June 6, 2014
5 mins read

ኡስታዝ አቡበከር አህመድ በጨለማ ክፍል መታሰራቸው ተሰማ

በአቡ ዳውድ ኡስማን –

(ድምጻችን ይሰማ እንደዘገበው)

በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት በሃሰት በሽብርተኝነት ተወንጅለው በእስር የሚገኙት ኮሚቴዎቻችንን የማረሚያ ቤቱ አስተዳር ሆን ብሎ የማሸማቀቅ እና የማዋከብ ተግባር እየፈፀመባቸው እንደሚገኝ መዘገባችን ይታወቃል::

በማረሚያ ቤቱ ከሚገኙ ህግ ታራሚዎች እና እስረኞች በተለየ መልኩ ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ በኮሚቴዎቻችን አመራሮች እና አብረዋቸው በታሰሩት ወንድሞች ላይ ትኩረት በማድረግ አቃቂር የ መፈለግ እና ባገኙትም ነገር ጉዳዩን በማግነን ለማሸማቀቅ እና ለማንገላታት የማረሚያ ቤቱ አስተዳደር አቶ አምባዬ እና የደህንነት ሃላፊ አቶ ኤርሚያስ እየተንቀሳቀሱ መሆናቸወ የተገለፀ ሲሆን ሲዝቱባቸው በነበረው መሰረትም የህዝበ ሙስሊሙን መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሆኑትን ኡስታዝ አቡበከር አህመድን በጨለማ ክፍል ውስጥ እንዲታሰሩ መደረጉን ምንጮች አስታውቀዋል፡፡

በኮሚቴዎቻን እና በወንድሞቻችን ላይ ልዩ ክትትል በማድረግ በጨለማ ክፍ ውስጥ እንዲሰቃዩ ለማድረግ ከበላይ የደህንንት አካላቶች ትዕዛዝ የተላለፈ ሲሆን ይህንንም ተግባራዊ ለማድረግ ድንገተኛ ፍተሸ በማድረግ ማንኛው እስረኛ ጠያቂዎች ሊሰጡት የሚችሉትን ገንዘብ ይዛችሁ ተገኝታቹሃል በሚል ኡስታዝ አቡበከር አህመድን እና ሼህ መከተ ሞሄን የማስፈራራት እና ቃላቸውን እንዲሰጡ የማድረግ እንቅስቃሴ ሲየደርጉባቸው ቆይተዋል፡፡በትላንትናው ዕለት ሃሙስም ኡስታዝ አቡበከር አህመድን በጨለማ ክፍል ውስጥ እንዲታሰር ማድረገቻውን ምንጮች አስታውቀዋል፡፡

ከሌላ እስረኞች በተለየ ሁኔታ ኮሚቴውን የማዋከቡ እና በጨለማ ቤት ለመቅጣት የማስፈራቱ ድርጊታቸው ህገ ወጥ መሆኑን ኡስታዝ አቡበከር አህመድ ለማረሚያ ቤቱ ደህንነት ሃላፊዎች ሲያሳስቡ ቢቆዩም የማረሚያ ቤቱ ሃላፊዎች ግን ኡታስዝ አቡበከርን በጨለማ ክፍል ውስጥ እንዲታሰር ማድረጋቸው ታውቋል፡፡

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከህግ እና ክፍርድ ቤቱ ተዕዛዝ ሁሉ የበላይ በሆኑ የደህንነት ሃይሎች በኮሚቴዎቻችን አመራሮች ላይ እና በተወሰኑ ወንድሞች ላይ እየተደረገ ባለው ጥብቅ ክትትል እና የዚህ መሰሉ የጨለማ ቤት ቅጣት የሚፈፀም ከሆነ ኮሚቴዎቸችን ለፍርድ ቤቱ እያቀረቡ የሚገኙትን የመከላከያ ምስክር እስከማቆም ሊደርሱ እንደሚችሉ ታውቋል፡፡ ህግ ተፅፎ ባለበት ሃገር ህጉ እየተጣሰ ንፁሃን እንዲንገላቱ መደረጉ የፍርድ ቤቱን ሚና ከቁብ የማያስገባ መሆኑን የሚያረጋግጥ በመሆኑ በችሎቱ የመቀጠሉ ሁኔታ አጠያያቂ ሊሆን እንደሚችል ተገምቷል፡፡

ሼህ መከተ ሞሄ እና ኡስታዝ አቡበከር አህመድ ላይ በጨለማ ክፍል አስገብተው እንደሚቀጧቸው የማረሚያ ቤቱ ሃላፊዎች ሲዝቱባቸው የቆዩ ሲሆን ዛቻቸውን በተግባር በመለወጥ በጨለማ ክፍል ውስጥ እንዳስገቧቸው ታውቋል፡፡

ኡስታዝ አቡበከር አህመድ እየተፈጸመባቸው የሚገኘውን ህገ ወጥ ተግባር ለፍርድ ቤቱ ያሳውቃሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ኡስታዞቻችንን እና ወንድሞቻንን አላህ ይጠብቅልን!!!

1 Comment

  1. The Minority Junta that has run the country by the law of the jungle is staggering when opposition movements are gaining momentum time after time. They are killing innocent people on a broad day light and frogmarching thousands of people, who they believe sympathizers of opposition, to prison day in, day out. Picking and obliterating prominent figures on the face of the earth is now a daily order in Ethiopia.
    I believe throwing Ustaz Abubaker into a solitary cell is part of the operation that has been going on in Ethiopia. The Trial of Ethiopian Muslim representatives, who have been languishing in Kelito prison, has attracted millions of Ethiopia inside and outside the country regardless of religion.

Comments are closed.

Previous Story

“ያመመኝ በእሙ የተነሳ ስለሆነ ‘ያመመኝ በሷ ነው’ የሚል ነጠላ ዜማ ሰርቻለሁ” – ድምፃዊ ጌድዮን ዳንኤል

989TeddyAfro NYC 26
Next Story

ቴዲ አፍሮ” – ከኮካ ኮላ – የዓለም ዋንጫ – የተሰጠ መግለጫ

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop