የኦርቶዶክስ ቤት ክርስቲያንን አንድ ሊያደርግ የሚችል የመፍትሄ ሃሳብ !

ግርማ  ካሳ
muziky68@yahoo.com
የካቲት 12 2015 ዓ.ም

«በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ! 

የአቡነ  ጳዉሎስን ሕልፈት ተከትሎ፣  በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ዉስጥ የተፈጠረዉን መከፋፈል ለማስቀረት፣ በመንፈሳዊ አባቶች መካከል፣ የሰላምና የእርቅ ዉይይቶች ተደርገዋል። ለሃያ አመታት የዘለቀዉ፣ ይህ በቤተ ክርስቲያን ላይ የወረደው የመከፋፈል እርግማን ተወግዶ፣  ቤተ ክርስቲያኒቷ  አንድ ሆና፣  «ሂዱና አሕዛብን እያስተማራችሁ፣ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅድስ ስም እያጠመቃችሁ፣ ደቀ መዛሙርት አድርጓቸዉ» የሚለዉና  በመድሃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ የተሰጠዉ፣ ታላቅ ተልእኮን መፈጸም ትችል ዘንድ፣ ሕዝበ ክርስቲያኑ በየአብያተ ከርስቲያናቱ፣ በየጸሎት ቤቱ ፣ በየገዳማቱ ሲጾምና ሲጸል ነበር።

ነገር ግን ከተጠበቀዉና ከተገመተዉ ዉጭ አስደንጋጭና አሳዛኝ መግለጫዎችን አነበብን። የክርስቶስ መድሃኔአለም ስም ተሰደበ። የዲያብሎስ ስም ገነነ። የትህትሃ የፍቅር እራስን የማዋረድ ክርስቲያናዊ መንፈስ ጠፋ። የእልህ የስደብ የመወጋገዛና የትእቢት መንፈስ ሰፈነ።

በአገር ደረጃ ካያን ፣ የከተማ፣   የክልል ፣ የፌደራል መንግስት  ሕጎች ይኖራሉ። ነገር ግን ከህጎች ሁሉ በላይ የሆነ ሕገ-መንግስት የሚባል ሕግ አለ። ፈረንጆች “The Supreme Law of the Land” ይሉታል።

ቤተ ክርስቲያንም የምትተዳደርበት ሕገ ደንብ ወይንም ቀኖና አላት። ካህናት ፣ ገዳማት፣ የሰንበት አስተማሪዎች ወዘተረፈ የሚታዳደሩበት ስርዓት/ሕግ/ቀኖና  አለ። እነዚህ የቤተ ክርስቲያን ሕጎችና ቀኖናዎች የቤተ ክርስቲያኒቱ ዋና መመሪያ የሆነዉን፣ የመድሃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል የሚያግዙ እንጂ፣  የሚተኩ አይደለም። ወንጌል ከሁሉም በላይ ነዉ። ለዚህም ነዉ በቅዳሴ ወቅት ወንጌልን ቄሱ በሚያነቡበት ወቅት፣ ምእመኑ በአክብሮትና በፍርሃት ቆሞ የሚያዳምጠው።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ  ቤተ ክርስቲያን አባቶችን እያጨቃጨቀ ያለ አንድ ጉዳይ ቢኖር፣  በቤተ ክርስቲያኒቷ የቀኖና መጽሃፍ የተጠቀሱ፣ ፓትሪያርክ እንዴት እንደሚሾምና እንደሚተካካ የሚገልጹ አንዳንድ አንቀጾች ናቸዉ። በዶክትሪን ወይንም በሃይማኖት ጉዳዮች አልተለያዩም። በአስተምህሮ አልተለያዩም። ልዩነታቸው፣ ቅንነትና ትህትና የተሞላ ልብ ካለ፣ በቀላሉ ሊፈታ የሚችል፣   የአሰራርና ማን መሪ መሆን አለበት የሚለዉ ላይ ነዉ።

አራተኛዉ የቤተ ክርስቲያኒቷ ፓትሪያርክ በሕይወት እያሉ አምስተኛ ፓትሪያርክ ይሾማሉ። «አምስተኛዉ ፓትሪያርክ የተሾሙት አራተኛዉ ፓትሪያርክ በፍቃዳቸው ሃላፊነታቸዉን ስለለቀቁ ነዉ» ያላሉ አንዳንዶች። ሌሎች ደግሞ «አይደለም ፤ በአቶ ታምራት ላይኔ ተገደው ነዉ» ሲሉ በፓትሪያርኩ ላይ ተደረገ የሚሉትን  ግፍ በምሬት ይገልጻሉ። ይሄ እንግዲህ ከሃያ አመት በፊት የሆነ ነገር ነዉ።  ጠባሳዉ ግን ለሃያ አመታት ይኸዉ በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ ጉዳት አደረሰ። ቤተ ክርስቲያኒቷ ተከፈለች። ለሃያ አመታት ጠብ ነገሰ። ተፋቅረን ተያይዘን በአንድ ላይ ወንጌልን ማስፋፋት የሚገባን ክርስቲያኖችን፣ ከፋፍሎና አጣልቶ ሆድና ጀርባ አደረገን።

እንግዲህ አስቡት፣ የመጽሃፍት ሁሉ የበላይ፣ የሕጎች ሁሉ የበላይ የሆነዉ ፣ ወንጌልን ያካተተዉ መጽሃፍ ቅዱስ ነዉ።  መጽሃፍ ቅዱስ የሚያዘው ፍቅርን፣ ይቅር መባባልን፣ አንድነትን፣ ትህትና የመሳሰሉትን ነዉ። የቀኖናዎች ሁሉ የበላይ ከሆነዉ፣ ከማያልፈዉና ከማያረጀዉ ሕያዉ የእግዚአብሄር ቃል ዉስጥ ፣ «እርስ በርሳችሁ ብትዋደዱ የኔ ደቀ መዛሙርት መሆናችሁን ሌሎች ያዉቃሉ»፣ « እራስህን ከሌላ የተሻለ አድርገህ አትቁጠር» ፣ «አንተ የሌላዉን ጉዳፍ ለማወጣት የምትቸኩል በአይን ያለዉ ያለዉን ትልቅ ምሰሶ መጀመሪያ ተመልከት» ፣  ‹‹በመጀመሪያ መባህን በመሰዊያው ላይ ትተህ አስቀድመህ ከወንድምህ ጋር ታረቅ››፣ «ማንም ከነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን የሚያሰናክል ፣ ወፍጮ ባንገቱ ታስሮ ባህር ዉስጥ ቢወረወር ይቀለዋል»፣ «ሌላዉን የሚያሰናክል ከሆነ ስጋ ባልበላ ለዘላለም ልቀር»፣ «እኔ መምህር ና ጌታ ሆኜ ይሄን ካደረኩ ( የደቀ መዛሙርቱን እግር ማጠቡ) እናንተም እንዲሁ አደርጉ» የመሳሰሉትን  ትእዛዛት እናነባለን።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የድንበሩና የዐባይ ጉዳይ!! (አንተነህ ሽፈራው)

የቤተ ክርስቲያን አባቶች በአንድ በኩል ለክርስቲያናዊ ሕግና ቀኖ ቆመናል  እያልን፣  በሌላ በኩል ከቤተ ከርስቲያን ሕግና ቀኖና በላይ የሆነዉን የጌታ ክርስቶስን ትእዛዝ ወደ ጎን እያደረገን፣  ያለ ይመስለኛል። ቀኖና፣  ወንጌልንም መደገፍ እንጂ ከወንጌል በተቃራኒ መቆም እንደሌለበት የዘነጋን ይመስለኛል። ዋናዉን ረስተን ትንሹ ነገር ላይ ስናከር ነው የሚታየዉ።

እንግዲህ «ንስሐ እንግባ ። ክርስትናችንን ፣ የክርስቶስ ተከታይና አገልጋይነታችንን፣ በምንለብሰው ካባ  ሳይሆን በስራችን አናሳይ» እላለሁኝ። ከወንድሞቻችን ጋር መስማማት አቅቶን፣ ይቅር መባባል ከብዶን፣ «እኔ ነኝ ፓትሪያርክ መሆን ያለብኝ …እርሱ ነዉ መሆን ያለበት ..» እየታባባልን፣ በእልህ  መንፈስ ተሞልተን፣ በአኮቴተ ቁርባን ወቅት ስጋ ወደሙን በእጃቸችን ለመያዝ መቆማችን  መቅሰፍት ነዉ»  እላለሁ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ቤተ ክርስቲያን ጥንታዊት ቤተ ክርስቲያን ናት።  እንደ እዉነቱ ከሆነ ፣ ከኛ በኋላ ክርስትናን በተቀበሉ አገሮች የሚኖሩ ዜጎች፣ እምነት የሌላቸውን ክርስቲያን እያደረጉ ባለበት ወቅት፣ የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን፣ በምስራቅ አፍሪካ ወንጌልን ለማሰራጨት የበለጠ መነሳት አይገባትም ነበርን ? በሚሊዮን የሚቆጠሩ እራሳቸውን ኦርቶዶክ ክርስቲያን ነን  የሚሉ፣  ነገር ግን የስላሴንና የስጋዌን ሚስጥራትን እንኳን በደንብ የማያዉቁ አሉ።  ብዙ የኦርቶዶስክ ልጆች በሃሺሽ፣ በጫት፣ በተለያዩ ከምእራባዉያን አገራት በመጡ ጸረ-እምነት ተግባራት የተጠመዱ ፣ በስም እንጂ ከክርስትና ጋር በተግባር የማይተዋወቁ ናቸው። አብያተ ከርስቲያናትን ከሚያዘወትሩት ይልቅ፣  የዳንኪራ፣ የጫትና የካቲካላ  ቤቶችን የሚያዘወትሩ በጣም ይበዛሉ።

ታዲያ  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ቤተ ክርስቲያን፣ በሯን ለመንፈስ ቅዱስ  ከፍታ፣ እራሷን ከመንፈሳዊ ባርነት አውጥታ፣ የማያምኑ  አሕዛብን  እንዲያምኑ ማድረጉን ለጊዜው እንተወዉና፣ ኦርቶዶክስ ነን የሚሉትን  እንኳ በቃለ እግዚአብሄርና በእምነት ማጠንከርና ማሳደግ አልነበረባትምን ?  የኦርቶዶክስ አማኞች ፣ ወንጌልን አልፎ አልፎ ቅዳሴ ሲመጡ በሚሰሙት ብቻ ሳይወሰኑ፣  ሌት ተቀን የሚያነቡትና የሕይወታቸው መመሪያ የሚያደርጉት፣ ሳይፈሩም በአደባባይ  የሚያወጁት መሆንስ አይገባምን ?

ነገር ግን መንፈሳዊ አባቶች፣ እረኝነታችንን ረስተን፣  መንጋዉን ለተኩላ ለመስጠት እየተዘጋጀን ያለ ይመስለኛል። ጥል ባለበት እግዚአብሄር የለም። «የትእቢተኞችን ቀስት ይሰብራል፣ ለትሁታን ግን ጸጋን ይሰጣል» እንዳለችዉ እናታችን ቅድስት ማርያም፣ እግዚአብሄር ትእቢትን ይጸየፋል። ትእቢት ባለበት ቦታ እግዚአብሄር የለም። በመሆኑም  የኦርቶዶስክ አባቶች እርቅ መመስረት ካልቻልን፣  ከእግዚአብሄር ክብር ይልቅ የኛን ክብር ካስቀደምን፣ በግልጽ በስራችን የምንናገረዉ፣   እግዚአብሄር ከእኛ ጋር እንደሌለ ነዉ። እግዚአብሄር የሌለበት ቦታ ደግሞ እንዲሁ መቆዘም እንጂ በረከት የለም።

እስቲ ትንሽ ጠለቅ ልበልና፤ ሁለቱ የኦርቶዶክስ ሲኖዶሶች፣  ሊስማሙበት ካልቻሉበት ነጥቦች መካከል በዋናነት የሚጠቀሰውን ለማየት እንሞክር።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የ‹‹እናውቅልሃለን›› የፖሊቲካ ፍልስፍና ውጤት! ዮሴፍ ሙሉጌታ ባባ

ዉጭ አገር የሚገኘዉ ሲኖዶስ አራተኛው ፓትሪያርክ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው፣  የፓትሪያክነት ሃላፊነታቸዉን እንዲወጡ ይፈልጋል። አዲስ አበባ ያለው ሲኖዶስ ደግሞ «ለሃያ አመት የተሰራዉን ሥራ መቀልበስ ነዉ። አምስት ተብሎ ወደ አራት መሄድ አይቻልም» በሚል አራተኛዉ ፓትሪያርክ ተመልሰው አራተኛ ወይንም ስድስተኛ ሆኖ መቀጠላቸዉን ሊደግፉ አልቻሉም። ‹‹አራተኛው ፓትርያርክ ወደ አገራቸው ተመልሰው ደረጃቸውና ክብራቸው ተጠብቆ፣ የሚያስፈልጋቸው ሁሉ ተሟልቶላቸው በመረጡት ቦታ በፀሎት ተወስነው እንዲኖሩ፣ ነገሮቹም ሆነ በእሳቸው አንብሮተ ዕድ የተሾሙ ቀኖናውን በቀኖና አሻሽሎ ሐዋርያዊ ሥልጣናቸውን ሰጥቶ፣ ስማቸውን መልሶ በሀገረ ስብከት መድቦ ለማሠራት፣ ፈቃደኛ ነዉ» ሲል በአዲስ አበባ ያለዉ  ቅዱስ ሲኖዶስ የመጨረሻ አቋሙን ያሳዉቃል። አሜሪካ ያለዉ ሲኖዶስ መልስ በመስጠት «አቡነ መርቆሪዮስ ፓትሪያርክነታቸውን መቀጠል አለባቸው። የቤተ ክርስቲያኒቱ ቀኖና መጠበቅ አለበት» በሚል አቋሙን በድጋሚ የሚያጸና መግለጫ ያወጣል።

ከሁለቱም ወገኖች ላሉ አባቶች እንግዲህ የምለው ይሄን ነዉ። እግዚአብሄርን እንጂ ሰዉን አንፍራ። አላስፈላጊ መግለጫዎችን  ከመስጠት እንቆጠብ። አለመስማማት፣ ለጊዜዉ መጋጨት ያለ ነዉ። ሐዋርያዉ ጳዉሎስና በርናባስም አንድ ወቅት ተጋጭተዉ ነበር። እግዚአብሄር ለቁጣ የዘገየ በምህረቱ ግን ባለጠጋ የሆነ አምላክ ነዉ። «የልጁ የየሱስ ክርስቶስ ደም ከሐጢያት ሁሉ ያነጻል« ተብሎ እንደተጻፈ፣ ለሰራናቸው ሐጢያቶች እና ስህተቶች እግዚአብሄር ይቅር ይለናል። የትላንትናዉን  ትተን፣ ዛሬ መልካምን ነገር ለማድረግ እንዘጋጅ። ዛሬ እራሳችንን ለፍቃዱ እናስገዛ። ጆሮዎቻችን የጥላቻን እና የእልህ ወሬዎችን ከመስማት የተደፈኑ ይሁኑ። ሁላችንንም ሊያስማማ የሚችል መፍትሄ ማግኘት ይቻል ዘንድ እንመካከር፣ በጋራም አብረን እንጸልይ።

አዲስ አበባ ያለው ሲኖዶስ፣ ፓትሪያርክ የሚሆኑ እጩዎችን ተቀበሎ ስድስተኛዉን ፓትሪያርክ ለማስመረጥ ስራዎችን እየሰራ እንዳለ እያነበብን ነዉ።  በቅርቡም አዲሱ ፓትሪያርክ ማን እንደሚሆኑ እንሰማለን። ይሄ ደግሞ ለሃያ አመታት የነበረዉ  የቤተ ክርስቲያን መከፋፋልና እርግማን እንዲቀጥል ሊያደርገው አይገባም። የእርቁን ሂደት ይረዳ ዘንድ፣ የኦርቶዶክ ቤተ ክርስቲያንን አንድ የሚያደርግ፣  አንዳንድ ሃሳቦችን በትህትና ለማቅረብ እሞክራለሁ። እነዚህን ሃሳቦች ሳቀርብ ፣ አገር ቤት ያሉም ሆነ በአሜሪካ የሚገኙ አባቶች፣ ትንሽ ሊቆረቁራቸው ቢችልም ትኩረት ሰጠዉ ሃሳቤን ያስተናግዱታል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ።

  1. አዲስ አበባ ያሉም ሆነ በዉጭ የሚገኙ አባቶች፣ መግለጫዎችን  ከማዉጣት መቆጠብ ይኖርባቸዋል። መግለጫ ማዉጣት ማንነትን አይሳይም። መግለጫ ማዉጣት ክርስትናን አያሳይም። «በፍሪያችሁ ያውቋቹሃል» ተብሎ እንደተጻፈ ክርስትናችንን፣ የክርስቶስ አገልጋይነታችንን፣ የቤተ ክርስቲያን መሪነታችንን በስራችን ነዉ ማሳየት የሚኖርብን። በስራችን ክርስትና ማለት ምን ማለት እንደሆነ፣ አርዓያ በመሆን፣  ለምንመራው ምእመን ማስተማር አለብን።
  2. በአዲስ አበባ የሚገኘው ሲኖድስ፣ ስድስተኛዉን ፓትሪያርክ በቅርቡ ያሳዉቀናል። አዲሱ ፓትሪያርክ በዉጭ አገር ካለዉ ሲኖድ ጋር በመነጋገር፣ አንድነት የሚፈጠርበትን፣ በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ የወረደው እርግምን የሚገፈፍበትን ሁኔታ በቀዳሚነት ማመቻቻት ቀዳሚ ተግባራቸው ሊሆን ይገባል። «ከሁሉም በላይ መሆን የሚፈልግ የሁሉም አገልጋይ ይሁን»  እንዳለ ጌታችን ኢየሱስ ፣ ፓትሪያክነታቸዉ የከፍታ ቦታን ለማግኘት ሳይሆን፣ ለማገልገል፣ የተበተኑትን ለማሰባሰብ፣ የተሰበረዉን ለመጠገን መሆን አለበት።
  3. አቡነ መርቆርዮስ በእድሜ ባለጠጋ የሆኑ አባት ናቸዉ። በርሳቸው ምክንያት ክፍፍሉ መቀጠል የለበትም። ለሰላም ሲሉ ፣ ለቤተ ክርስቲያኒቷ አንድነት ሲሉ፣ ለእግዚአብሄር ክብር ሲሉ፣ እግር ማጠብ ይኖርባቸዋል። እርግጥ ነዉ በቆኖናዉ መሰረት ፓትሪያርክ ሳይሞት ፓትሪያርክ አይሾምም። ከዚህ በፊት ስህተቶች ተሰርተዉ ሊሆን ይችላል። ከዚህ በፊት በደል ተፈጽሞባቸዉ ሊሆን ይችላል። ነገር ግን አሁን ከዚያ አልፈዉ መሄድ ያለባቸው ይመስለኛል።  ይቅር ማለት መቻል ያለባቸው ይመስለኛል። ከሃላፊነታቸው በፍቃዳቸው ቢለቁና አዲስ ለተመረጡ ፓትሪያርክ እዉቅና ቢሰጡ፣ የዲያቢሎስን ሥራ ነበር የሚያፈርሱት። በመሸነፍም ያሸንፉ ነበር።
ተጨማሪ ያንብቡ:  ሱዳን መሬት ወረረች - ጌታቸው ኃይሌ

እዚህ ላይ በቅርቡ የካቶሊኩ ፖፕ ያደረጉትን መመልከት ሊጠቅም ይችላል። «ቤተ ክርስቲያኔን ለመምራት የአካል ጥንካሬ የለኝም። የኔ ፖፕ ሆኖ መቀጠል ጥሩ አይደለም። በኔ ምትክ ሌላ ሊሰራ የሚችል ፖፕ መመረጥ አለበት» ብለው፣  ለቤተ ክርስቲያን ጥቅም ሲሉ፣ ፖፕ ቤኔዲክት ከሃላፊነታቸው ሊነሱ ነዉ። አቡነ መርቆሪዮስም  እንደ የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያንን ጥቅም አስቀድመዉ፣ ቤተ ክርስቲያኒቷን አንድ ለማድረግ፣ የቤተ ክርስቲያኒቷን ቀኖና በጠበቀ መልኩ፣  ቁልፍ ሚና ይጫወታሉ ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ።

እንግዲህ እንደ ክርስቲያኖች ትልቅ መንፈሳዊ ዉጊያ ከፊታችን ይጠብቀናል። ጸረ-ወንጌል የሆነው ዲያብሎስ፣ በታሪክ ትልቅ ስራን የሰራች ቤተ ክርስቲያንን ለማዳከም እየጣረ ነዉ። በመሆኑም ሕዝበ  ክርስቲያን ሁሉ ከመቼውም በበለጠ አጥብቆ መጸለይና መጾም ይኖርበታል።  በወጡት፣ ጠቃሚ ያልሆኑ መግለጫዎች ተስፋ መቁረጥ የለብን። ክርስቲያን ተስፋ አይቆርጠም። ከንግስት አስቴር መማር አለብን። አማሌቃዊዉ ሃማ እሥራዔላዉያንን ለመጨረስ አዋጅ አሳወጀ። እነ አስቴር  ጾም ጸሎት አወጁ። በእግዚአብሄር ፊት አነቡ። አዋጅን የሚሽር ሌላ አዋጅ ታወጀ። ሃማ መርዶኪዮስን ለመስቀል ባዘጋጀው እንጨት ላይ ተሰቀለ። ሃሌሉያ።

እንደዚሁም እኛ በእምነት፣  በጾምና በጸሎት እግዚአብሄር  ፊት ከቀረብን፣  ተአምራት ማየት እንችላለን። ቤተ ከርስቲያንን ከመፈራረስ ልናድናት እንችላለን። አንድነቷን ማስጠበቅ እንችላለን። ከርግማን ወጥታ ፈረንጆች ከሚያደርጉት በላይ ለወንጌል መስፋፋት የተሰለፈች ልናደርጋት እንችላለን።

እዚህ ላይ አንድ ትልቅ ቁም ነገር አንርሳ። በቤተ ክርስቲያኒቷ ያሉትን ችግሮች በማባባስ፣ የፖለቲክ ትርፍ ለማግኘት የሚሞክሩ፣ ዲያብሎስ እራሱ እየተጠቀመባቸው  ያሉ ግለሰቦችና ድርጅቶች ይኖራሉ። በፖለቲካ እንቅስቃሴ ዉስጥ ገብቶ መሳተፍ የራሱ ቦታና ጥቅም ቢኖረዉም፣  በቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ግን፣  የእግዚአብሄር ሥራ የሚሰራው በፖለቲካ መድረክ አይደለም። የእግዚአብሄር ሥራ የሚሰራዉ እንደ ወገዛ፣ ስድብ፣ መግለጫ ማዉጣት በመሳሰሉ የፖለቲካ መሳሪያዎችን በመጠቀም አይደለም። የእግዚአብሄር ሥራ የሚሰራዉ በመንፈሱ ነዉ። በቤተ ክርስቲያን ዉስጥ ችግር የሚፈጥሩ ካህንም ሆነ ጳጳስ ካሉ፣ የሚበቀላቸው እራሱ እግዚአብሄር ነዉ። «ፍርድ የኔ ነዉ!» ይላልና የሰራዊት ጌታ እግዚአብሄር።

በመሆኑም የምናቀራርብ፣ የምናስታርቅ፣ ልዩነቶችን የምናጠብ፣ መግባባት ንግግርና መቀባበል እንዲኖር የምናበረታታ ፣ የተሳሳተን በጨዋነት የምንገስጽ፣ የወደቀን የምናነሳ፣ የሚያጠፋን ከጥፋታቸውዉ የምንመልስ እንሁን እንጂ፣ በእሳት ላይ ነዳጅ አናርከፍከፍ።

እግዚአብሄር ልቦናችንን ለፍቅሩ አይምሯችንን ለጥበቡ ይክፈትልን !

 

 

 

9 Comments

  1. Girma, you suggestions are dividing rather than uniting. You cannot fix one wrong by another wrong. You can fix a wrong or an injustice only by doing right or justice. The only way we can get out of the predicament the TPLF has put the EOTC is by restoring Abune Merkorios to his patriachate entrusted to him by the Almighty God. He was forcefully removed from his position by atheist TPLF ringleaders and thugs in flagrant violations of the cannon of the ETOC. This is not only a sin in spirituality but it is a crime in mundanity as well. Moreover, the issue is not only about Abune Merkorios but it is also more importantly about the cannon of the ETOC. The issue is about the church being an independent institution of faith in God or a subservient to the will of gun toting TPLF thugs and ringleaders. No one in his/her good conscience allow the violations of the cannon of the church. Appeasing the violators by allowing the current njustice to prevail would only serve as a receipe for more violations. By advocating for the prevalence of injustice, Girma has become the latest devil’s advocate. I advise him to serve the TPLF thugs in another capacity than delving in sin. Girma is trying to mislead, though in vain, by comparing apples with oranges. Pope Benedict XVI is resigning from papacy of his own freewill and, of course, the will of God. But Abune Merkorios has been forcefully removed from his God given position by gun toting atheist TPLF ringleaders and thugs.

    • @ haile melekot , let me ask you an honest question , do you have any evidence that supports abune merkorios forcefully removed from his post ? i think it is just a heresay , bring your evidence ? i tell you you have nothing , but why not the abune merkorios speaks about this issue instead of by interpraters , ? and if benedict resigned are you saying comparing orange with apple ? abune merkorios is getting old , if you really think , how long will serve the church ? over all your comment is just very biased in support of abune markarios , with no evidence but emotion . why the abun wants a top position ?

      • Fre, you may choose not to accept the plenty of evidence that are out there. You may just close your eyes and choose not to see but that does not mean that there is nothing out there to be seen. Among others let me just mention two of them. First, if hearing from Abune Merkorios is what you are waiting for to be convinced about his forceful removal, I have a good news for you. Abune Merkorios spoke just recently, on the eve of this year’s Ethiopian Christmas, that he had been removed forcefully from his position at the gun point by the atheist TPLF thugs. Second, according to wikileaks, the former seville of the TPLF, Tamrat Layne, divulged to a U.S. diplomat in Addis Ababa that he signed off on the order from his TPLF bosses to remove Abune Merkorios from his position forcefully. What more evidence do you want to see other than both the victim and the perpetuator testfying about the incident in the same words concurring 100% on the circumstances? The testimonies of both the victim and the perpetuators are exactly the same. What else do you want to see? Do not keep moving the goal post over and over again every time the evidence you asked for is presented to you just because you choose to remain unconvinced even in the face of such overwhelming evidence. Are you waiting for God to come down to the earth and talk to you to convince you? If you are a follower of the EOTC and know the cannon of the church, patriarchate is a lifelong annointment. It does not put any age limit. If you are blessed with a long life by the will of God, you may still serve in that capacity as long as you breathe even if you are 150 years old according to the cannon of the EOTC. What we go by is the cannon of the church, not by what makes or does not make sense to you or me. So your argument about age would not hold water as far as the cannon of the church is concerned. You may still choose to close your eyes not to see the overwhelming evidence but I hope you can now see who is driven by evidence and who is driven by emotion.

  2. The writer has always controversial ideas. Remembering at the times of Kinijit split.

    The problem in the church has started when the leftist have joined in the inner work of church administration. The church has started adopting those revolutionary words like “vote of confidence; petition, coroum, etc. ”

    My conclusion is church is infiltrated by leftists (revos)

  3. I am asking the site administrator:

    Why did you delete my comments?
    Was the writer angry and opposed to it?
    Why do you entertain a one sided opinion?

    Thanks.

  4. Girma kassa u used some good words to cover your woyane mission! We need the church to be united. Abune Merqoriows must take the patriarch position!

  5. Dear Girma Kassa
    Progress not compromise in the TRUTH of the church~ keeping the DIVINE ORDER OF THE CHURCH is required. Compromising our beliefes and the CANNON is not the right path for the true unity of the church. The solution is not men’s precepts or idea ( such as yours ) but the law of God’s church. Your idea rather the malicious political opinion contains a hidden agenda of supporting TPLF and lengthenning the life of the tigrians supermacy rule in Ethiopia. The root of the cancer in Ethiopia is the TPLF system and the inside SYNODOS being the right hand tool of the dictator rule of Ethiopia. In my humble desire , we need to cut out the cancer from its source- we need to free the orthodx church from the prison of TPLFites. This will happen only when the system is abolished unconditionally and completely. We should never allow our temporary challenges of the TPLF system to become excuses for giving up on God’s law of the church~ the CANNON. By the way, faithful servants never retire. They serve faithfully as long as they are alive. You can retire from your career, but you will never retire from serving God. Real servants are faithful to their call of God. Servants finish their tasks, fulfill their responsibities, keep their promises, and complete their committements. Listen, Girma, They do not leave a job half done, and they donot quit when they get discouraged. They are trustworthy and dependable. Abune Merqorios is counted on first by Almighty God and then by his children of the faith. He has the DIVINE vows to fulfil and committement to honor . May you please leave Abune Merqorio ALONE!
    Abune Merqorios is keeping his vows… whatever the cost will be for the Almighty God is with him always.
    May I close by the word of God~ ” A good name is rather to be chosen than great riches, and loving favour than silver and gold” (proverb 22: 1)
    LONG LIVE FOR THE TRUSTWORTHY SPIRITUAL FATHER~ ABUNE MERQORIOS AND ABA MELKATSEDIQ

  6. I did not be leave on the above option of the guy who wrote about Abune Merkoreyose . I think he never knows about the problem of the churchu. Who brought the problems of the church? I think Mr Kassa is the supporter of weyane. The best way of unity is eradicate the weyane regime from Ethiopia. Weyane divides the Church in two parts. The main reason is Ato Tamrat Layene.

Comments are closed.

Share