የኢትዮጵያ ወጣቶች ብሄራዊ ንቅናቄ የሰማያዊ ፓርቲን የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ ደገፈ

(ዘ-ሐበሻ) በአዲስ አበባ ሰማያዊ ፓርቲ ሚያዚያ 29 2005 ዓም የአፍሪካ ህብረት የወርቅኢዮቤልዮ በአል በሚከበርበት ሰዓት ሰላማዊ ሰልፍ መጥራቱን ተከትሎ “የሰማያዊ ፓርቲ ጥሪ የሁሉም ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ ጥሪ ነው!” ያለው የኢትዮጵያ ወጣቶች ብሄራዊ ንቅናቄ “ሰማያዊ ፓርቲ በመግለጫው የጠቀሳቸው አራት ጥያቄዎች የኢትዮጵያ ወጣቶች ብሔራዊ ንቅናቄ መልስ እንዲያገኙ ከሚታገልላቸው ዋና ዋና የህዝብ ጥያቄዎች መካከል ውስጥ የሚገኙና ዘረኛው የወያኔ/ኢህአዴግ መንግስት በዘረጋው የጭቆናና የግፍ መረብ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ በግዴለሽነት በግልፅ በአደባባይ ከሚፈፅመው ስቃይ ፣ መከራና ፣ እንግልት ጥቂቶቹ በመሆናቸው ፤ የኢትዮጵያ ወጣቶች ብሔራዊ ንቅናቄ ሰማያዊ ፓርቲ ያቀረበው ወቅታዊና ተገቢ የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪን ሙሉ ለሙሉ የተቀበለው መሆኑን በአፅንዎት ይገልፃል::” ሲል ባወጣው መግለጫ ላይ አስታወቀ።

ንቅናቄው ለዘ-ሐበሻ በላከው መግለጫው “የሰማያዊ ፓርቲ ጥሪ ህዝባዊ በመሆኑ ፤ በዚህ ዘረኛ የወያኔ/ኢህአዴግ መንግስት ከልክ ያለፈ ጭቆና ፣ ረገጣና ፣ እንግልት ደርሶብኛል የምትሉ ንፁሃን ኢትዮጵያውያን ዜጎችና ፣ በምንወዳት ሃገራችን ለህዝብ የሚበጅ ቀና ለውጥን የምትመኙ ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ ፤ እንዲሁም ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች ፣ የሃይማኖት ተቋማትና ፣ የሲቪክ ማህበራት ታላቅ ሃገራዊ ሃላፊነትና የህዝብ አደራ በጫንቃችሁ እንደተሸከማችሁ በመገንዘብ ፤ የሚጠበቅባችሁን ህዝባዊ ተልኮ መፈፀም ታሪካዊ ግዴታችሁ መሆኑን በመረዳት ፤ ከሰማያዊ ፓርቲ ህዝባዊ የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ ጎን እንድትቆሙ ሲል በጥብቅ እያሳሰበ ፤ ሃገራዊ ጥሪውን በአክብሮት ያቀርባል:: የሰማያዊ ፓርቲ ጥሪ የሁሉም ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ ጥሪ ነው!” ብሏል።

[gview file=”https://zehabesha.info/wp-content/uploads/2013/05/የሰማያዊ-ፓርቲ-ጥሪ-የሁሉም-ሃገር-ወዳድ-ኢትዮጵያዊ-ጥሪ-ነው.pdf”]

 

ተጨማሪ ያንብቡ:  በጎንደር የአንድነት ፓርቲ አባል ለአቤቱታ ባህርዳር ሄዶ የደረሰበት አልታወቀም

3 Comments

  1. This is Good news and this is what it needs to be done. Those useless people who called themselves ” opposition” group, If they care about Ethiopia, then this is the time to go out and demonstrate with them but I don’t think they will do that. I’m proud of you two! I hope more will join. We are with you all the way and God bless you all.

  2. We are proud of the youth. We will definitely be part of it. Thanks guys, keep it up!!! Freedom is not free

Comments are closed.

Share