Hiber Radio: ዶ/ር አክሎግ ቢራራ እና የአረናው አምዶም ገ/ሥላሴ ልዩ ቃለምልልስ ስለምርጫው * አገዛዙ የሕዝቡን ድምጽ ወደጎን አድርጎ ለራሱ የሰጠውን የምርጫ ውጤት ይፋ ለማድረግ ተዘጋጅቷል * በኦሮሚያ አንዳንድ አካባቢዎች ተማሪዎች የሕዝብ ድምፅ እንዲከበር መጠየቅ ጀምረዋል * በአዲስ አበባ የ17 ዓመቷን ወጣት ሃና ሌላንጎን የደፈሩት ከ17 ዓመት እስከ እድሜ ልክ እስራት ተፈረደባቸውና ሌሎችም

/

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ
የህብር ሬዲዮ የግንቦት 16 ቀን 2007 ፕሮግራም

< …የምርጫው ውጤት አስቀድሞ የተገመተ ገዢው ፓርቲ የፈለገውን ድምጽ ለራሱ የሚሰጥበት የይስሙላ ነው … በአገር ውስጥም በውጭም ያለው ለውጥ እንዲመጣ የሚሰራው ሀይል ግን በአንድነት ፈጣን ውሳኔ መውሰድ አለበት። በአገር ውስጥ አብዮት መቀስቀስ እንዲችል… >

ዶ/ር አክሎግ ቢራራ የአገር ቤቱን የይስሙላ ምርጫ አስመልክቶ ለህብር ሬዲዮ ከሰጡት ማብራሪያ የተወሰደ (ሙሉውን ያዳምጡት)

<…በምርጫው ድምጽ መሰረቅን አስመልክቶ ገበሬውም ተማሪውም መምህሩም በአጠቃላይ ሁሉም ተመሳሳይ ግንዛቤ አለው። ድምጼ እንዳይሰረቅ ብሎ ነበር በድፍረት ስቃይ እየደረሰበት ታዛቢ ልሁን ለው….ተቃዋሚዎች ተባብረው በጋራ የህዝቡን ድምጽ ለማስከበርና አስገድደው ወደ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ለማምጣት መታገል ለባቸው …>

የአረና የሕዝብ ግንኙነት ሀላፊ ወጣት አምዶም ገ/ስላሴ (ከመቀሌ ምርጫውን አስመልቶ ለህብር ሬዲዮ ከሰጠው ማብራሪያ የተወሰደ )

በየመን ያሉ ኢትዮጵያውያን አጣብቂኝ እና የተባበሩት ሀይሎች የአየር ድብደባ ያደረሱት ጉዳቶች(ልዩ ዘገባ)

የኢሳት የገቢ ማሰባሰቢያ በቬጋስ(ከበዓሉ አዘጋጆች አንዱ ጋር የተደረገ ቃለ መጠይቅ)

አስተያየት በአገር ቤቱ ውጤቱ አስቀድሞ የታወቀ ምርጫ ላይ

ሌሎችም

ዜናዎቻችን

የተቃዋሚ የምርጫ ታዛቢዎች ጥቃት ሲፈፀምባቸው ዋለ

አገዛዙ የሕዝቡን ድምጽ ወደጎን አድርጎ ለራሱ የሰጠውን የምርጫ ውጤት ይፋ ለማድረግ ተዘጋጅቷል

ሕዝቡ በተዘረፈው ድምጹ ጉዳይ ተቃውሞ እንዳያቀርብ በሚል የሰብዓዊ ጥሰቱ ቀጥሏል

በኦሮሚያ አንዳንድ አካባቢዎች ተማሪዎች የሕዝብ ድምፅ እንዲከበር መጠየቅ ጀምረዋል

በአዲስ አበባ የ17 ዓመቷን ወጣት ሃና ሌላንጎን የደፈሩት ከ17 ዓመት እስከ እድሜ ልክ እስራት ተፈረደባቸው

ኬኒያዊው ጠበቃ ፕሬዝዳንት ኦባማ ልጃቸውን ከዳሩልኝ ለጥሎሽ 50 ከብቶች 70 በጎችና 30 ፍየሎች እሰጣለሁ ማለቱ ተሰማ

የኤርትራ መንግስት ለአገሪቱ ወጣቶች ስድትና ሞት የሰብዓዊ ተሟጋች ድርጅቶች ጭምር ይጠየቃሉ አለ

ኢትዮጵያና ኤርትራ በኮንፊዴሬሽን እንዲዋሃዱ የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ ጠየቁ

የሔጉ ውሳኔ በአዲስ መልክ እንዲቀየር አንድ ታማኝ የተቃዋሚ መሪ ገልፀዋል

ተጨማሪ ያንብቡ:  የህዝቡን እኩል ተጠቃሚነትና ህጋዊ ተጠያቂነትን ማስፈን ሃገሪቱን ላጋጠማት ችግር መፍትሄ ይሆናል- ጠ/ሚ/ር ዶ/ር አብይ አህመድ

ሁቨር በኔቫዳ ስራ እንዲጀምር ህጉ ፀደቀ

ስራ ከመጀመሩ በፊት ለተቆጣጣሪው ኩባንያ ማመልከት አለበት ተብሏል

የሚሉና ሌሎችም ዜናዎች አሉን

Share