የኢሳት 3ኛ አመት ክብረ-በዓል የሙስሊሞች ብቻ ነው እንዴ? ከ ልጅ ተክሌ

ስለክብረ-በአሉ እንግዶች፤ ስለመንግስትና ሀይማኖት መለያየት፤

ከ ተከለማርያም ሳህለማርያም

1-     ጽሁፍ ካላበሳጨ ወይ ካላስጨበጨበ አይመቸኝም። ላለፉት ጥቂት ሳምንታት የሚያበሳጭ ወይ የሚያስጨበጭብ ርእስ ስጠብቅ ሳልጽፍ ቆየሁ። የኢትዮጵያውያን፤ በተለይም የአማርኛ ተናጋሪ፤ ኢትዮጵያዊያን ከቤንሻንጉል መባረር በራሱ በቂ አናዳጅና አሳዛኝ ክስተት በመሆኑ፤ እንዲሁም ሌሎች ስለጻፉበት እሱ ላይ ብዙ አልደክምም። ስለዚህ ሌላ አናዳጅ ርእስ ናፈቅኩ። እነሆ ባያናድድም፤ ምን ነካቸው የሚያስብል ርእስ ከኢሳት አገኘሁ።

2-    ባለፈው ሰኞ፤ ከአድካሚው ውሎዬ እረፍት ለመውሰድ ወደኢሳት ድረ-ገጽ አመራሁ። የደንቡን አድርሼ ከኢሳት ድረገጽ ወጥቼ ለመሄድ ጣቴን ጠቅ ለማድረቅ ስንቀለቀል፤ በአይኔ የቀኝ ጠርዝ፤ በኢሳት ድረገጽ የግራ ማእዘን ላይ፤ ስድስት ሰባት ወንዶች የተደረዱበት ምስል አየሁና ተመለስኩኝ። አንዳንዶቹ የተለመዱ ፊቶች ናቸው። “ሲሳይ አጌና፤ ታማኝ በየነ፤ ሻምበል በላይነህ፤ ሄኖክ የሺጥላ …”። ሌሎቹ ግን በቃለምልልስ ካልሆነ በስተቀር፤ ከኢሳት ጋር በተያያዘ ለሚደረግ ዝግጅት አዳዲስ ናቸው። የኢሳት ሶስተኛ አመት ዝግጅትን ለማድመቅ የተመረጡ እንግዶች ናቸው። የሚያበሳጭም ባይሆን፤ እነሆ የሚያወያየው ርእስ የነዚህ ሰዎች ለእንግድነት መመረጥ ነው።

3-    ከኤፕሪል 13 እስከ ሜይ 26 የኢሳት 3ኛ አመት ክብረበዓል በተለያዩ ከተሞች ይካሄዳል። ነጂብ ሞሀመድ፤ ከታማኝ በየነና ሄኖክ የሺጥላ ጋር ቅዳሜ ሎስ አንጀለስ ይገኛል። እሁድ እዚያው ሳንዲየጎ ይጓዛሉ። እነዚሁ ሰዎች።ታማኝ በየነና ሻምበል በላይነህ ካሊድ ኦማርን ይዘው እሁድ ኤፕሪል 20 ሳን ሆዜ ይገኛሉ። ታማኝ በበነጋው እሁድ ኤፕሪል 21 መንሱር ኑርን ይዞ ሲያትል ይታያል። ነጂብና ታማኝ እንደገና እሁድ ኤፕሪል 28 ናሽቪል፤ ቴነሲ ይገኛሉ። ጃክሰንቪል ፍሎሪዳ ታማኝና ሻምበል ሜይ 18 ይገኛሉ። በስድስት ከተሞች በሚካሄዱ የኢሳት ዝግጅቶች ላይ አምስት የሙስሊም የሀይማኖት መሪዎች የመጋበዙ አመንክዮ ትንሽ ግራ አጋብቶኛል? በኔ አስተያየት፤ ኢሳት የሁሉም ኢትዮጵያውያን ከሆነ፤ ነውም፤ በኢሳት ሶስተኛ አመት ዝግጅቶች ላይ ከስድስቱ ከተሞች ውስጥ በአምስቱ የሙስሊም ሀይማኖት መሪዎች ዋንኛ ተጋባዥ እንግዶች መሆናቸው ብልሀት ያነሰውና ያልተጠና ነው። ይሄ አካሄድ ያለውን ፖለቲካዊ አንድምታና የሚያስተላልፈውን መልእክት የኢሳት አስተዳደር የተረዳው አልመሰለኝም።

4-    ሙስሊም ኢትዮጵያዊያን፤ በተለይም በአገር ቤት ያሉቱ የሚያደርጉትን ሰላማዊና በሳል ትግል ብደግፍም፤ የኢሳት 3ኛ አመት ዝግጅት ግን ሀይማኖታዊ አንድምታ በሚኖረው መልኩ መሆኑ ትክክል አይመስለኝም። ምክንያቱም ኢትዮጵያዊያን ዜግነትን ሳይሆን ሀይማኖትን መሰረት አድርገው እንዲደራጁ የማበረታታት ተጽእኖ ያሳድራልና።ሙስሊሞች  ባንድ በኩል ሙስሊሞች ለመብታቸው መታገላቸው የሚደገፍ፤ የሚያስቀና፤ የሚኮረጅ ነው። ሙስሊሞችም ይሁኑ ሌሎች በሀይማኖት ዙሪያ የተደራጁ ሀይሎች በኢትዮጵያ ውስጥ እንደአንድ ፖለቲካዊ ጎራ ወይም ቡድን ይታዩ፤ ወይንም እንደ አንድ ፖለቲካዊ ቡድን (Political Block) ሆነው እንዲወጡ እናበረታታቸው ወይንም እውቅና እንስጣቸው የሚለውን ሀሳብ በጽኑ እቃወመዋለሁ። እንደዚያ ብለው የሚያስቡ ሙስሊሞችም ሌሎች ኢትዮጵያዊያንም ሊኖሩ ይችላሉ። ኢሳት ግን ሙስሊሞችንም ይሁን ማናቸውንም የሀይማኖት ድርጅት ፖለቲካዊ ሀይል አድርጎ በሚያወጣ ጉዞ ውስጥ አባል መሆን የለበትም ብዬ አምናለሁ። ዜግነትን መሰረት አድርጎ የሚንቀሳቀስ እንደኢሳት ያለና ብዙዎቻችን በሀይማኖታችን ሳይሆን በዜግነታችን የተከተልነው ተቋም አንዱ ላይ አይደለም፤ ሁለቱም ላይ አይደለም፤ አምስት ዝግጅቶች ላይ የሙስሊም ሀይማኖት መሪዎችን ነጥሎ መጋበዙ ምን ማለት እንደሆነ አልገባኝም።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የሙስና ምርመራ እየተወሳሰበ ነው! "መበላላት እንዳይጀመር ስጋት አለ"

5-    አንዳንድ በጓዳ ብቻ የምንላቸውን ነገሮች በጨዋ ደንብና በሰለጠነ መንገድ እስከሆነ ድረስ በአደባባይም መነጋገር አለብን። ብዙዎቻችን በኢሳትም በኩል ይሁን በሌላ መስመር የሙስሊሞቹን ትግል ብንደግፈም፤ ድጋፋችን የሚቀጥለው ግን የኛን ብሄራዊ የጋራ ትግል እስካገዘና፤ በመጨረሻ እንደ ሀይማኖት ቡድን የሚያደርጉት ትግላቸው በኛ የጋራ ጥቅም ላይ ችግር እስካልጋረጠ ድረስ ነው። የሙስሊሙ አንድ ወጥ ፖለቲካዊ ሀይል ሆኖ መውጣት፤ ሀይማኖታችንን ሳይሆን ዜግነትን ብቻ መሰረት አድርገን ለምንንቀሳቀስ ሀይሎች ጠንቅ ነው። በተለያየ ሀይማኖት ተከታዮች መካከል ያለውን አለመተማመንና ጥርጣሬም ያባብሳል። በስድስት ከተሞች ከሚካሄዱ ስድስት የኢሳት 3ኛ አመት ልደት ዝግጅቶች ላይ በአምስቱ ላይ፤ ኢሳት ሙስሊሞችን ብቻ እንግዶች አድርጎ መጋበዙ የኢሳትንም ጥቅም በሀይማኖቶች መካከል ያለውን ጥርጣሬና ፍራቻም ከግምት ያስገባ አይደለም።

6-    የሙስሊሞቹን ትግል ስንደግፍና ከሙስሊሞቹ ጎን ስንቆም፤ ሀይማኖትና መንግስት የተለያዩ ናቸው፤ መንግስት Secular ይሁን፤ የሚለውን መሰረታዊ የፖለቲካ መርህ አምነንበት፤ የመንግስትን ጣልቃገብነት በኦርቶዶክሱም ሆነ በእስልምናው ሀይማኖት ስለቀመስነው ነው እንጂ፤ የሙስሊሞች አንድ ፖለቲካዊ ሀይል ሆኖ መውጣትን ተቀብለነው አይመስለኝም። መንግስት በማናቸውም ሀይማኖቶች ጉዳይ ገብቶ መፈትፈት የለበትም ከሚለው መሰረታዊ ሁላችንንም ከሚያስማማ የሰለጠነ ሀሳብ በመነሳት ነው። እንጂ ሙስሊሞች ተደራጅተው፤ አንድ የፖለቲካ ሀይል እንዲሆኑ የማድረግ ፖለቲካዊና አገራዊ ግዴታ አለብን ከሚል የሀላፊነት ስሜት በመነሳት አይደለም የሙስሊሙን ትግል የምንደግፈው።

7-    እንግዲህ ጫፍ ጫፉን እንደሰማሁት ከሆነ፤ የኢትዮጵያ ተራማጆች መንግስትና ሀይማኖት ይለያዩ ሲሉ ትግል የጀመሩት ከዛሬ 50-60 አመታት በፊት ነበር። ያ ትግላቸው ተሳክቶ መንግስትና ሀይማኖት ካለፈው የ66 አብዮት ጀምሮ ተለያይተው ከርመውም ነበር። እነሆ ኢህአዴግ ስልጣን ከያዘ በሁዋላ፤ ላለፉት 20 ምናምን አመታት ደግሞ መልሶ ከሀይማኖት ተቋማት ጉያ አልወጣም ብሏል። አሁንም መንግስትና ሀይማኖት ይለያዩ፤ መንግስት በሙስሊሞች ጉዳይ ጣልቃ አይግባ ስንል ያ ብዙ ወጣት ኢትዮጵያውያን የሞቱለት መርህ ይከበር ማለታችን ነው። መንግስት በኦርቶዶክሱም  ይሁን በሙስሊሙ፤ በመጅሊስም ይሁን በሲኖዶስ፤ ጣልቃ አይግባ ማለታችን ነው። በሙስሊሙም አይግባ ስንል፤ መንግስትና ሀይማኖት አይለያዩ ማለታችን ነው እንጂ ሙስሊሞች ወይም የማናቸውም ሀይማኖት ተከታዮች ፖለቲካዊ ሀይል ሁነው ይውጡ ማለታችን አይደለም።

8-    ይሄ የአምስቶ ከተሞች የሙስሊም መሪዎች ብቻ እንግዶች ሆነው የሚገኙበት አካሄድ ግን፤ ሙስሊሞች ተጽአኖ መፍጥር የሚችሉ አንድ ትልቅ የፖለቲካ ቡድኖች አድርጎ የመፍጠር አዝማሚያ የያዘ ነው። ያ አንደኛ መንግስትና ሀይማኖት ይለያዩ የሚለውን መርህ ይሽራል፤ ምክንያቱም ሀይማኖት በመንግስት ጣልቃ እንዲገባ ሊያደርግ ይችላልና። ሁለተኛ፤ ያንን ሚዛናዊ የሚያደርግ ወይም የሚፎካከር ጠንካራ የኦርቶዶክስም ይሁን የፕሮቴስታንት ድርጅት በሌለበት ሁኔታ፤ በኢትዮጵያ ውስጥ የሙስሊሞች ብቻ ሀይማኖትን መሰረት ያደረገ ጠናካራ የፖለቲካ ጎራ ሆኖ መውጣት ለኢትዮጵያ አደጋ ይጋብዛል። ኢሳትም፤ በሙስሊሞች ላይ የሚደርሰውን በደልና ግፍ ከመዘገብና ከማጋለጥ አልፎ፤ አስተዳደሩ ሙስሊሞችን ብቻ የክብር እንግዳ አድርጎ ወደመጋበዝ ሲያመራ ማንም ህጻን ሊያደርገው የማይሳነውን ጥንቃቄ ማድረግ አለበት።መንገስት ሴኩላር ይሁን ስንል፤ ይሄንን መንግስት ለመጣል የምፈልግ ሀይሎችም ሴኪውላር መሆን አለብን። እንጂ፤ የምንሰራው ስራ በሀይማኖታዊ አንድምታ እንዲተረጎም አድርገን መሆን የለበትም።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ኢትዮጵያየአባይወንዝባለቤትናት? (ኪዳኔ ዓለማየሁ)

9-    የኢሳት ሶስተኛ አመት ክብረበኣል ስግጅቶች ላይ ከስድስቱ ከተሞች በአምስቱ የተጋበዙት፤ ከታወቁቱ መደበኛ እንግዶች በስተቀር፤ በአትሌትነት፤ በሯጭነት፤ በሙዚቀኛነት፤ በደራሲነት፤ የማንንም ሀይማኖት በማይወክል በፖለቲካ መሪነት አይደለም የተጋበዙት። በጎበዝ የሀይማኖት መሪነታቸው የምናውቃቸው ሙስሊሞች ከሚኖሩበት ከተማ ውጪ በክብር እንግድነት ኢሳትን ወክለው መጋበዛቸው ብዙዎችን ግራ ሊያጋባ፤ ሊያሸሽም ይችላል። እነዚህን ሰዎች በመጋበዝ ልናመጣ ያሰብነው ትርፍ፤ በግልጽ ላንሰፍረው የማንችለው ትልቅ ኪሳራ እንደሚያመጣብን፤ አደገኛ አካሄድ እንደሆነም አላስተዋልንም የሚል ራእይ ተገልጾልኛል። ተደርጎ ቢሆን ኖሮ፤ የጋዜጠኛው ሳዲቅ መጋበዝ አይከነክንም። በጋዜጠኝነት ኢሳትን ሲረዳ የቆየ ሰው ነውና፤ ልክ ሲሳይ በአጋጣሚ ለኢሳት የሚሰራ ኦርቶዶክስ ክርስቲያን ጋዜጠኛ እንደሆነው ወይንም ታማኝ ለኢትዮጵያ የቆመ ኢሳት ውስጥ የሚሰራ ክርስቲያን እንደሆነው፤ ሳዲቅም በቅጥርም ባይሆን በፈቃደኝነት ለኢሳት የሚያገለግል ሀይማኖቱ እስልምና የሆነ ጋዜጠኛ ነው። አሁን የሆነው ግን ያ አይደለም።

10-   የነጂብና የኦማር፤ እንዲሁም የመንሱር ሁኔታ ግን ግራ ገብቶኛል። በግሌ ከነጂብም ይሁን ከማናቸውም ሙስሊሞች ጋር ምንም ችግር የለብኝም። ዞሮ ዞሮ ግን ነጂብና ካሊድ የሀይማኖት መሪ ናቸው። ነጂብ የፈርስት ሂጅራ ፋውንዴሽን። ከዚህ ቀደም የሚጋበዙትም ይሁን አሁን እነሱን የሚያጅቡት የኢሳት ሰዎች ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን ወክለው ነው የሚመጡት ከሚል ግምት ካልተነሳን፤ ወይንም እነታማኝና ሌሎች “ሜይንስትሪም” የኢትዮጵያ ፖለቲከኞች ኦርቶዶክሱን ይወክላሉ የሚል ያልተጻፈ ግምት ከሌለ በስተቀር፤ ታማኝም ይሁን ሻምበል፤ አበበ ገላውም ይሁኑ አበበ በለው ለኢሳት ዝግጅቶች የሚገኙት በዜግነት እንጂ በሀይማኖት አይደለም። ኦርቶዶክስን ወክለው አይደለም። ስለዚህ የሄኖክና የታማኝ፤ የሻምበልና የሲሳይ መገኘት የሙስሊም ሀይማኖት መሪዎችን መገኘት አያካክሰውም።

11-    ወዳጄ ታማኝ፤ ከዚህ ቀደም በስህተት ሙስሊሞቹን የካሰ መስሎት በልጅነቱ የክርስቲያኑ በኣል ሲከበር ስለሙስሊሞች በአል አለመከበር የተናገረው ንግግር በየዋህነት ቢታለፍም፤ በምንም መልኩ ግን ታማኝ እንደ ኢትዮጵያዊ እንጂ የክርስትና እምነት ተከታዮችን ወክሎ የሰነዘረው የይቅርታ ንግግር አይመስለኝም። እኔና ታማኝ ኦርቶዶክሶች ብንሆንም ኦርቶዶክሶችን አንወክልም። እኔ እስከማውቀው ድረስ፤ እነ ነጂብ ትናንትም ዛሬም ከኢሳትም ጋር ያገናኛቸው የሀይማኖት መሪዎች መሆናቸው ነው። የሀይማኖት መሪዎች ከጋበዝን ደግሞ ቢመጡም ባይመጡም የኦርቶዶክሱንም የፕሮቴስታንቱንም፤ የይሁዲውንም፤ የካቶሊኩንም ነው እንጂ፤ በምን መስፈርት ነው የሙስሊሞቹን ብቻ የምንጋብዘው? ይሄ አደገኛና መታረም ያለበት አካሄድ ነው።

12-   እንደምረዳው፤ እንደሚመስለኝም፤ ኢሳት የሙስሊሞቹን እንቅስቃሴ ሌት ተቀን የሚዘግበው፤ በሙስሊም ኢትዮጵያዊያን ላይ በመንግስት የሚፈጸመው ኢፍትሀዊነት ሁሉንም ኢትዮጵያዊና የሰው ልጅ ስለሚመለከት ነው እንጂ፤ ብዙዎች የነቁም ያልነቁም የሙስሊሙን እንቅቃሴና አካሄድ በጥርጣሬ የሚመለከቱ ስጋት የገባቸው ኢትዮጵያዊያን የሉም ማለት አይደለም። ያንን እኔ ራሴ ሌላው ቢቀር ኢሳት ውስጥ በምሰራበት ወቅት ከሚደርሱን የስልክና የኢሜል መልእክቶች እረዳለሁ። በዚህ ሁኔታ ውስጥ እንደ ኢሳት ያለ ለሁሉም ኢትጵያዊያን በእኩልነትና ፍትሀዊነት ላገለግል ቆሜያለሁ የሚል ተቋም፤ ዝግጅቶችን ሲያዘጋጅ በክብር እንግድነት ስለሚጋብዛቸው ሰዎች ማንነትና በህዝብ ዘንድ ሰለሚፈጥሩት ስሜት ጥንቃቄ ማድረግ አለበት። ከስድስት ዝግጅቶች በአምስቱ ላይ እነ ነጂብን ሲጋብዝ ሊፈጥር የሚችለውን አንድምታ፤ ሊያሸሽ የሚችለውን ህዝብ ማሰብ አለበት። ኢሳት ደግሞ የሙስሊሞችና የኦርቶዶክሰቶች ብቻ ሳይሆን፤ ለአገር ያላቸው ተቆርቋሪነት ጎዶሎ ቢሆንም እንኳን፤ የጴንጤዎችም ጭምር ነው። ወይም ነው ብለን ነው ማሰብ ያለብን። ዝግቶቹ በተለያየ አጋጣሚ የተዘጋጁ ቢሆኑ አይገርምም። ነገር ግን ሆን ተብሎ ባንድ ላይ ታስቦበት ይሄንን ቅርጽና አንድምታ እንዲይዝ የተዘጋጀ ይመስላል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የመጨረሻው ደወል !! ( አሥራደው ከካናዳ )

13-   መቼም በነካ እጄ ለመጨመር ያህል፤ ከላይ እንዳልኩት፤ መንገስት ሴኩላር ይሁን ስንል፤ ይሄንን መንግስት ለመጣል የምፈልግ ሀይሎችም ሴኪውላር መሆን አለብን ማለቴ ነው። እንጂ፤ የምንሰራው ስራ በሀይማኖታዊ አንድምታ እንዲተረጎም አድርገን መሆን የለበትም። በመሰረቱ የሀይማኖት ስራ በሰውና በእግዚአብሄር መካከል ያለውን ግንኙነት የሚመለከት ነው፤ የፖለቲካ ዓላማ ደግሞ በሰውና በሰው መካከል ያለውን ግንኙነት የሚመለከት ነው። የተለያዩ ሀይማኖት ተከታዮች ባሉባት አገር፤ ሀይማኖት የሰውና የሰውን ጉዳይ እንዲዳኝ መጋበዝ የለብንም። ሀይማኖት በሰውና በሰው መካከል ያለውን ግንኙነት የሚዳኘው ፖለቲካ ላይ ተጽእኖ ማሰደር ሲጀምር ነው። ተጽእኖ አሳዳሪውን ሀይማኖት (በኛ አገር፤ እስልምናን ሊሆን ይችላል) የሚገዳደር ወይም የሚያርቅ በሌላ ሀይማኖት ዙሪያ የተደራጀ ሀይል (ምሳሌ ኦርቶዶክስ ወይንም ፕሮቴስታንት) ከሌለ፤ የዚያ ተጽእኖ ፈጣሪ ሀይማኖት (እስልምና) አንድ ወጥ በሀይማኖት ዙሪያ የተሰባሰበ ሀይል ወይም ቡድን ሆኖ መውጣት ለሁላቸንም አደጋ ነው። ኢሳት ያንን አደጋ መከላከል እንጂ ማበረታተት የለበትም።

14-  መቼም የሆነ ሆኗል፤ ድስት ተጥዷል፤ ጠላም ተጠምቋል፤ ጠጅም ተጥሏልና፤ የተጋበዙት ሰዎች ይሰረዙ፤ ወይንም አቡነ ፊሊጶስን ፈልጋችሁ ደባልቁ ብለን አንጮህም። ይሁን እንጂ፤ ለወደፊቱ ይሄ እንዳይደገም ጥንቃቄ ያስፈልጋል። ያለበለዚያ የምንቆጣም እንኖራለን።

15-  ለነገሩ፤ እሁን እነ ሌንጮ ለታ፤ እነ ዲማ ነጎ፤ ይሄን የመሰለ ፖለቲካዊ ጮማ አዋጅ ይዘው አንድነታችን ደጅ ላይ ቆመው፤ እጣ ፈንታችን የሚወሰነው ከኢትዮጵያዊነት ታዛ ስር ነው እያሉ አዋጅ ሲነግሩ፤ ሲሆን ሲሆን ለቀጣዮቹ ወራት እነሱን ብቻ፤ ካለበለዚያም ከሌሎች ጋር እየቀየጥን የአገራችንን ነገር መምከር ነበር እንጂ፤ ሀይማኖታዊ መሪዎች ላይ ማተኮር አልነበረብንም። ለወደፊቱ ጥንቃቄ ይደረግ። የኢሳት አስተዳደርን ለዛሬ ምረነዋል። ለወደፊቱ ይታረም።

እኛው ነን። ታሰበ፤ ተጻፈም፤ በአገረ-ካናዳ፤ ቶሮንቶ፤ ሚያዚያ፤ 2005/2013

 

 

22 Comments

  1. Semam Lij Tekele, First of all thank you for the article.

    Why do you guys confuse and use “Amharic Speaking” instead of “Ethinic Amhara”. This thinh has to stop. You guys are killing the Ethinic Amharas morethan TPLF did by denying their Ethinic Idenity. STOP distorting it. All Amharic speaking are not Amharas. TPLF is deporing not all “Amhara speaking” Ethiopian. TPLF/eprdf is specifically targeting Ethinic Amharas.

    Please stop distorting the identity of Ethinic Amharas. you guys are writing a document that will be kept for long. So what happened on Ethinic Amharas has to be written without distortion.

    I say stop it.

  2. Gira yagaba yeneberew ante Esat wist mesratih naw!!! ante mesrat yalebih Eri-Tv neber!!! atachberbir ye negelle shaabia nah !!!…arios!!!

  3. your point is useless why you consenterat on thier religion backgrond your thought completely against esat that is clear peopels not jujed because of thier religion or another thing they are ethiopian get lost

  4. Lege Tekle,
    your view is pointless. you had been part of fund rising. no one complain about you and others are all christians. what is your problem? i think you not happy because you will not be their (kenat) . Those people are more influential than you are. they have thousands followers which is supporting ESAT. wether you happy or not this is right move for ESAT unity. i have one Q for you those people activity in ESAT are journalist or artist and religion leaders. who are you? to listen what you say.

  5. Lij Tekle’s concern is valid and far sighted, but it could have done it with in them selves since he is one of ESAT staff.

    Raza

  6. Liking tekile.ye liking timhirt Viet hideh remarkable.me abundant behuala mekefafelign ansemam.hagerachin Ethiopian Muslim enable Christian tebabiren were democracy enqeyiratalen.yihim. yemihonew lehulum ethiopiawi equl. Mebit. Bemesitet new.

  7. I think the idea behind inviting the likes of Nejib is so that they explain about the Ethiopian Muslim’s question to the audience. The biggest fear for Ethiopia today is TPLF using it’s last card of survival of dividing Ethiopians across religious lions. Thus there shouldn’t be any information gap as to the Muslim’s movement.

    I share your view had there not been the ongoing protests and still ESAT were to incline towards the Muslims.

    Ps: you could already have raised the issue to your colleagues in ESAT instead of bringing it up here.

  8. It seems to be you are desperately seeking fame at the price of deported & in concentration camps contained suffering amhara people. You said on ESAT yehu weg weekly programm, those uprooted people from benishangul are amharic speaking people but not amharas. Denying ethnic cleansing, deporting or displacing, robbing property of ordinary people because of their ethnic origin is crime against humanity. Now you are penalysing muslim activist who fighting for freedom. Shame on you! I wish i will never see you on ESAT again. My recommendation to you ETV is a good platform for you. you will feel better & solomon tekalegne & mimi sibeatu will be wellcoming you. Shame on you!

  9. Mr. Tekele your Articles is pointless,why you did spend your time in such crab. we do not excepect such cheap thinking from you. you better think wisely before you write anything on public since you are one of Media person. we love Esat so do not try to make us confused.
    I will look forward you in a better and useful Articles.

  10. LEJ TEKLU, NEGERUN KE ENE SISAY GAR LEMEWEYAET AKMU SELELELEH
    ANBABIN MATERAMES MERETEH. AY LETAWEK BAYNET.

  11. lej Tekle minew dehna sew alineberkim? min nekah betam aznalehu kante aytebekim ene c/t negn gin alikawemim lemin beahun seat silemebt yemitagelut enesu nachew menigisitim yemifeligew lik enidante lemekefafel new silezih yhe enidayror enesu lehizib akuwamachewn biyasredu minu lay new tifatu? Tekle akuwamih tenshadede minew?

  12. I just want to write about tekele my expretion (sera yatach molekese kobuan qeda tesfalech ) Esat our Ethiopian voice long live

  13. teklu endemimeslegn sewochu yetegabezut wektu muslimoch be woyane lay tekuawmo eyaregubet bale gza new, keza befit muslimochen Esat lay bezum ayeche alawkem ,seletefenakelut ye amara bher tewelajoch beya seatu be Esat lay yemensemawum, ahun eyederesebachew yale cheger selehona newe, yaneta akahed yemitekmew woyanen becha yemeslegnal, Esat west mesrateh degmo yasazenal, egan ortodoxoch becha lemin Esat west seru belen asben anwkem, serachewen becha newena yeminayew,

    • በተለያዩ አከፋፋይ መንገዶች ሃይማኖትንም ጨመሮ በወያኔ መሰሪ ስራ የተራራቀዉን ህብረተሰብ ለማቀራረብና ለኢሳትም የገንዘብ ገቢ ለማስገኘት በማሰብ በየቦታዉ ያሉት የድጋፍ አካሎች ሌት ከቀን በሚሯሯጡበት ሰዓት ስህተትም ከነበረ ባለዉ ቀረቤታ ፕሮግራሙ ከመዉጣቱ በፊት እንዲስተካከል ማድረግ ከዘገየም ለወደፊቱ እንዲታሰብበት ማሳመን ሲችል በዚህ መንገድ መዉጣቱ ብዙ ጥያቄዎችን የሚአስከትል ነዉ። አወቀዉም አላወቀዉም እየተደረገ ለአለዉ ጥረት ጥሩ አስተዋጽኦ የለዉም። አልታየዉም ብሎ መናገር አይቻልም። የአልገባን ነገር ግን ተክሌን ለዚህ ጽሁፍ ያነሳሳዉ ምን እንደሆነ ነዉ። ምንም ይሁን ምንም ጤነኛ አይደለምና ለሁላችንም ልቦና ይስጠን።ዋናዉ ጠላታችን ላይ እንድናተኩር፡፡

  14. በተለያዩ አከፋፋይ መንገዶች ሃይማኖትንም ጨመሮ በወያኔ መሰሪ ስራ የተራራቀዉን ህብረተሰብ ለማቀራረብና ለኢሳትም የገንዘብ ገቢ ለማስገኘት በማሰብ በየቦታዉ ያሉት የድጋፍ አካሎች ሌት ከቀን በሚሯሯጡበት ሰዓት ስህተትም ከነበረ ባለዉ ቀረቤታ ፕሮግራሙ ከመዉጣቱ በፊት እንዲስተካከል ማድረግ ከዘገየም ለወደፊቱ እንዲታሰብበት ማሳመን ሲችል በዚህ መንገድ መዉጣቱ ብዙ ጥያቄዎችን የሚአስከትል ነዉ። አወቀዉም አላወቀዉም እየተደረገ ለአለዉ ጥረት ጥሩ አስተዋጽኦ የለዉም። አልታየዉም ብሎ መናገር አይቻልም። የአልገባን ነገር ግን ተክሌን ለዚህ ጽሁፍ ያነሳሳዉ ምን እንደሆነ ነዉ። ምንም ይሁን ምንም ጤነኛ አይደለምና ለሁላችንም ልቦና ይስጠን።ዋናዉ ጠላታችን ላይ እንድናተኩር፡፡

  15. ሀሳቡ ትክክል ነው ወያኔ 3ወይም 4 ጥያቄዎቻችውን በትክክል ቢመልስ በቡድን የሚያደርጉት ትግል መቆሙ አይቀርም ብለን እናስብ።ግን ወያኔኢህአድግ ጥያቄውን ለመመለስ ዴሞክሪያሳዊ ባህሪ ስለሌለው እንቅስቃሴው ሊቀጥል ይችል ይሆናል።
    እንደአረቡ እስፕሪግ አብዪት Back የሚያደርጉ እስላማዊ ፓርቲዎች ባለመኖራቸው እንቅስቃሴው የኢትዩጵያ ህዝብ ትግል አካል እንደሚሆን ብንጠብቅም ድንገቴ ክስተቶች እና የሀገራችን ታሪካዊ ጠላቶች ሙስሊም ወንድሞቻችን ባላለሙት መንገድ ሀገራችንን የሚበታትን ፖለቲካዊ አጀንዳ ሊሸከሙ ይችላል።ስለዚህም የሚስሊሙ ህብረተሰብ ጥያቄ ከኢትዬጵያ ህዝብ ጥያቄ ጋር በጋራ የሚመለስ ስለሆነ ከተወሰነ ሀይማኖታዊ ጥያቄዎች ወጥቶ ሀገራዊ አጀንዳ መያዝ ያስፈልጋል።በኔ ይሁንባችሁ እንዲህ ያለ ነገር አይደርስም ሊለን የሚፈልግ ካለ እሳት ከነደደ በሁላ ለማብሰያነት ብቻ እንደሚያገለግል የሚያስብ የዋህ ሰው ነው።
    የሙስሊሙን እንቅስቃሴ የምደግፈው ህገ መንግስታዊ መብታቸው ስለሆነ እንጂ በሰበቡ ታግለው ከወያኔ ቀንበር ነጻ እንዲያወጡኝ አይደለም።
    ከዚያም እንደወያኔው በደማችን የተገኘ ድል ነውና ሁሉም ነገር ይገባናል የሚለን የእስላምም ሆነ የክርስቲያን ሀይል ወይም ቡድን አንሻም።
    ወደ ግብዣው ልሂድና በአጋጣሚ እና በቅንነት ከሙስሊሙ ጐን ለመቆም የተደረገ እንደሚሆን አስባለሁ ሆኖም እንቅስቃሴው ብቸኛ የፖለቲካ ሀይል ሆኖ እንዲወጣ አውቆትም ሆነ ሳያውቅ የሚሰራ ቡድን እስላምም ሆነ ክርስቲያን ወይም ሌላ ከሚደርስበት ትችት ወይም ተቃውሞ ሊያመልጥ አይችልም። ጋባዥም ሆኑ ተጋባዥ በዚህ መንገድ ባይረዱትም ጸሃፊው ለወደፊቱም አስጠንቃቂ የሆነው ሀሳቡ ደግሜ ትክክል ነው እላለሁ።

  16. Temple, it is is a good article. You deserve appreciation for bringing forth an idea whichnmightnbe harbor end by many other Ethiopians.however, I think you have missed the point. First and foremost Your talk about “Muslim political force”is no different than woyane’s scare mongering tactics. I hope you haven’t fallen victim for that. Otherwise, how on earth do you consider the mere invitation of a group which represents the only and active opposition to the regime as such. As far as I am concerned the action by ESAT is justified for the following reasons:
    1 it should be remembered that Muslim were passive participants in their nations affairs for ages and the current issue has brought them to the front and medias like ESATshould be able to support this noble trend.
    2. Like it or not, Muslims movements is the only viable movement trully confronting the regime which we consider as tyrannical. ESAT as public media has a responsibility to support such movement.
    3. This is win win situation for both. ESAT THROUGH ITS DEDICATED WORK HAS BECOME THE VOICE OF THE MILLIONS OF MUSLIMS, SO, IT WILLBE APPROPRIATE FOR ESAT take advantage of the new block of potential supporters to maintain and strengthen its work.
    4. My brother, the presence of Orthodox Christians, be it as a leader or other wise is a default phenomenon in any ethiopian rlelated activity. I believe their presence on a poster to announce the occassion wouldn’t make much differerence. but, the muslims, has the potential to draw more and new ethiopians to the occassion.
    5. I believe Muslim leaders have correctly understood that the major goal of the regime is to saw animosity b/n the two major religion followers. Thus they are looking for a forum to foil such a heinous plan by making clear the goal of the movement to the larger non Muslim audience. We need to say KUDOS to ESAT for playing their role as a public media.

    I could have gone further, but, I will stop here for the moment and once more, I would like to remind you my brother, please think win win .

  17. Tekle, yante neger “aweqesh aweqesh siluat yeqes mist metsehaf atebech” yemilewen yastawesengal. It is ESAT that gave you unearned prominence. Live and learn, ESAT Board.

    Whyd do you get a joy out of creating controversy? Do not you care at all about the harm that you cause with your baseless allegations? Instead of embracing those who are doing more than their fair share fo rour freedom. you question their participation? Have you ever questioned when the majority of the panelists are Christian?

    You want to be active contriutor to the struggle and also want and ask for to be recognized for your contribution. But it is very common for you to write things that either do not make sense or that harm more than help the cause you claim to stand four.

    To think that you were itching to find something that would make one angry by itself should serve as a warning for you and people around you. It is not normal. Who eagerly looks for something that is infuriating?

    May God give you a little more wisdom!

  18. wow me like Leg Takela point Ebakatu politic ena Haymanot enlaey yalezy ke WEYANE men telayen 6 Muslim Enam algbagem Esat?

  19. ኬንያ እያለ ተክሌ አዕምሮውን ታሟል ሲባል ሰምቼ አዝኜ ነበረ:: ድኖ ኢሳት ላይ ሳየው ድስ አለኝ:: ዛሬ ከኢሳት ለቀቀ መሰለኝ መዘባረቅ ጀመረ:: ኢሳት ለሰዎች ሁሉ ካልታገለ ዋጋ የለውም ብሎ የሚፅፍ ሰው እንዴት ጴንጤዎች በጠቅላላ ላገር ያላቸው አመለካከት የተንሸዋረረ ነው ብሎ ይፅፋል? እብደቱ ተመልሶ ካልጀማመረው በስተቀር ይህን አይፅፍም::

  20. I respect Tekeles out spokennes but this one is diffrent. Defenetlly he crosse the line. I think, you just write becouse you have to write. You do not have to unless you have a substanss issue and take a rest before you said it. I hope you will take it back if you are in your mind.

  21. Hi Tekle,

    I like your article. We know EPRDF is Ethiopia’s enemy. But muslims will be more dangerous to Ethiopia if they get the chance. U can see what is happening in Afganistan, Iraq, Syria, Libya …. So, ESAT, please stop playing with fire. Stop creating radicals. No need of giving special attention to the muslims. They must be treated as usual and equally like all Ethiopians.

Comments are closed.

Share