዳልሆነ እንኳን አዋቂ አፍ ያልፈታ ህጻን የሚያውቀው ጉዳይ ነው።
የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት ነጋሶ የነበሩ ሲሆን እርሳቸውም አሻንጉሊትነት በቃኝ ብለው ጥያቄ መጠየቅ ሲጀምሩ እንዲነሱ ተደረገ። አንተ ጎበዙ እሯጭ በምን መስፈርት ነው ታዲያ ፕሬዚዳንት መሆን ያማረህ? የዘር መሰፈርትን ካላሟላህ፣ እጅና እግር እያለህ፣ ሕሊና ካለህ እንደ ኳስ መንከባለል እንዴት ይቻልሃል?
ነጋሶ ቢያንስ ከመሰናበታቸው በፊት መለስን “መንግስቱ መንግስቱን ሸተትከኝ” ማለታቸው የሰሩትን ስህተት ማረሚያ ሲሆናቸው ገነት ዘውዴን ግን ማስለቀሱን ተጽፎ አነበብን። እንደ ሰማነው ገነትን ያንሰቀሰቃቸው ላቶ መለስ ያላቸውን ፍቅር ለመግለጥ ብቻ ሳይሆን የነጋሶን ወንበር ይመኙ ስለነበር ነው። “ፕሬዚዳንት ገነት ዘውዴ” ምናምን እያሉ እራስ ለማታለል ማለት ነው።
ነጋሶ ፕሬዚዳንት ሲሆኑ ለመጀመሪያ ግዜ በኢትዮጵያ ታሪክ ስልጣን በሰላማዊ መንገድ በህዝብ ለተመረጠ ሰው ሲሰጥ በአይኔ በብረቷ አየሁ ብለው የድንቢጥ ማስክርነት ሰጥተው የነበሩት ገነት ዘውዴ፣ ለመለስ ምን አስለቀሳቸው ብለን መመራመር አያስፈልገንም። ነገሩ “ሆድ ሲውቅ…” እንደሚባለው መሆኑ ነው። ግን ያዞ እንባቸውም ከንቱ ቀረ። የወይዘሮ ገነት ዘውዴም ጌታ በዚያው አሸለቡ፣ እኛም ታዝበናቸው ቀረን። ምስኪን!
ነጋሶ ሲሰናበቱ ያተንኮለኛ አንባገነን ጥያቄ የማይጠይቅና አሻንጉሊትነቱን ሙሉ በሙሉ የሚቀበል ሰው አፈላልገው መቶ አለቃ ግርማን ፕሬዝዳንት ብለው ሰየሙ። ጋሽ ግርማ መቼም ድሮም ወስላታ እንደነብሩ አብረዋቸው የሰሩ ሁሉ የሚመሰክሩት ጉዳይ ነው። ህሊናቸው አይወቅሳቸውም። ይኸው እስካሁን አልጋ ላይ ሆነው፣ በዊል ቼይር እየተገፉ የህወሃቶች ላንቲካ እንደሆኑ መሞቻቸው ተቃርቧል። መቶ አለቃ ግርማ ወደ መቃብራቸው በህወሃቶች ሰረገላ ታጅበው ሲጋዙ ዶ/ር ነጋሶ የኢትዮጵያን ህዝብ ይቅርታ ጠይቀው ለህዝባችን አንድነትና ነጻነት እየታገሉ ይገኛሉ። ከጥፋቱ የሚማር ሁሉ ታላቅ ሰው ነው።
ሃይሌ ሆይ፣ ያንተ ዋናው ጉብዝና እሩጫ ነው። እንኳን አጸያፊውንና የሚከረፋውን የህወሃቶች የዘር ፖለቲካ መፈትፈት ይቅርና ሽምግልናም አልሆነልህ። ታስታውስ እንደሁ አቶ መለስ በግፍ ያሰሯቸውን አገር ወዳዶች ለማስፈታት ከነፕሮፌሰር ኤፍሬም ጋር
3
ሆነህ ያደረከው ጥረት መልካም ቢሆንም ምንም ያልበደሉ ንጽሃን ዜጎች ስንት ግፍና ጭፍጨፋ የፈጸሙትን መለስ ዜናዊን ይቅርታ እንዲጠይቁ ተደርጓል። ይሄ ደግሞ በታሪክ ያስወቅሳል።
በርግጥ ህወሃቶች ምን ቃል እንደገቡልህ አላውቅም። ይሁንና እንኳን ፕሬዚዳንትነት ጠቅላይ ሚኒስትነት ፈጽሞ አይመጥንህም። ጠቅላይ ሚኒስቴር ስል ጋሼ ሃይለማሪያም ትዝ አሉኝ። እኚህ ግለሰብ ገና አርባ ምንጭ ሲሰሩ ጀምሮ የሚታወቁበት አንድ መለያቸው ለህወሃቶ ጭራ መቁላት ነበር። ቀስ በቀስ ወደ ባለራዩ መሪ ቢሮ ጠጋ ሲሉም ስራቸው ከጭራ መቁላት ወደ ምንጣፍ አንጣፊነት ከፍ እንዳለ የሚውቋቸው ሁሉ የሚናገሩት ጉዳይ ነው።
ዛሬ በህወህት ጄኔራሎችና አማካሪዎች ታጅበው የመሪነት ስልጣን ሳይሆን የአሻንጉሊትነት ሚና በመጫወት ላይ ይገኛሉ። እኚህ ሰው የሌለና ያልነበረ ራእይ እጠብቃለሁ ብለው ደፋ ቀና ሲሉ በቁሙ የሞተው “መሪ” የሚል ቅጽል ወጥቶላቸው ተከብረው ሳይሆን የህወሃቶች ላንቲካና መጫውቻ ሆነው ሲሽከረከሩ ይውላሉ። ሰው ለህሊናው ማደርን ትቶ ሆድ ለመሙላት ብቻ ከኖረ የሚያዳምጠው ህሊናው የሚናገርውን እውነት ሳይሆን የሆዱን ፍላጎት ብቻ ነው። ጋሽ ሃይለማሪያም ህሊናቸውን አፍነው ሆዳቸውን እያዳመጡ መኖራቸው የሚያስከብራቸው ሳይሆን ለዘላለም የሚያስንቃቸው የታሪክ እውነታ ነው።
ውድ ሃይሌ፣ ሌላው ምኞትህ ደግሞ ፓርላማ ገብቶ ህግ ማውጣት ነው። ለመሆኑ ይሄ የህወሃቶች አዳራሽ ከመቼ ወዲህ ነው ለሃገርና ለወገን የሚጠቅም ስራ ሰርቶ የሚያውቀው። ወያኔዎች ዴሞክራሲ አመጣን ብለው ሁሉን ነገር ሙሉ በሙሉ እንደፈለጋቸው ተቆጣጥረው፣ ህዝብ እያስለቀሱ ፣ እያፈኑ፣ እየገደሉ፣ እያሰቃዩና እየዘረፉ ሲኖሩ ለመሆኑ መቼ ነው ፓርላማ ተብዬው የህዝብ ብሶት ተወያይቶ የሚያውቀው? የትኛውን መብት ነው ያስጠበቀው?የትኛውን ህግ ነው ያስከበረው? እኛ እስከምናውቀው ፓርላማ ማለት የህወሃቶች የቧልት አዳራሽ ነው። ቧልት ካማረህ፣ ለህወሃቶች ጭራ እየቆላህ፣ እያጨበጨብክ መኖር ካማረህ ወደ አዳርሹ ግባና የሚሉህን ሁሉ አድርግ። እኔ ግን ኪሳራ እንጂ ትርፍ እንደማታገኝ ከወዲሁ ልነግርህ እወዳለሁ።
እንደሰማሁት ከሆነ የሙስና እናት በመባል የሚታወቁት አዜብ መስፍን ከፓርላማ አባልነታቸው፣ ከኤፈርት ቁንጮነታቸው በተጨማሪ የአዲስ አበባ ከንቲባና የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት መሆን ይፈልጋሉ። አዜብ ከባላቸው ሞት በሁዋላ ፍላጎታቸውም በጣም እንደጨመረ እንደውም የመለስን እራእይ አስጠባቂ እኔ ነኝ ማለታቸው ትክክል ነው። በዘር ላይ ተመስርቶ የኢትዮጵያን ህዝብ ደም እየመጠጠ ያለው ኤፈርት ባለቤቶ ጋር መወዳደር በፖለቲካው ብቻ ሳይሆን በንግዱም ዘርፍ ብዙ ኪሳራ ስለሚያስከትልብህ ጠንቀቅ ብትል ይሻልሃል። ፕሬዚዳንትነቱንም ሆነ ፓርላማውን ለነአዜብ ተውላቸው። የነሱ የፍርድ ቀን እሩቅ አይደለም…
አንተም የኢትዮጵያን ህዝብ ማገልገል ከፈለክ ህዝባችን ከህወሃቶች የአፓርታይድ አገዛዝ ነጻ ለመውጣት የሚያደርገውን ትግል በሙሉ ልብህ ደግፍ። ትንሽም ብትሆን መሰዋእትነትና ዋጋ ክፈል። ፓርላማም ሆነ ቤተምንግስት ገብተህ የህወሃቶች ጉልቻ አትሁን።
ለማንኛውም የኔን ምክር ተውና የባለቤትህን የአለምዬን ምክር ስማ። ሴት መቼም ሁል ጊዜም ብልህ ነችና፣ አለም አያዋጣህም ብልሃለች። “ጨው ለራስህ ብትል…” ነው ነገሩ።
እኔ በበኩሌ የምመኘው በአገሬ እንደማንም ተራ ዜጋ ተከብሬ የነጻነት አየር እየተነፈስኩ መኖር ብቻ ነው። ከቤተ መንግስት ይልቅ የእናቴ ደሳሳ ጎጆ ትናፍቀኛለች።
ነጻነታችን ሲታወጅ ቤተመንግስት ሳይሆን አዲስ አበባ መንገድ ላይ እንደምንገናኝ ተስፋ አደርጋለሁ።የሰው ምክር ብትሰማ መልካም፣ ካልሰማህ ግን አንተንም እንደ አቶ መለስ በአደባባይ ካገኘሁህ ቀልብህን ገፍፌ….በማለት በፈገግታና በደስታ አጭሯን ጦማሬን አጠቃልላለሁ። …ለአለምዬ ልባዊ ሰላምታዬን አድርስልኝ። ያንን ቱጃር ግን ካገኘኸው እንደማለቀው ንገርልኝ!
ለማንኛውም መልካም እድል ለሁላችን!

ተጨማሪ ያንብቡ:  በለው! ቄንጠኛ ዳንስ በዕንባ ሲደንስ

20 Comments

  1. What’s wrong with this guy,

    This is not patriotic, why ? any one has the right to support any party he wanted. Please Abebe, you discredit your self trying to convince others beyond their will. Haile has got the right to support any one, hasn’t he ?
    Amazing, how people are living with below average thinking mind. Obang is a real hero, he is working for the unity of Ethiopia, promoting peace and tranquility with out any hidden agendas, but you are promoting hate, aren’t you ? Please act like as educated person. I’m sorry.

    • @Hulem: Where did Abebe talk about hate? The problem with you supporters of the dead legacy of the dead Meles is that if people do not support your idea, you get mad and don’t know what you say.

      Abebe is advising Haile, a good runner with strong legs but childish minded poor person to notice before being a child puppet of the racist Woyane junta.

      Abeeeeee LOveeeeeee YOuuuuuuuuu.

      Long live EEETTTHHHIIIOOOPPPIIIAAA!!!!!!

  2. Thank you Abe. Even though it is in Amharic I don’t think he understand what you are trying to tell him until he fulfill his dream and be ashamed of, he is very greedy. Let him try his best and will pay it back there is no jock with Woyane the murder they will eat him live.

  3. Great piece. Haile the Fool should read this piece several times. Yes, this must be kept for the record. Haile has climbed the ladder of fame easily through hard work and our support. He will god down if he cannot accept this advice. It takes months to get people’s support, but it takes the people only a second to hate someone. Haile, our collective advice is to stay away.

  4. Bunch of Dogs always Barking(targeting) on individuals, you will last rest of your life like this, you don’t have any qualify to insult or consult Haile gebreselassie he is all time legend he knows what he do, who are you people? bunch of losers, piss of shit. Long live Haile.

    Brain cancer neftegnoch – perish in hell

  5. Bunch of dogs always targeting individuals, you will last rest of your time like this, you don’t qualify to insult or consult Haile coz’ he is all time legend he knows what he do, who are you people ? losers, piss of shit. Long live Haile.

    Brain cancer = neftegna —> perish in hell

  6. Thanks abe you are my hero. hope he will red this letter and do the right thing. If haile do not change and foll with wayne.

  7. Haile g sellasie should learn from Negasso Gidada and all the others who have served as woyane lap dogs in this and other positions.

    Girma w giorgis’s main job is to drink coffee with invited guests of TPLF and to shake hands with them when the guests leave.
    Girma’s job is to eat and drink choice food and drinks with every guest that come to do business with TPLF POLITBUREAU. He is not even allowed to sit in a meeting with these guests.

    So Girma w giorgis is basically living just to fill his bell and to get a servant to push him around in his wheel chair.

    Haile g sellasie has enough money, he is not there to fill his belly, but for fame. He like to be famous. But I am afraid this is the wrong way to seek fame.
    Shaking hands with people wont make anybody famous.

    The reason why the woyane want Haile in this position is clear. Haile is already a famous athlete and will add credibility to the fascist TPLF if he takes up this post.The woyane are desperately trying to lure people into their circle by bribing them with money, corrupting them, and giving them positions which are meaningless.

    Haile g sellassie cannot do anything different from Negasso or Girma w giorgis. He will be used as a pawn and instead of gaining he will lose everything that he got through hard work and discipline.

    HAILE, please listen. woyane fascists are murderous, corrupt, hateful, and divisive. The woyane are known more for their destructive policy by inciting violence and murder on ethnic, tribal and relegious lines. The system the woyane have created is a repressive system that does not allow people to freely express themselves, to excercise their democratic rights. there is no justice and no freedom.
    Haile g sellassie can not do anything to change this set up. SO DO NOT BE A LOSER. YOU ARE KNOWN TO BE A WINNER.
    COLLABORATING WITH THE CORRUPT, FASCIST WOYANE WILL MAKE YOU ONLY A LOSER. NO ONE IS A LOSER WITH THE DIVISIVE , HATEFUL FASCIST WOYANE.

  8. ABEBE GELEB, ante menem moral yelehem HAILEN G/S yemenager
    HAILE G/S..ye Ethiopia gegena newu, ante gene fesam nehe.
    ante na ESAT,TAMAGE BEYEN..be JUWAR Gorade..angetachene letasemetun tesemametachuwal leboch.
    Hail G/S..ETHIOPIA WUSTE PRESIDENT yemehon mebet alewu. ante ena anten yemeselachu gen yememeret ena yememeret mebet yelachum.ezawu America hunachu medere feri hula atelefelefu., jegena yalewu be hageru be mederu laye newu….Hail gegena newu..,president le mehon be yaseb mebetu newu…ETHIOPIAN PPL WE DON’T NEED YOUR ADVICE, TOXIC DAISPORA TOXIC DAISPOPRA .TOXIC

  9. Abebe:

    Doesn’t people have the right to support any organization they want ? For you to say that Haile does not have to run for office is absurd. Please mind your own business and stop for dictating what others may or may not have to do.

    By the way how do you know that Haile may run as a member of EPRDF ? What if he runs under UDJ or Semayawi ? You see …it is not good to rush and blame others ….. Talking about freedom is one thing; working for freedom is something else. had you valued freedom and democracy, you have have respected the freedom of Haile.

  10. Abebe gelebawu…arefe kuch beleh ke ESAT yetureta birr bela, anten mane mekari arehehe..tule tula.

  11. Thanks Abebe our hero who stood bravely in the face of the fascist tribalist minority Tigrean ethnic apartheid architecture Meles and his enablers western hypocrites and for being the voice for voiceless. Thanks for shutting the liar tyrant for good and for send him to hell by ringing the freedom bell “we want freedom”. Also this Article is a timely advise for Haile who was licking the Weyanne’s dirty smelly ass for a while. First it is an insult for Ethiopians to suggest a runner for president as there no qualified educated, nationalist and elected by the people leader to bring himself as a candidate. Second all Ethiopians are disappointed and disgusted by Haile’s drama when the ethnic apartheid fascist tyrant Meles died and I believe Haile is an opportunistic selfish individual who has no care for the suffering of the majority Ethiopian people under the Tigrean minority ethnic apartheid system!

  12. Haile wanted to participate in politics to serve his nation. He has not yet disclosed his agenda and political vision. This is his right, no one can deprive him of. We need to encourage such Ethiopians to come to politics to contribute towards democratizing us and our country. I remember what Professor Mesfin said when was asked why now (to come to politics). He said that we (those who have the caliber, the potential and the knowhow) all are running away from politics, thus the guys from Tgray jungle came with jungle made rules and sieze political power. Now now are under “AGEZAZ” being punshed by TPLF made vision. His his own plans. Let us wait and see it may educate. There is no unque way of emancipating ourselves. I wish him good luck! I want him to stay with true colour. A jenuine Ethiopian.

  13. you are not my hero after I watched TG television.sorry for that.Please zehabesha why dont you post my comment?

Comments are closed.

Share