በአርባ ጉጉ እና አካባቢው በአማራው ህዝብ ላይ የተፈጸመውን የዘር ማጥፋት ወንጀል መካድ አይቻልም – ሞረሽ ወገኔ የባህል ማህበር በስዊድን

(24/10/2014)
ሞረሽ ወገኔ የባህል ማህበር በስዊድን

ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያም ከሸገር ራዴዮ ጣቢያ ጋር በ09/08/2014 ያደረጉት ቃለ መጠይቅ ምንም እንኳ አማራውን አስመልክቶ የሰጡት ማብራሪያ እርስ በራሱ የተምታታ ቢሆንም፣ አማራውን ህዝብ የለም ከማለት አልፈው በአርባ ጉጉ በአማራው ህዝብ ላይ የተፈጸውን የዘር ማጥፋት ወንጀል ክደዋል። የፕሮፌሰር መስፍን ክህደት ’እስላም ኦሮሞዎች ክርስቲያን ኦሮሞዎችን ነበር የገደሉት’ ለማለት ከሆነ፣ ሀቁና መረጃዎቹ ከፕሮፌሰር መስፍን ክህደት ጋር እንደማይጠጣሙ በተከታታይ መረጃዎችን እየመዘዝን የአርባ ጉጉን እልቂት ለማቅረብ እንሞክራለን። ወይም ጉልበታቸው ለፈረጠመ ወንጀለኞች መውጫ ቀዳዳ በመፈብረክ የተለመደው የፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያም ”የወንድ በር እንስጥ” ፍልስፍናም ከሆነ በአማራው ህዝብ ላይ የተፈጸመውን የዘር ማጥፋት ወንጀል ያልተፈጸመና ያልተደረገ አያደርገውም ልንላቸው እንገደዳለን። ከአባሎቻችንና ከደጋፊዎቻችን ጋር ለመወያየት የግብዣ ወረቀት ከላክን በሗላ፣ ከስብሰባው በፊት በአማራው ህዝብ ላይ በአርባ ጉጉ የተፈጸመውን የዘር ማጥፋት ወንጀል ፕሮፌሰሩ መካዳቸው ብዙዎችን እንዳስቆጣቸው መልክት ሲደርሰን፣ እኛም አንድን ሰው ከሀዲ ከማለታችን በፊት መረጃዎችን አቅርቦ ፍርዱን ለአንባቢ ለመተው፣ በጊዜው የመላው አማራ ህዝብ ድርጅት ለኢህአዴግ፣ ለውጭ መንግስታት ዲፕሎማቶችና ለኢትዮጵያ ህዝብ እንዲደርስ ያወጣውን የአቋም መግለጫ ከሞላ ጎደል ይህን የመስላል።
የመላው አማራ ህዝብ ድርጅት ’መአህድ’ ኢህአዴግ በካድሬዎቹ አማካኝነት በአማራው ላይ የሚያካሂደውን የእልቂትና የሽብር ዘመቻ እያፋፋመው የአማራ ህዝብም ከፋሽስቶች ዘመን በባሰ ሁኔታ እያለቀ መሆኑን ባወጣው የአቋም መግለጫ አብራርቷል።
የመአህድ ፕሬዜዳንት ለሽግግር መንግስቱ ምክር ቤትና ለልዩ ልዩ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ባቀረቡት መግለጫ ላይ እንዳብራሩት በአማራው ህዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለው ግፍና በደል ”ሰብአዊ አእምሮ ሊሸከመው የማይችል ነው” በተለይ ከግንቦት 26 ቀን 1984 ዓም ጀምሮ ጭፍጨፋው በከፋ መልኩ እንዲቀጥል ተደርጎ የጭፍጨፋው ሰለባ የሆነው አማራ ሬሳው በገደል ውስጥ እንዲጣልና በቤት ውስጥ እንዲቃጠል እየተደረገ ነው። ይላል

ተጨማሪ ያንብቡ:  የምስራች ለኢህአዴግ የምጡቅ ጭንቅላት ባለቤትነት ምልክቶች በአንድ ካድሬ ተገኘ

”ከግንቦት 26 ቀን 1984 ዓም ጀምሮ በአማራው ላይ ከፍተኛ ጭፍጨፋ የተካሄደው በአርሲ ክፍለ ሀገር በአንቦሳ ከተማና በአካባቢው ነው። ኢህአዴግ በዚህ ስፍራ የሚኖሩ ተወላጆችን ሰብስቦ ’በነዚህ መንደሮች የሚኖሩ አማሮች ይገደሉ ብላችሁ ፈርሙ’ በማለት ትእዛዝ ሰጠ።

በማግስቱ ግንቦት 27 ቀን 1984 ዓም አቡሌ የተባለውን መንደር በኦህዴድ (የኦሮሞ ህዝብ ዲሞክራቲክ ድርጅት) የታጠቀ ወታደር ተከቦ ተኩስ ከተከፈተ በሗላ መንደሩ በላውንቸር መደብደብና ማቃጠል ሲጀመር ህዝቡ ህይወቱን ለማዳን ህዝቡ በየአቅጧጫው መሸሽ ጀመረ። ከሚሸሹት መካከል 30 ህጻናት ቤተክርስቲያን ቅጽር ግቢ እንደተጠጉ ከቤተክርስቲያኑና ከካህናቱ ጋር ተቃጥለዋል። አከታትሎም 150 የአማራ ነዋሪ ቤቶች እንዲቃጠሉ ተደርጓል።

የአውራጃው የኢህአዴግ ተወካይ አቶ ዲማ ጎርሜሳ ለወራሪው ሰራዊት ”አማራን መጨረስ ዛሬ ነው” የሚል መፈክር በማሰማት አበሳ የሚባለው የአማሮች መንደር እንዲከበብ አስደርገው ህዝብ ከቤቱ ሳይወጣ መንደሩ እንዲቃጠል ተደርገ። በመንደሩ ከነህይወታቸው በቤት ውስጥ እንዳሉ የሞቱት ቁጥር የማይታወቅ ሲሆን የቤቶቹ ጠቅላላ ብዛት 150 ነው። ከቃጠሎው የተረፉት 50 ሰዎች ተይዘው በጥይት ተረሽነዋል።

በሌላም አሼ በተባለ መንደር በአማራ ተወላጆች በአካባቢው የሚፈጸመውን ሰቆቃ እየተመለከቱ የመንግስት ሃይል ያድነናል ብለው ሲጠብቁ 25 ሰዎች የኢህአዴግ ሰራዊት ፈጅቷቸዋል።

በጉና ወረዳ አዲስ አለም በተባለ ቦታም 150 ቤቶችን ከነነዋሪዎቹ ከማቃጠላቸውም ሌላ ሁለት የአገር ሽማግሌዎች እጅ እግራቸውን አስረው አቃጥለዋቸዋል።

ዋቄንትራ ከተባለው መንደር 100 ቤቶችን ከነነዋሪዎቹ አቃጥለዋቸዋል።

መሶ የተባለውን መንደር በጦር እንዲከበቡና 100 ቤቶች እንዲቃጠሉ ተደርጓ ከቃጠሎው የዳኑት 80 ሰዎች እጃቸው ታስሮ በኦህዴድ (የኢህአዴግ አንዱ ክፍል) ተረሽነው ሬሳቸው ቆሬ ከሚባል ገደል ውስጥ እንዲጣል ተደርጓል። አንድ ሰው በተአምር ከዚህ መአት ተርፏል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ዕዉነትን ለመናገር የሚደፍር በመከራ እና ጭንቅ ጊዜም ከፊት የሚገኝ ሠዉ ከወዴት ይሆን ?  - ማላጂ

እንደሴ ባዩ የሚባለው መንደር ነዋሪ የሆኑ አማሮች በተመሳሳይ ሁኔታ በኦህዴድ ሰራዊት እነዲከበቡ ከተደረገ በሗላ ከመንደሩ ነዋሪዎች መካከል 80 የሚሆኑት እጅ እግራቸውን ታስረው ተወስደዋል። ወደ ገደል እንደተወረወሩም ይወራል።
ስድስት ቤተ-ክርሲቲያናት በዚህ አካባቢ ተቃጥለዋል። ይህ ሁሉ የተፈጸመው ግንቦት 27 ቀን 1984 ዓም በአንድ ቀን ነው ሲል የመአህድ መግለጫ አብራርቷል።

እንግዲህ ፕሮፌሰር መስፍን በሸገር ራዲዮ ጣቢያ የካዱት ይሄንን በአማራው ህዝብ ላይ የተፈጸመውን የዘር ማጥፋት ወንጀል ነው።
moweswe@gmail.com

9 Comments

  1. ሞረሽ ወገነ ትግሉን ከ ፕሮፈሰር መስፍን ጋር አደረገ እንደ? የሞረሽ ወገነን ደህና ጅምር የጎጠኛ ጎንደረና የደርግ ካድረ ስብስብ አሽመድምዶ ሲገድለው ማየት በጣም ያሳዝናል::ሞረሽ ውስጥ ቁንጮ ላይ ላሉት የጎንደር መሃዪምናንና የኢስፓ ካድረዎች ፕሮፈሰር መስፍንን ከጎንደር ሳይሆን ከትግረ ትግረዎች በላይ አንደሚጠሉአቸው አውቀናል; ; ግን አናት ደንቆሮቆች መስፍንን በመስደብ አንደሳቸው ትልቅ መሆን አይቻልም;; ስድብ አውቀት አይደለም;; አዋቂ ለመሆን ከመሳደብ ተማሩ ተማሩ ተማሩ”

  2. Amhara elites are known for the betrayal of the suffering of their own people not only professor Mesfin there are many many Amhara elites who deny the continuing genocide on their own people and many of them are helping to facilitate the Genocide perpetrated by TPLF OLF and SHABIA.
    WHAT IS WRONG WITH AMHARA ELITES? why Amhara elites are the only elites in the world who does not give a shit about the suffering and displacement of their own people?

  3. በመሰረቱ በኢትዮጵያዊነት የኮራውን፣የዳበረውን፣የተዋደቀውን፣የተቃቀፈውን “አማራ” ካልተባለ በወያኔ ከፋፋይነት መዝገብ ስሙ ካልቀለመ የምትሉ የወያኔ ሙንጣዞች የስድብ ባንካችሁን መስፍን ወልደማሪያም ከከፈታችሁ ከራረማችሁ።ዛሬ ከሃዲ፣ትላትና የጃጀ ስትሉ ይህ ከቶም የኢትዮጵያ የጨውነት ባህል ሳይሆን፣የመደዴ እረኛ ትፋት ነው።በጌታችሁ ወያኔ መርሆ መሰረት በጎሳ ፖለቲካ “አማራ” የሚባል አናሳ ጎሳ አለ ብላአቸሁ ማጭበርበራችሁ ሳያንስ፣በአማራው ስም የስድብ የዘለፋ ሱቅ መክፈታቸሁ የሚያሳዝን ነው።ወኔ ጉንድሽ በመሆናቸሁ በኢትዮጵያዊነት መቆምም መታገልም አትችሉም።ኢትዮጵያዊነትን፣ አማራ ፈላሻ እያላችሁ መከፋፈል ትንሽነት ነው።ወያኔነትም ነው።ለመሆኑ መቼ ነው “አማራ” የምትሉት ኢትዮጵያዊ ወክሉኝ፣በስሜ አጭበርብሩ ያልችሁ? ደመራችሁም ቀነሳችሁ፣አባዛችሁም አካፍላችሁ፣በትኛውም የጎሳ ሂሳብ ሕግ የማበገረው “ኢትዮጵያዊነት” ብቻ ነው። “በስሜት የተሳሰረና አንድነት ያለው፣የአማራ ኅብረተሰብ የሚባል ነገር የለም”።በኢትዮጵያዊነት ሰጥሞ፣በኢትዮጵያዊነት አንድ ወጥ ሆኖ አማሪኛ ቋንቋ እየተናገረ አለ ይኖራል።

  4. መኢአድ በጋምቤላ አማራው ላይ እየደረሰ ባለው ጭፍጨፋ ያቀረበውን ማስረጃ እንዲሁም የኢሃዴግ መሪዎች ባደባባይ የተናገሩትን በቴፕ ያለ ማስረጃ በአርባጉጉ ጉራፈርዳ ያሶና መተከል ወዘተ. ፕሮፌሰሩ ምን ብለው ሊያስተባብሉት ይችላሉ? እንደኔ ከሆነ ለሰውዬው ቦታ ከመስጠት አማራውን ከዳር እስከ ዳር ለማንቀሳቀስና ራሱን እንዲያድን እንዲችል መስራቱ ቢመረጥ የሚሻል ይመስለኛል:: ሞረሽ በአማራው ቤት ውስጥ ገብቶ የማንቃት ጥበብ ማፈላለግና ትግል ብሎ አማራውን ማታገል የሚችልበትን ዘዴ ላይ ማተኮር አለበት:: ለመሆኑ የሚያወጣቸውን መግለጫዎች በአገር ቤት ያለው አማራ ያገኘዋል ወይ? ድርጅቱ ስለመኖሩ ኢትዮጵያ ያለው አማራ ያውቃልን? ሞረሾች አስቡበት::

  5. I agree with professor Mesfine. Where is Amhara?If there is Amhara defend yourself from extinct. Shown up like professor Asrat

  6. ፕሮፌሰሩ በምን ስሌት አስበው ነው አማራ የሚባል ብሄረሰብ የለም ብለው ደፍረው ሊናገሩ የቻሉት? ይሄ ማለት በአማራ ህዝብ ላይ የሚካሄደውን ግልጽና ስውር ጭፍጨፋ ከመደገፍ ተለይቶ አይታይም ። በሌላ አባባል ወደ 35 ሚሊዮን የሚጠጋ አማራ እንዲሁም ወደ 10 ሚሊዮን የሚጠጋ ከተለያዩ ብሄረሰቦች ቅልቅልና ወደ 5 ሚሊዮን የሚጠጋ በውጭ የሚኖሩ የአማራ ስደተኞች፡ በድምሩ 50 ሚሊዮን የሚጠጉ አማራዎችን ፕሮፌሰሩ በቁማቸው ቀብረዋቸዋል ማለት ነው? ለግንዛቤ ያህል፦ ሂትለር ከ20 ሚሊዮን በላይ የሶቬት ህብረትን ህዝብ በአውዳሚ መሳሪያ አጠፋው፡ እርስዎ ደግሞ በቃልዎት ብቻ 50 ሚሊዮን የሚጠጉ አማራዎችን ያጠፉ በኢትዮጵያ 3000ሺ አመት ታሪክ ውስጥ የመጀመሪያው ሰው ነዎት። ስለዚህ ስህተትዎን በቅርብ ጊዜ ውስጥ እንደሚያርሙት እምነቴ የጸና ነው። ለምሳሌ ያህል የሌሎች ሃገሮች ምሁሮች በምን አይነት መልክ ሃሳባቸውን እንደሚገልጹ እንመልከት፦ http://survincity.com/2010/07/russian-scientists-appeal-to-jews-in-russia/

  7. This is a typical backward Gondere propaganda. They had bee claiming that other Amharas are inferior and they are superior. Now, Moresh (ESAPA) is thinking and talking in terms of Begemeder-Gonder only. Professor Mesfin is a gentle person who knows what he is doing and saying. He was born and lived in South and knows that area than the Moresh people who are mainly from Metema area who are closer to Sudan than to other Ethiopian brothers and sisters.
    Therefore, ATo Tekle Bishaw is proving his being Dergue cadre and ignorant about history and facts. He wants to use peoples’ emotions simply by denouncing and defaming respected individuals and Ethiopians unless they are from Gonder.

  8. አማራ የሚባል የለም ማለት ምን ማለት ነዉ?
    እኔ 100% አማራ ነኝ!

Comments are closed.

Share