አቶ ስዬ በተመድ ተቀጠሩ

June 30, 2013

አቶ ስዬ በተመድ ተቀጠሩ  (ከኢየሩሳሌም አርአያ)

አቶ ስዬ አብርሃ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰላም አሰከባሪ ተቋም ውስጥ በወታደራዊ አማካሪነት በጥሩ ደመወዝ መቀጠራቸውን ምንጮች ጠቆሙ። በሙስና ወንጀል ተከሰው ከወንድሞቻቸው ጋር ለስድስት አመት ታስረው የተፈቱት ስዬ በተፈቱ ማግስት የአሜሪካን ድምፅ ራዲዬን ጨምሮ ለተለያዩ መገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ « ፖለቲካ ከልጅነቴ ጥርሴን የነቀልኩበትና አብዛኛው እድሜዬን ያሳለፍኩበት በመሆኑ ከትግሉ መድረክ ልርቅ ጨርሶ አልችልም» በማለት አስረግጠው መናገራቸውን እነዚሁ ወገኖች ያስታውሳሉ። « መድረክ » የሚል የፖለቲካ ስብስብ ከፈጠሩና የአንድነት አባል መሆናቸውን በይፋ ካወጁ በኋላ «ለትምህርት» በሚል ወደ አሜሪካ የመጡት ስዬ ከአንድነት ፓርቲ ሪፖርት እንዲያደርጉ የቀረበላቸውን ተደጋጋሚ ጥያቄና ማስጠንቀቂያ ችላ በማለት መልስ ለመስጠት ፈቃደኛ ሳይሆኑ መቅረታቸውን አመልክተዋል። በመጨረሻ « በቅርቡ አገር ቤት ተመልሼ ትግሌን እቀጥላለሁ » ማለታቸውን ያልሸሸጉት ምንጮቹ ስዬ ይህን በተናገሩ ሰሞን በሲያትል በተደረገ ስብሰባ ላይ « ለ21 አመት የተጀመረውን ልማትና ዲሞክራሲ እናስቀጥላለን» በማለት ብዙዎችን አንገት ያስደፋና ያሳዘነ ንግግር ማሰማታቸውን አስታውሰዋል። በአቶ መለስ ዜናዊ ሞት የተሰማቸውን ሃዘን ለመግለፅ አደባባይ መውጣታቸው ብሎም « ያሰራቸውን ስርአት ዲሞክራሲያዊ » አድርገው ለማቅረብ መሞከራቸው አስገራሚ ነበር ብለዋል።

ከሲያትሉ ስብሰባ በኋላ የኢትዮ ሚዲያ ኤዲተርን « አንተ አክራሪ ነህ» ሲሉ አቶ ስዬ ለመዝለፍ መሞከራቸውና በአንፃሩ ጋዜጠኛውም « ስዬ አንተ የተቃዋሚ ፓርቲ አትመስለኝም፤ የኢህአዴግ ባለስልጣን መሰልከኝ» በማለት እንደመለሰላቸው በስፍራው የነበሩ ታዛቢዎች ገልፀዋል። የተቃዋሚው ጎራ በተለይም «መድረክ»ን አዳክመው በመውጣት ለገዢው ፓርቲ አስተዋፅኦ አድርገዋል በማለት ብዙዎች ስዬን ይኮንናሉ። በቅርቡ ከስሚንቶ ጋር በተያያዘ በህገወጥ ንግድ ተሰማርተው ተገኝተዋል የተባሉትና የ«ምፍአም ትሬዲንግ» ባለቤት የሆኑት የስዬ ወንድም ምህረትአብ አብርሃ በድጋሚ በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው የታሰሩ ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም በሙስና ወንጀል ተፈርዶባቸው የእስር ጊዜያቸውን ጨርሰው እንደወጡ ይታወቃል። ከዚሁ ክስ ጋር በተያያዘ አቶ ስዬን ጨምሮ የሁሉም ወንድሞቻቸው የባንክ አካውንት እንዲታገድ ተደርጓል። « ስዬ የባንክ አካውንት እንኳ የለኝም » ሲሉ እንደቆዩ ያስታወሱት ምንጮች « አሁንስ ስዬ ምን ይሉ ይሆን?…ምን ያክል ገንዘብ በባንክ አስቀምጠው ይሆን?» በማለት ይጠይቃሉ።

 

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop