May 2, 2013
5 mins read

የአቡነ ጴጥሮስ ሐውልት ወግ – ከበእውቀቱ ስዩም

02

ማለዳ መነሣት አልወድም፡፡ ዛሬ ግን አቡነ ጴጥሮስ ከመታሰቢያቸው ዙፋን ሲወርዱ ለመታዘብ በማለዳው ካልጋየ ጨክኘ ወረድሁ፡፡ ለአቡነ ጴጥሮስ ፍቅር ስል የማለዳ እንቅልፌን ብሰዋ አይቆጨኝም፡፡ በቅርቡ በሚከፈተው ጦማሬ ላይ ስለ ጀግናው ጴጥሮስ በሰፊው የመጻፍ ሐሳብ አለኝ፡፡
በቦታው ስደርስ፣የጴጥሮስ ሀውልት በጣውላ ተገንዞ ቆሟል፡፡ድብርት ተጫጫነኝ፡፡ምናልባት አያቶቼ አቡኑ ሲረሸኑ በተመለከቱበት ሰአት የተሰማቸው ስሜት እንዲህ ሳይሆን አይቀርም፡፡ የራስ ቁር የደፉ የቀን ሠራተኞች በአቡኑ ትክሻ ላይ እንደ ወፍ ሰፍረዋል፡፡ ወደ መርካቶ በሚሄዱ ተሳፋሪዎች የተሞሉ ሚኒባሶች አደባባዩን ታክከው ሽው ይላሉ፡፡ ተሳፋሪዎቹ፣ በመስታውት አሻ…ግረው የሚመለከቱት ትእይንት ብዙ የመሰጣቸው አይመሰልም፡፡
በፋሲካ አስፈሪ የዶሮ ዋጋ ለተጠመደ አእምሮ ታሪክ ምኑ ነው??
ከተመልካቹ በላይ የፖሊሱ ቁጥር የሚበልጥ መሰለኝ፡፡አንድ ፒካፕ መኪና ስትበር መጣችና ቁና ሙሉ ፌደራል ፖሊስ አራገፈች፡፡ሰብሰብ ብለን በቆምንበት አንዱ ፖሊስ ጠጋ አለና‹‹ እናንተን አይመለከታችሁም ከዚህ ሂዱ›› አለ፡፡ካጠገቤ የቆመ ጎበዝ ‹‹ማየት መብታችን ነው›› ብሎ መልሶ ጮከበት፡፡አሀ! የጴጥሮስ መንፈስ አልከሰመም ማለት ነው፡፡ፖሊሱ ምንም ሳይመልስ ከሬድዮ መገናኛው ጋር እየተመካከረ ካካባቢው ራቀ፡፡
ከጥቂት ጊዜ በኋላ ጋዜጠኛ ጓደኞቼ ካሜራቸውን ታጥቀው ደረሱና ተቀላቀሉኝ፡፡ ሀውልቱን ማስቀረት ስላልቻሉ ምስሉን ቀርጸው ለማስቀረት ተሯሯጡ፡፡
ድንገት ቀና ብየ ሳይ ከሀውልቱ ፊትለፊት ጅማ በር የሚባል ፣ጣልያን የሠራው አሮጌ ሕንጻ ይታየኛል፡፡ባቡሩ የአቡነ ጴጥሮስን መታሰቢያ ደቅድቆ ሲያልፍ፣ጣልያን ሠራሹን ግንብ ንክች አያደርገውም፡፡ጉደኛ ባቡር!!!
በጣውላ የተገነዘውን የአቡኑን ሀውልት ለመሸከም አንድ አዳፋ ረጅም ተጎታች መኪና ብቅ አለ፡፡ዳይኖሰር የመሰለ ክሬን ሀውልቱን ነቅሎ ሲያንጠለጥለው፣ሀውልቱ የነበረበት ቦታ ጥርስ የወለቀበት አፍ መሠለ፡፡ቀሪውን የማየት ፍላጎት ስላልነበረኝ ከጓደኛየ ጋር ወደ ፒያሳ አቀናሁ፡፡ብዙ ነገር እዬተለወጠ መሆኑን አየሁ፡፡የጥንቱ መሀሙድ መዚቃ ቤት ወደ ቡቲክ መቀየሩን አስተዋልሁ፡፡ የጥንቱ አያሌው ሙዚቃ ቤት ፍራፍሬ መሸጫ ሱቅ ሆኗል፡፡ከጥቂት ወራት በፊት ብርቱካኔ የሚለው ሙዚቃ ይንቆረቆርበት የነበረው ቦታ ፣አሁን ብርቱካን በኪሎ ይሸጥበታል፡፡
አዲስአበባ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ያለጥርጥር፣ባቡር ይኖራታል፡፡ቀለበት መንገዶች ይኖሯታል፡፡ አሪፍ ህንጻዎች ይኖሯታል፡፡ነገር ግን፣ ትናንት የሚባለው ነገር አይኖራትም፡፡ A city without past ላዲስ አበባ የተገባ ቅጽል ነው፡፡
ወደ ሰፈሬ የሚሄድ ታክሲ ስፈናጠጥ፣ የሚከተሉት የጸጋየ ገብረመድህን ግጥሞች ሽው አሉብኝ፡፡
….መጭው ደመና ጥቁረቱ፣
ጮቁ፣ ማጡ፣ የክረምቱ፣ አቤት ዝቅጠቱ ማስፈራቱ
የኛስ ትውልድ አከተመ፣ አገራችንን አምክነን
የነገስ ዘር ምን ይበለን፣ስንተወው ሲኦል አውርሰን
(ከበ እውቀቱ የቀደሙ ሥራዎች መካከል ካላያችሁት እዩለት ዘንድ እነሆ፡)

7 Comments

  1. በጣም ያሳዝናል። ምን ብዬ ሀዘኔን እንደምገልፀው እንኳን አላውቅም። ሀውልቱን ለማፍረስ ስለተፈለገ ብቻ እንጂ ሀዲዱ ሀውልቱ በነበረበት ስፍራ ብቻ እንዲያልፍ የሚያስገድደው ምንም ዐይነት የተፈጥሮ ሁኔታ ሊኖር አይችልም። በእኔ በኩል የሀውልቱን መፍረስ የመለስን ራዕይ የማስቀጠል አካል አድርጌ ነው የማየው። መለስ ኢትዮጲያን ከማፈራረስና ለባዕዳን አሳልፎ ከመሸጥ ውጪ ምንም ዐይነት ራዕይ አልነበረውምና።

    ለነገሩ ኢትዮጲያ እንደአቡነጴጥሮስ ያሉ የሞቱላትን ጀግኖች ሀውልት እያፈረሰች እንደመለስና ሳሞራ ያሉ የገደሏትን ባንዳዎች ሀውልት የጀመረችው ዛሬ አልመሰለኝም። አሁን የሚታየውን ሁኔታ ልዩ የሚያደርገው በተጠናና በተደራጀ መልኩ በዕቅድ የሚፈፀም የጥፋት እርምጃ መሆኑ ነው።

  2. andegna minim tiyake yelelew.
    bewketu much love and respect for you.
    andegna neh.

  3. It is okay Wyanis r not going to for ever, We will put back in a better place.
    People in Jijga are pissing on Meles statue, We also will have a big statue for Abebe Gelaw and all ESAT staff.

  4. this terrifies the father of everything in this remarkably beaaaaaaaaauuuuuuutiiiiiiiifl country of of mine and yours. I’ve been living in constant fear that these addicts were going to leave this country simply with “contemporary” claims stuffed with borrowed fascist, racist, rootless, ideas. They should be placed tens of rounds on psychiatric holds and placed under their grand (but Banda)parents conservatorship. They deserve neither me nor my land. I would be creatively dead if I were to say that I am alive. This act situated us between failures and those “banda’s” boys scaling heights of success. But But a human being is on the right track, if he learns from the bad phase of life. If we can learn from such a period when we were down, then we are on the right track. Now I feel blessed that I experienced real downs in my country’s history. I have one thousand reasons to live as well as die for. Every day is a test! To your wonder I belong to the evangelical sect. St. Peter is deep inside my philosophy.

  5. በውኑ ክርስቲያን ኢትዮጵያውያንን ምን ነካን? ምን አይነት የፍርሃት ቆፈን ውስጥ ብንገባ ነው? ሁሉን እንዳላየን የምናለፍፈው? እንዴት ከሙስሊም ወንድሞቻችን መማር አቃተን? ነጥሎ መምታት የለመደው ወያኔ በሁለታችንም ላይ ዱላውን ካሳረፈ እንሆ ሁለት አስርት አመታት አለፉ። እኛን ክርስቲያኖችን ካለ መሪ አስቀረን፤ አባቶችን ለሁለት ከፈለ፤ የቤተክርስቲያንን ሐብትና ንብረት ዘረፈ፤ የእራሱ የሆኑትን፤ ቆብ፣መቋሚያ፣ቀሚስ፣መስቀል፣ጽናጽል የያዙ ቀልበ ቢስ ሰዎችን፤ በቤቱ ክርስቲያኒቱ ልዩ ልዩ መዋቅር ውስጥ አስገብቶ፤ ተቆጣጥራታል። በዚህም ብዙ ምዕመናንን ተኩላ ነጠቃቸው። ይሄን ደባ በክርስቲያኑ ፈጽሞ ከአጠናቀቀ በዃላ ወደ ሙስሊ ዞር ሲል ግን እንደ ጠበቀው አላገኘውም። መሪያችንን እኛው ነን የምንመርጥ ብለው ግብ ግብ እንደ ገጠሙት ናቸው። እንደ ክርስቲያኑ በቀላሉ ዘው ብሎ አልገባም። ጋና ትግል እንደ ገጠመ ነው!!!! እነሱ ጋ እንዲህ ትግሉ ሲበረታ ሰሞኑን ወደ ክርስቲያኑ ዞር ብሏል። ሌላውን እንተወውና ከሀይማኖት ጥበቃ አልፈው፤ ለአገር ግድ ብሏቸው፤ ለእምዬ ኢትዮጵያ ሲሉ፤ በግፍ የተገደሉትን ያቡነ ፔጥሮስን ሃውልት፤ በመንገድ ስራ ስበብ፤ በማን አለብኝነት፤ የስቅለት ዋዜማ፣ የጸሎት ሐሙስ ዕለት መንቅለው ጣሉት። አምላከ ኢትዮጵያ እነሱንም እንዲሁ ይንቀላቸው። እኛ ከርስቲያኖች፤ አይነተን እንዳላየን አለፍን!! ውርደት ነው። የፊታችን እሁድ፤ ትንሳዬከ ብለን ስንዘምር ምን ይሰማን ይሆን? በውኑ አምላካችን ምስጋናችንን ይቀበል ይሆን? አይመስለኝም!! ወዮልን!

  6. *****************************
    ያ መከረኛ በቡር ጀግናውን አነሳው
    ጌታ በቸርነቱ መለስን ነቀለው
    የተነሳና የተነቀለ ልዩነት አለው
    የተነሳው ተመልሶ ተስተካክሎ ሲተከል
    ሟች በራዕይ በፋውንዴሽን ሲሸነግል
    አቡኑ በሀገር መውደድ እንቢኝ ብለው
    ሌላው በሀገር ክህደት እደወጡ መቅረታቸው
    ሳትመልሳት ብትቀር በቦታዋ አሻስለህ በቦታው
    ኢትዮጵያዊ አደለም ጣሊያን ነው የሚያዝነው
    ለሀገር የሞተና ሀገር የገደለ አንድ አደለም በለው!!
    ****************************************

  7. Do not sad, do not your heart troubled God has many way be strong. As long as these the so-called priests and decon in our generation modern Eli and his children repent their sin and serving the Lord in their heart we will lose our value one by one. Think about Eli and his children. they lost the glory God, they fall under the hand of palistine. Shame after sahme they crowned now we are the same Eli and his children. Eli had no vision, dream and never worship God but he was priest his children were prostitiute thief and rude now look Deacons priests they have girlfiend they stole church money for personal use they not fear God. In X church(minneapolis) almost 2 years ago after they stole and use for personal use 17,000 $ they said the thief stole the money by breaking the window church; first of all how can 17000 $ sombody kept in the Church? Wake up, through prayer, kneedown and fasting we can remove all things.

Comments are closed.

Gologota
Previous Story

‹‹ጎልጎታ››፡- ከዚህ የሚበልጥ ፍቅር . . . !!!

Next Story

“አንተ የኔ ጀግና ነህ፡፡ ብትሞትም በእውነትህ ኮርተህ ሙት!” ሰርካለም ፋሲል

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop