የዶ/ር መረራ የቡዳ ፖለቲካ እና መቀበል ያቃተው መራራ እውነት – ግርማ ሠይፉ ማሩ

ግርማ ሠይፉ ማሩ

girmaseifu32@yahoo.com; www.girmaseifu.blogspot.com

ዶክተር መረራ “የኢትዮጵያ የታሪክ  ፈተናዎች እና የሚጋጩ ሕልሞች” በሚል አዲስ መፅኃፍ አስነብቦናል፡፡ በአንድ ጋዜጣ ላይ የዶክተር መረራ ከዮኒቨርሲቲ መሰናበት ያመጣው አንድ በጎ ጎን መሆኑን አንብቤያሁ፡፡ እኔም በዚህ እስማማሀለሁ፡፡ ብዙ የሀገራችን ፖለቲካኞች ጋዜጠኛ መቅረፀ ድምፅ ይዞ በሚጠይቃቸው ጥያቄ መልስ ከመስጠት የዘለለ ብዕርና ወረቀት አገናኝተው የሚያምኑበትን የፖለቲካ መስመር እና በግላቸው ያላቸውን ምልከታ ማካፈል ይቸግራቸዋል፡፡ የዶክተር መረራ ከዚህ በፊትም በተመሳሳይ ለንባብ ያበቃው መፅኃፍ ጋር ይህን መፅኃፍ ሲጨመርበት ቢያንስ በፖለቲካ መስመሩ ላይ ግልፅ መረዳት እንዲኖረን ያደርጋል፡፡ ለዚህ ፅሁፍ መነሻ የሆነኝ ግን በዋነኝነት ዶክተር መረራ አውቆ የሚዘላቸው አንድነትን የሚመለከቱ ጉዳዮች ሲሆኑ እግረ መንገዴን ከመፅኃፉ የተረዳሁትን ለማካፈል ጭምር ነው፡፡

ዶክተር መረራ በእኔ መረዳት ዛሬም መኢሶን ነው፡፡ በተቻለው መጠን መኢሶን በመከላከል እና ዋናውን ጥፋት በደርግና ኢህአፓ ትከሻ ላይ ሲጭን ነው የሚታየው፡፡ መቀበል ያቃተው መራራው እውነት መኢሶን ከደርግ ጋር ተባብሮ የደርግን ጡንቻ ማፈርጠሙ ከዚያም ተከትሎ ለተፈጠረው ጥፋት ድርሻውን ማንሳት እንዳለበት በግልፅ ሊያሳየን አለመቻሉ ነው፡፡ ድርሻ መውሰድ ስል ጥፋትን አምኖ ይቅርታ መጠየቅ እና ለእርቅ ዝግጁ መሆን ማለቴ ነው፡፡ በእኔ የፖለቲካ እሳቤ ውስጥ ሂሳብ ማወራረድ የሚል የለም፡፡

ዶክተር መረራ አሁን ኢትዮጵያ የምንላትን ሀገር ቅርፅ ያሲያዙትን ምኒሊክን ጀግንነት በጥያቄ ምልክት ውስጥ በማስገባት እና ከሶማሊያ ጋር አብረው ሀገር ሲወጉ ነበር የሚባሉትን “ዋቆ ጉታን” ጀግና እያደረገ በአክራሪ ኦሮሞ ብሔርተኞች ድጋፍ የመሻት ፍላጎቱን በመፅሃፉ ውስጥ ታዝቢያለሁኝ፡፡ ዶክተር መረራ ወደ መሃል እንምጣ እያለ ጥግ ጥጉን የሚሄድ መሆኑን ማሳያም ጭምር ነው፡፡ እንደሚታወቀው የዶክተር መረራ አብረን እንስራ እስከ “ግንባር” ብቻ ነው፡፡

የዶክተር መረራ የቡዳ ፖለቲካ ብሂል በሁሉም ጉዳይ ችግሮችን ወደሌሎች ማላከክ ባለብን አባዜ ጥሩ ገላጭ ቢሆንም፤ የዚህ የቡዳ ፖለቲካ ሰለባ ዋነኛው ግን ዶክተር መረራ መሆኑ ብዙ ማሳያ ማቅረብ ይቻላል፡፡ በተለይ መድረክ የሚባለውን ስብስብ አንዴም እንኳን ለሚፈጠሩት ችግሮች ኃለፊነት የሚወሰድ አካል አድርጎ አያቀርበውም፡፡ ዶክተር መረራ በሚመራው ድርጅት ውስጥም ያለውን ችግር ለማየት እና ለማስተካከል አይፈልግም፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  የወልቃይት ጠገዴ መሬቱን እንጂ...! | ሳምሶን ኃይሌ

የዶክተር መረራ “የኢትዮጵያ የታሪክ ፈተናዎች እና የሚጋጩ ሕልሞቸ” የሚለው መፅኃፍ ይህች ሀገር ከፈታና የምትወጣው እና ህልሞች ቅዠት ሳይሆኑ አውን የሚሆኑት “የኦሮሞ ልኢቃን” እና “የአማራ ልሂቃን” የያዙትን ፅንፍ ሲተዉ እና መሃል መንገድ ላይ ሲገናኙ እንደሆነ ይገልፃል፡፡ እኔ በፍፁም ያልገባኝ “የአማራ ልሂቅን” የሚባለው ፍረጃ ነው፡፡ ኢትዮጵያዊ ብሄረተኝነት የሚያቀነቅኑት ለማለት ከሆነ ሌሎችም አማራ ያልሆኑ በዚህ ረድፍ ውስጥ ይገኛሉ፡፡ ወይም ደግሞ አማራ ማለት ኦሮሞ ያልሆነ ሁሉ ማለት እንደሆነ በግልፅ ሊነግረን ይገባ ነበር፡፡ ወጣም ወረደ እኔ በመሪነት ሁሉ የተሳተፍኩበትን አንድነት ፓርቲን በአማራ ልሂቀን የሚመራ ተብሎ ተፈርጇል፡፡ ስለዚህ ይህ መሰረታዊ ስህተት ሀገራችን ከፈተና እንድትወጣ የታዘዘላት የዶክተር መረራ መድሃኒት እንደማይሰራ የሚያመላክት ነው፡፡

ዶክተር መረራ የቡዳ ፖለቲካው ሰለባ መሆኑን በደንብ የሚያሳየው “ለአንድነት ሆዴ መቁረጥ የጀመረው፤ በ2205 ክረምት የድጋፍ ማሰባሰቢያ ስብሰባዎችን በአሜሪካ ለማካሄድ ተሰማምተን ከሄድን በኋላ እነ ግርማ ሠይፉ ሙሉ በሙሉ ባልገባኝ ምክንያት የጋራ እንቅስቃሴ እንዳናደርግ ባደረጉ ጊዜ ነበር፡፡ በጊዜው ለአንድነት መሪ ለነበረው ለዶ/ር ነጋሶም ምሬቴን ገልጨ ነበር፡፡ ምሬቴ ለዶ/ር ነጋሶም የገባው ይመስለኛል፡፡ ለማረም ግን አልቻለም፡፡….”  የሚል ክስ በገፅ 147 ላይ አስፍሮዋል፡፡ ተመሳሳይ ክስ በሌለሁበት በመድረክ ስብሰባ ላይ ሰሜን ጠርቶ እንዳቀረበ ሰምቻለሁ፡፡

በመጀመሪያ ደረጃ የድጋፍ ማሰባሰቢያ ስብሰባዎችን በአሜሪካ ለማካሄድ ተሰማምተን የሚለው አውነት አይደለም፡፡ እኔም እርሱም በግላችን አሜሪካ እንደምንሄድ ሲታወቅ ከተቻለ በጋራ ስብሰባ ብናደርግ የሚል ሃሳብ አንሰተን ሙከራ እንድናደርግ በሚል “አዲስ ቪው ሆቴል” ተገናኝተን ተነጋግረናል፡፡ ሙከራ ደግሞ ሊሳካም ላይሳከም ይቸላል፡፡ ይህን ዶክተር ነጋሶ ለአንድነት ድጋፍ ሰጪዎች ገልፀውላቸዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን ዶክተረ መረራ ዘወትር እንደሚያደርገው “የኦሮሞ ኮሚኒቲ” ለብቻው ሰብሰቦ ገንዘብ ያሰባሰብ ነበር፡፡ ይህ ገንዘብ ለመድረክ የሚገባ አይደለም፡፡ ከዚህ በሚተርፈው ጊዜ የአንድነት ድጋፍ ሰጪዎች ስብሰባ እንዲጠሩ ጥያቄ ቀረበላቸው፡፡ የአንድነት ድጋፍ ሲጪዎች በጣም በሰለጠነ ሁኔታ ስብሰባ አድርገው በቂ ዝግጅት ሳይደረግ ድንገት የዚህ ዓይነት ስብሰባ መጥራት እንደሚቸገሩ አስታወቁ፡፡ በወቅቱ ደግሞ “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” በሚል አንድነት ለጀመረው ዘመቻ ድጋፍ እያሰባሰቡ ስለሆነ ተጨማሪ ሌላ ድጋፍ ማሰባሰቢያ ለማድረግ ጊዜ እንደሚወስድባቸው ምክንያታቸውን ገለፁ፡፡ ይህን ለዶክተር ነጋሶም፣ለዶክተር መረራም ተነግሯል፡፡ ዶክተር መረራ ግልፅ ሆኖ ያልገባው ምን እንደሆነ አልገባኝም፡፡ የኦሮሞ ኮሚኒቲን ሰብሰቦ ለድርጅቱ ገቢ እየሰበሰበ፣ የአንድነትን ለመድረክ አድርጉት የሚለውን ዝግጅት ያልተደረገበትን ጥያቄ አንቀበልም ማለት ለምን እንዳሰከፋው አላውቅም፡፡ በግሌ ለመድረክ ገቢ ለመሰብሰብ ዝግጁ መሆኔን በተደጋጋሚ ገልጨለት እያለሁ ግን ለምን ሊከሰኝ እንደፈለገ አላውቅም፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  የፈተናው ዘርፈ ብዙና ከባድ ነው - ጠገናው ጎሹ

ሌላው ዶክተር መረራ በመድረክ ውስጥ አነድነትን የአማራ ወኪል ለማድረግ የሚሰራውን ሸፍጥ (ኦፌኮ በኦሮሚያ፤ አረና በትግራይ፤ የፕ/ሮ በየነ ድርጅቶች በደቡብ) መታገል ሳይችል “አንድነት ከመድረክ ካልወጣሁ” ብሎዋል በሚል ይከሰናል፡፡ ይህን ሸፍጥ ግልፅ የሚያደርገው መድረክ በ2007 ምርጫ አንድም ዕጩ በአማራ ክልል ያለማቅረቡ ነው፡፡ እውነቱ አንድነት እንደ ፓርቲ ከመድረክ የመውጣት ጥያቄ አንስቶ አያውቅም፤ በግለሰብ ደረጃ የመውጠት ፍላጎት ያላቻው የሉም ማለት አይቻልም፡፡ አሁን ከመድረክ ጋር ለመስራት ሽር ጉድ የሚለው ሰማያዊ ፓርቲ መስራቾች ከአንድነት የወጡበት ምክንያቱ አንዱ የመድረክ ጉዳይ ነበር፡፡ አንድነት የነበረው ጥያቄ መድረክ የእውነት “ግንባር” ወይም “ውህድ” ፓርቲ ይሁን ነበር ጥያቄው፡፡ በግልፅ ዶክተር መረራ የውህደት ተቃዋሚ ሲሆን ሁሉም የመድረክ አባል ድርጅቶች አንድነት ላይ ያላቸው የጋራ ጥያቄ የገንዘብ ምንጫችን ይዋሃድ የሚል ነበር፡፡ በመጨረሻም አንድነት “በሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” በጀመረው ህዝባዊ እንቅስቃሴ ከኢህአዴግ እኩል የተረበሹት የመድረክ አመራሮች አንድነትን ከመድረክ አግደው፣ እንደ ኢህአዴግ ይቅርታ ካልጠየቀ አይገባም ሲሉ የአንድነት አባላት ደግሞ መድረክ ሲታዘል ተንጠልጥሎ የቀረ ሰለሆነ ከጫንቃችን ይውረድ ብለው ወስነዋል፡፡ ይህ ደግሞ ተገቢ ውሳኔ ነበር፡፡

አንድነት ከመድረክ መልቀቅ ብዙም ሳይወራ አንድነት በሁለት ሺ ሰባት ምርጫ ላይ በያዘው ግልፅ አቋም መነሻ በስርዓቱ እንዲፈርስ ሲወሰን ከመድረክ ባንወጣ አንድነት ሳይፈርስ እንደሚቆይ እንረዳለን፡፡ ውሳኔያቸን ግን አሁን መድረክ እና አባል ድርጅቶቹ ባሉበት አቋም በፓርቲ ሰም ከመኖር ለጥቂት ጊዜም ቢሆን ባሳየነው ቁርጠኝነት የበለጠ እንደሰታለን፡፡ አንድነት ከመድረክ ወጥቶም በግዛቸው ሸፈራው መሪነት ቢቀጥል መንግሰት ይህን አሳፋሪ እርምጃ አይወስድም ነበር፡፡ ምክንያቱም ባለበት የሚረግጥ ፓርቲ ማንም አይፈራውም፡፡ ግብ አስቀምጠን የምንሄድበትን አውቀን ስንሄድ ነው ፈተናው የመጣው፡፡ ዶክተር መረራ እንደፃፈው አንድነት የፈረሰው ከባለራዕይ ወጣቶች፣ ከሀረና፣ ከኦፌኮ፣ ወዘተ በመጡ አምስተኛ ረድፈኞች አይደለም፡፡ ከተለያየ ፓርቲ ወጥተው በተለይ ከብሄር ፓርቲ ለቀው አንድነትን የተቀላቀሉ ወጣቶች አንድነት ዶክተር መረራ እንደሚለው የአማራ ልሂቃን ሳይሆን የሁሉም ቤት መሆኑን በመረዳታቸው ነው፡፡ ይህን መራራ እውነት ደክተር መረራ መቀበል የግድ ነው፡፡ አንድነት የሁሉም ቤት መሆኑ ያስፈራው መንግሰት ያለምንም አፍረት አንድነትን ለማፍረስ የተነሳውም በተለይ በኦሮሚያ ስናደርገው የነበረው ያልተጠበቀ ንቅናቄ ጭምር ነው፡፡ አንድትን ለማፍረስ የተሰለፉት ሆዳሞች ደግሞ ከሁሉም ሰፈር የተሰበሰቡ ናቸው፡፡ ይህ ደግሞ የድርጅት ስራችን ክፍተት መሆኑን እናምናለን፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ከሕዝብ እውነተኛ ፍላጎቶች መማር ብልኅነት ነው - አምባቸው ደጀኔ

በመጨረሻ ዶክተር መረራ የአምቦ ወጣቶች እሰኪነግሩት ተሸፍኖበት የነበረው አውነት “የከብት ሌባን የሚጠብቀው ባለቤቱ ነው፤የኮሮጆ ሌባን የሚጠብቀው ህዝብ ነው፡፡” የሚለው ነው፡፡ አንድነት ፓርቲ በ2007 ምርጫ እሳተፋለሁ ሲል በአደባባይ የተናገርነው “ምርጫ ቦርድን ቁጥር ደማሪ እናደርገዋለን” የሚል ነበር፡፡ አንድም ምርጫ ጣቢያ ላይ ድምፁን የሚጠብቅ ህዝብ ካለሰለፍን ብንሰረቅም አንጮህም ብለን ተነሰተን ነበር፡፡ አሁንም ዶክተር መረራ ዘግይቶም ቢሆን እንደተረዳው የኮሮጆ ሌባን ለመጠበቅ የሚቆም መረጫ በሌለበት ምርጫ ፌዝ ነው፡፡ ለመምረጥ የተመዘገበ፤ ለሚደግፈው ድምፅ የሚሰጥ፣ የሰጠውን ድምፅ በትክክል የሚቆጥር ህዝብ ሲኖር ምርጫ ወደዲሚክራሲ መሸጋገሪያ ይሆናል፡፡ ይህ እንዳይሆን የሚከለክል መንግሰት ደግሞ በሌላ መንገድ ወንበሩን ለመልቀቅ መረጧል ማለት ነው፡፡

ቸር ይግጠመን!!!

4 Comments

  1. This guy is deep against Oromo. His center of writing or attempt to write is Oromo. The center of his attempt is trying to deny the suffering of Oromo and others under the past rulers. This is always observable in all of his writing whenever he writes and whatever topic he chooses to write on. I am sure he is a a grandson or son of National.
    I am not really supporter of MEISON. But does he know the the actions of This organization, where Oromo intellectual were visible, let the Oromo struggle dragged and also delayed the liberation of you people like from century old chauvinist approach toward of the God given right of all people. Instead of attempting to breathe your poison let you join the others who look forward with Oromo and other for equal right of the nation’s and nationalities.

    Adios,
    Hunde

  2. I agree with the writer on Merrera’s extreme politics. I have observed Merrara claiming Oromo for himself and demanding other none Oromos to support his struggle financially and public relation. But, you will never see Merrara voicing crime against Amhara. His PhD thesis is full of Amharaphobic go read it. Merrara and elite Oromo nationalists harbor deeply rooted hate for Amhara and just like their Shabea/TPLF masters, they don’t hide it. They write and speak their anti Amhara bigotry on public. We must tell them who they are.

    • @ Alex,

      Probably the Oromo intellectuals are writing the facts and truth of the past which are itching your hears. the issue is not with the writers. It is fully your problem who has hard time to accept the truth of the past.
      There is dirty saying that you and your likes throw out from your untrained mind and tongue. – in your mind Oromo intellectuals have no intellectual capacity to express their mind and they are followers of Shabia and TPLF. In your view Oromo Organizations advocating for Oromo case are mastered by Shabia and TPLF. All these and others expressions are reflections of your mindset about Oromo people. Let you know that the history you and your likes talk as your grandfathers history were made by Oromos like Balcha, Gebeyehu, H/Georgis, Ras Ali, Ras Mekonnen, Iyasu, Tayitu, Teferi Mekonnen and others. Educate yourself and get out of your narrow mindset which you got from your grandfather or fathers.

      When it comes to intellectual level, let the rest of the Ethiopians speak about the educated Oromo intellectuals despite your likes have tried to belittle them for more than 50 years until 1991.

      Walk up and get to the 21 century. Don’t tie your self in the thoughts of your grandfathes of 19 century.

      Adios,
      Hunde

  3. ዶክተር መረራ ከጠባብ ብሔርተኝነት ነፃ ሊወጣ ያልቻለ ገና አሁንም እንደተማሪ የሚንቀሳቀስ የተምታታ ፍልስፍናን የሚከተል ግለሰብ ስለሆነ በአገር ደረጃ ሊታመን ይሚችል አይደለም::
    የዛሬ 30 ዓመትም ዛሬም በንግግሩ ውስጥ ” የኦሮሞ ልጆች ” የሚለው ሃይለቃል አልለቀቀውም::
    ራስን በራስ የምወስን መብትን ካላብራራ
    አንቀጽ 39 ኝን በግልጽ ካልተቃወመ የሱም ድርጅት የተሰለፈው አማፈራረስ ክቆሙት ጋር ስለሆነ ሊታመን አይችልም::

Comments are closed.

Share