(ሰበር ዜና) ቋሚ ሲኖዶሱ ፓትርያርኩ አስተዳደር ነክ ውሳኔዎችን ብቻቸውን እንዳይሰጡ የውሳኔ ሃሳብ አቀረበ

July 17, 2013

የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ተማሪዎች በተቃውሞ ላይ
(ሰበር ዜና) ቋሚ ሲኖዶሱ ፓትርያርኩ አስተዳደር ነክ ውሳኔዎችን ብቻቸውን እንዳይሰጡ የውሳኔ ሃሳብ አቀረበ 1
(ዘ-ሐበሻ) ቋሚ ሲኖዶሱ ሳይሰበሰብ፣ የተማሪዎቹ ጥያቄ በአግባቡ ሳይመለስና ሳይጠና ከአቡነ ጢሞጢዎስ ጋር ባላቸው ጥብቅ ወዳጅነት የተነሳ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ እስከ መስከረም ድረስ እንዲዘጋ ፓትርያርኩ አቡነ ማቲያስ ወስነዋል በሚል ቋሚው ቅዱስ ሲኖዶስ ተቃውሞውን ማሰማቱን ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ አመለከተ። ከአዲስ አበባ ለዘ-ሐበሻ ሾልከው የመጡት የቤተክህነት መረጃዎች እንዳመለከቱት የቋሚው ቅዱስ ሲኖዶስ አባላት አስቸኳይ ጉባኤ እንዲጠራ አድርገዋል።
ጉባኤው መቼ እንደሚደረግ የዘ-ሐበሻ የቤተክህነት ምንጮች ያልደረሱበት ቢሆኖም በቅርብ ቀናት ውስጥ እንደሚደረግ ግን ያላቸውን እምነት ገልጸዋል። የቋሚ ቅዱስ ሲኖዶሱ አባላት ባወጡት የውሳኔ ሃሳብ መሰረት ፓትርያርኩ ቡራኬ ከመስጠት በቀርቭ አስተዳደራዊ የሆኑ ውሳኔዎችን ብቻቸውን እንዳይሰጡ ይከለክላል። ይህ አዲስ የውሳኔ ሃሳብ እንደሚለው ፓትርያርኩ አስተዳደራዊ ውሳኔዎችን ሲሰጡ በቅድሚያ ከቋሚው ቅዱስ ሲኖዶስ ጋር እንዲነጋገሩበትና በጋራ እንዲወሰን ያዛል። ይህ ፓትራይርኩ በአስተዳደራዊ ውሳኔዎች ላይ ስህተት እንዳይፈጽሙ ወይም የሚደርስባቸውን ወቀሳም ይቀንሳል በሚል የቀረበው የውሳኔ ሃሳብ በተጠራው ጉባኤ ላይ ከጸደቀ ሕግ ሆኖ እንደሚያገለግል የዘ-ሀበሻ የቤተክህነት ምንጮች አጋልጠዋል።
በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ የተነሳው የተማሪዎች ተቃውሞ እስካሁን እልባት አላገኘም። ዘ-ሐበሻ አሁንም ጉዳዩን ተከታትላ መረጃውን ለሕዝብ ታደርሳለች።

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop