ፖሊስ ማሰሩን የአንድነት አባላትም ወረቀት መበተኑን ገፍተውበታል (ዛሬ የታሰሩት 4 ደረሱ)

July 16, 2013

(ሰበር ዜና ከፍኖተ ነፃነት) ዛሬ ሐምሌ 9, 2005 ዓ.ም የታሰሩት አባላት 4 ደርሰዋል፡፡ ኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ የታሰሩ 3 የአንድነት አባላትን ለማስፈታት ወደ ስፍራው የሄደውን የአዲስ አበባ ዞን ስራ አስፈፃሚ የሆነው አዲሱ ካሳሁንን ከታሳሪዎቹ ጋር ቀላቅለውታል፡፡
ከአንድነት አዲስ አበባ ዞን ለፍኖተ ነፃነት የደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው ዛሬ የተሰማሩት አባላት በተለያዩ የከተማዋ ክፍሎች በተሳካ ሁኔታ ወረቀት የመበተን ተልዕኳቸውን በአግባቡ ተወጥተዋል፡፡ በትላንትናው እለት 42 የአንድነት አባላትና ለአንዱ ታሳሪ ዋስ ለመሆን የሄደ ግለሰብ መታሰራቸው አይዘነጋም፡:
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የፀረሽብር ህጉ እንዲሻርና በሌላ እንዲቀየር እያሰባሰበ ስለሚገኘው ፊርማ የሚያብራራ በራሪ ወረቀት በመበተን ላይ የነበሩት ባይሳ ደርሳ፣ አለማየሁ በቀለ፣ ግርማ ሹቤ የተባሉትን የአንድነት አባላት ዛሬ ሐምሌ 9 ቀን 2005 ዓ.ም በፖሊስ ታስረዋል፡፡ የአንድነት ፓርቲ የአዲስ አበባ ዞን ለፍኖተ ነፃነት እንዳስታወቀው በዛሬው ዕለት ሁለት መቶ የሚሆኑ የፓርቲው አባላት በተለያዩ የአዲስ አበባ የክፍሎች በራሪወረቀቶችን በመበተን ላይ ናቸው፡፡

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop