July 23, 2024
13 mins read

ትግሉ  አፋፍ  ሲደርስ ፣ የሚፈጠሩ ውጥ-እንቅጦች እና አዙሪቶች !!

451628420 491773623409845 242423440167739044 n 1ታሪካችን ወደኋላ ብለን ስናማትር አነ ኢሕአፖ ፣ ኢዲዩ  እና ወ.ዘ.ተ. ፖርቲዎች ትግላቸውን እያጧጧፉ ወደ መንበረ እርካቡ እያኮበኮቡ ባሉበት ወቅት እነዚህን ፖርቲዎች ይመሩ የነበሩ መሪዎች ከመጋረጃ ጀርባ ከመንግስት ጋር ወይም ከፖርቲዎቹ ተቀናቃኞቻቸው ጋር ውስጥ ለውስጥ አየተሻጠሩ ፣ እየተሞዳሞዱ እና ከድል በኋላ ስልጣኑን እንቀማለን በሚል የስልጣን ጥሜት በሕዝብ ቅቡልነት ያላቸውን ፖርቲ መሪዎች አስበልተዋል እንዲሁም የመሪዎችም መመታት “ መሪው የተመታ ጦር እንደሚበረግግ በግ ነውና“  ትግላቸው ከግብ ሳይደርስ ፣ ብዙ ታጋዮች መስዋት ሁነው ፣ እርካበ ሥልጣኑ በማይገባው አካል ገብቶ ሕዝብ እንደ ሕዝብ ያየው እና ያሳለፈው ስቃይ የቅርብ ዓመታት ታሪክ እና በቁጭት የሚታወስ ክስተት ነው።

ለምሳሌ ኢዲዩ ( የኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ህብረት) የደርግን መንግስት ሲፋለም የነበረ ሲሆን በነ ጄነራል ነጋ ተገኝ ፣ በራስ አዳነ ስዮም ፣ ራስ መንገሻ ስዩም ፣ አጣናው ዋሴ እና ወ.ዘ.ተ. እየተመራ በሕዝብ ቅቡልነት አግኝቶ ደርግን አንቀጥቅጦት ነበር። ነገር ግን ኢዲዮ በአሻጥር ከኢሕአፖ መሪዎች ጋር ፍትጊያ ውስጥ እንዲገባ የቀድሞው ወያኔ ( የአሁኑ ህወሃት) ሰርጎ ገቦች ማለትም እንደ ራስ መንገሻ ስዩም ባሉ አቀባባሪነት ራስ አዳነ ስዩምን በማስመታት እና በመግደል የኢዲዩ ትግል ጫፍ ሳይደርስ እንዲጨናገፍ ሁኗል።

የኢሕአፓ ትግል በአብዛኛው የሕዝብ ድጋፍ አግኝቶ የነበረውን የበርሃ ትግሉን ወደኋላ ትቶ በከተማ “የነጭ ሽብር እና የቀይ ሽብር” የእርስ በርስ መገዳደል ሆን ተብሎ እና በሻጥር እንዲያተኩር እነ መኤሶን ፣ ህወሃት እና የደርግም እጅ ታክሎበት የኢሕአፖ የበረሃው የአሲንምባ ትግል እየተጨናገፈ በብሄር ጡዘት በሰከሩት እና አፍቅሮተ ህወሃት በነበራቸው በእነ በረከት ስምኦን ፣ አዲሱ ለገሰ ፣ ተፈራ ዋልዋ እና ወ.ዘ.ተ. እጅ በመግባቱ እና በመውደቁ በሚያሳዝን መልኩ ስፍር ቁጥር የሌለው ወጣት እረግፎ ትግሉ አፋፍ ሳይደርስ ሊኮላሽ ችሏል።

ወገኖቼ አንድ ሊታወቅ የሚገባው በኢሕአፖ ፣ በኢዲዩ እና በሌሎች አደረጃጀት ፖርቲወች ከ1966 ወዲህ በአሻጥር ፣ በደባ እና በእርስ በርስ ሽኩቻ “ የጦስ ደሮ” ሁነው የተሰውት የአማራ ልጆች ፣ ምሁራን እና አመራሮች እንጂ የሌላ ብሔር ተወላጆች እነ በረከት ስምኦን ፣ እነ እራስ መንገሻ ስዩም ፣ እነ አዲሱ ለገሰ እና መሰሎቹ አልነበሩም ይልቅኑ  እራሳቸውን  “ኢድህን” ምናምን ብለው በመሰየም ከህውሃት ጋር በመለጠፍ የአማራን ህዝብ አገላተዋል ፣ አስጨፍጭፈዋል እና ዐፅመ እርስ ቱን እነ ወልቃይትን ፣ ራያን ፣ መተክልን እና መሰሎችን አሳልፈው ለህውሃት አስረክበው ነበር። ባለፉት  ሃምሳ ዓመታት በአማራ ምድር የአማራ ነገድ ኖረ እንጂ በቀኝ አዙር ከመገዛት ውጭ ከእራሱ እትብተ ምድር የተወለዱ  ወይም የተፈጠሩ መሪዎች ኑረውት ወይም አፍርቶ አያውቅም  ።

የአማራ ሕዝብም “ከእትብቴ የወጡ አማራ ልጆቼ የአስተዳድረኝም” ብሎ አያውቅም ። በስመ አማራ የተሰባሰቡ የሌላ ብሔር ቅልቅሎች አፅመ እርስቱ ድረስ ወርደው በላዩ ላይ እየተሾሙ አስተዳደሩት ፣ መሩት ፣ ፍርደ ገምድል ሆኑበት፣ አሰሩት ፣ አንገላቱት ፣ ገደሉት እና ረግጠው አሰቃዩት  እንጂ።  ይህም የሆነው አንገት ማተቡ ላይ ያንጠለጠለው “የኢትዮጵያዊነት መርህ እና ፍቅር ይበልጥብኛል” ስለሚል እና “ስለሚያጎላድፈው እና ፈሪሃ እግዚአብሔርም” ስላለበት “እሺ ፣ ይሁን” ብሎ ከመገዛት ውጭ ሌላ አማራጭ ስላልነበረው ነበር።

አሁን ግን ኢትዮጵያዊነት “እንደ ወላጅ እና ልጅ” ግንኙነት እንዲሆን አማራውን እያስገደደው መጥቷል “ ዝንጀሮዋ መጀመሪያ መቀመጫየን” እንዳለችው “ልጅ ወላጅ ደህና ሲሆን ነውና” በሰላም ፣ በፍቅር እና በስርዓት ተኮትኩቶ የሚያድገው ፣ አማራውም “ መጀመሪያ እራስ ደህና” ብሎ ፣ “ኢትዮጵያ በእግዚአብሔር ፅጋ እና ድጋፍ ራሴ የሰራኋት” በመሆኗ “የትም አትሄድብኝም” ብሎ ለራሱ ደህንነት እና የመኖር ዋስትናውን ለማስጠበቅ ተነስቷል ፣ ማንም ከግዲህ በኋላ ምንም ሆነ ምን ከዓላማው የሚነቀንቀው እንደሌለ ሊሰመርበት ይገባል።

ይህን የማይናወጥ አቋሙን እና ውሳኔውን ወደተግባር ለመለወጥ ደግሞ እንደ ትላንትናው በስማ በለው ፣ በምስለኔ ፣ በጭቃ  ሹም ፣ በስመ አማራ ተብየዎች እና የእንግዲህ ልጆች እንዲመራ የሚደረገውን አካሄድ “እርሜ ነው” በማለት የአማራ ሕዝብ ወስኖ እና “ሆ” ብሎ ስለተነሳ ፣ ከራሱ አብራክ የወጡ ልጆች እንዲመሩት እና እንዲያስተዳድሩት ፋኖን እርካብ እና ልጓም አድርጎ እየተፋለመ ይገኛል።

እነዚህን መሰረታው መርሆዎች ፣  መስፈርቶች እና ነጥቦች መሰረት አድርጎ የአማራ ፋኖ መሪ የመሆን ወይም የግለሰቦች ወደ ስልጣን እርካቡ የመምጣት ጉዳይ ሳይሆን የሚከተሉት እንኳር ነጥቦች መሰረት እድርጎ ሊከወን ይገባል እንላለን  ፣ በአራቱ የአማራ ግዛት አፅመ እርስቶች ማለትም በጎጃም ፣ በሽዋ ፣ በጎንደር እና በወሎ ላይ የማያወላውል አቋም ያለው እና ለነዚህ አካባቢዎች የኢኮኖሚ ፣ የማህበራዊ እና የፖለቲካ ምህዳሮች መስፋት ፣ ማደግ ፣ ጥንካሬ እና ልዕልና ፀንቶ የሚታገል ፣

. አዲስአበባን ጨምሮ የወልቃይት የራያ እና ነባር የአማራ አፀመ እርስቶችን ወደባለቤቱ  የአማራ  ሕዝብ ይመለሱ ዘንድ የማያውላዳ አቋም ያለውና ይህን እውን ለማድረግ ፅኑ አቋም ያለው ፣

-የአራቱን አካባቢዎች ማለትም የሽዋ ፣ የወሎ ፣ የጎንደርን እና የጎጃምን ባህል ፣ ወግ ፣  ትብህል እና ቱፊት በውል ፣ በደንብ የሚያውቅ እና የኖሩበት ሊሆኑ የግድ ይላል ፣

– በፋኖ ትግል ምስረታ እና እንቅስቃሴ በፋና ወጊነት ከጅምሩ ጀምሮ ንቁ ተሳታፊ እና ከመስራቾቹ አንድ የሆነ፣

– የአማራ ህዝብ ሆነ  የአማራ ፋኖ ታጋዮች ከቀደም ጀምሮ ለአማራ ሕዝብ ነፃነት ፣  ሰብአዊ መብት መጠበቅ በመሪነት የተቀበሉት  እና ለዚህ  ዓላማ ከጅምሩ እና ከመነሻው ጀምሮ  መስዋዕት የከፈለ መሆኑን የሚያቁት እና ያረጋገጡለት ፣

– ለአማራ ሕዝብ ልእልና እና ሰላም ዱር ቤቴ ብሎ የገባና እራሱን አሳልፎ ለመስጠት የማይናወጥ እቋም ያለው ፣

– የአማራ ሕዝብ የስልጣን ባለቤት እንዲሆን የፀና እምነት እና አቋም ያለው ፣

– ከድርድር በፊት የአማራ ሕዝብ የስልጣን ባለቤት እንዲሆን የሚታገል እና በዚህ አቋሙ ሸብረክ የማይል፣

– ከዚህ በፊት በተቋቋሙ ፓርቲዎች ወይም ድርጅቶች መሪ ሆኖ ከሆነ እጩ  ተመራጩ  ባሳየው ለውጥ እና እምርታ አንቱነትን ያተረፈ እና በመሪነቱ ወቅት የመራው ፖርቲ ወይም ድርጅት ዓላማው ግብ እንዲመታ ያደረገ  መሆኑ በመስፈርትነት ሊታይ የግድ ይላል ፣

– መቸም  የእኛ ሃገር ትግል አንዱ በመሪነት የታጨ  ወይም የተሰየመ ከጎኑ ያለውን አጋር መሪ ስልጣኔን ይቀማኛል በሚል ስጋት ፣  መንግስቱ ኃይለማሪያም ኮለኔል አጥናፉ አባተን እና ኮለኔል ተፈሪ ባንቲን ፣  መለስ ዜናዊ ክንፈን እና መሰሎችን ፣  እነ አብይ ኢጅነር ስመኘውን ፣  ጀነራል አሳምነው ፅጌን እንደ በላቸው የዚህ አይነት የተደበቀ ማንነት የሌለው መሆኑ ሊረጋገጥ እና ማነነቱ ከግለ ታሪኩ ጋር ነጥሮ ወጥቶ ሊመረመር የግድ የሚል ይሆናል፣

የመሪነት መስፈርቶች ከትንሽ በጥቂቱ  እነዚህ ቢሆንም በአራቱ የአማራ ጠቅላይ ግዛቶች ያሉ መሪዎች ከላይ የተጠቀሰው የፖለቲካ ውጥንቅጥ ፣ ሻጥር ፣ ደባ እና ከመጋረጃ ጀርባ ከጠላት ጋር እና ከብልፅግና ጋር በጎንዮሽ በውጭ ሃገራት ግፉት በሚደረጉ ሻጥር አዘል የድርድር ክንውን ህሳቤ እና ሽረባዎች ሰለባ እንዳይሆኑ ከወዲሁ እንመክራለን።

 

ድል ለፋኖ

ከተዘራ አሰጉ ( ከምድረ እንግሊዝ)።

2 Comments

  1. እንዲህ ያለ ጊዜ ክቡር ታየ ደንዳ ክቡር ጁዋር መሃመድ፤ ክቡር በቴ ኡርጌሳ ክቡር ቀሲስ(ዶላር) በላይ ሰማዩን በእርግጫ ካልመታሁ የሚሉ ዛሬ ላይ ግማሹ ወደ ላይ ግማሹ ግንብ ውስጥ ግማሹ ከሩቅ ሁኖ ይዶልታል እንደው የጊዜ ነገር ይገርማል ይህ እሽክርክሪት ለአቶ ዳንኤል ክብረት ለአቶ ስዩም ተሾም ለወ/ሮ ቤተ ልሄም ታፈሰ(ምንም እንኳን ደቂቅ ቢሆኑም) ለአቶ ሽመልስ አብዲሳ ለአቶ አብይ መሃመድ፤ለአቶ አገኘሁ ተሻገር፤ ለው/ሮ አዳነ አቤቤ፤ለአቶ ይልቃል ከፍያለው፤አረጋ ከበደ፤በለጠ ሞላ፤ለአቶ ብርሃኑ ነጋ( ከአካዳሚክ ህይወት ስለተፋታ መጠሪያው አይሆንም ብዬ ነው) ይደረስ ይሆን? እንደው ለዚህ አንድ ሆዳቸው ብለው ነብስና ስጋቸውን ባያሰቃዩዋት። ህሊና ያለው ዜጋ ተሰብስቦ ታስሮ እነዚህ ዘራፊ የደም ነጋዴዎች ውጭ መቆየታቸው የባሰ ሊያመጣባቸው ነው እንጅ ለሌላ አይመስልም። ትግሬ እንደዛ ምድር ሰማዩ ጠቦት ዛሬ ላይ እንዲህ እንደተነፈሰ ባሉን ሁኖ ሲታይ ከዚህ ብዙ መማር ይገባ ነበር ሰው ነንና የትላንቱን ቶሎ እንረሳለን። የሆነ ቪዲዮ ላይ አዜብና ሰማኻል እንደ ባሌት ደናሽ ባንድ እግራቸው ሲሽከረከሩ አይቼ የተሸኘው መለስ ትዝ ብሎኝ አይኖቼ እንባን አቀረዘዙ ይህም ሰብአዊነት ስለተላበሰኝ ነው የሚያሳዝነው ወጣቶቹ መቃብሩ ላይ ሽንት መሽናት ከጀመሩ ቆዩ። አስከሬኑን አስወጥተው ወደ አደዋ እንዳይወስዱ በሱ ስርአት ብዙ የተጎዳ ስላለ በዛም አይመችም እናቱ ኤርትራ ናቸው ይባላል ኤርትራን የሰራቸው ስራ ቢያንስ በ7 ትውልድ አይረሳም አንዳንዶቹ ከዚህ ሁሉ ውዝግብ አስከሬኑ ተቃጥሎ አየር ላይ እንዲበተን ይመክራሉ መበተኛውም የትም ሃገር እንዳይደርስ ፓስፊክ ውቅያኖስ መሃከሉ ላይ ቢሆን ይመረጣል ምድርም ሆነ ውሃ ላይ ካረፈም ጠንቅ ነው የበኩላችሁን አስተያየት ስጡበት የሃሳብ እጥረት ስለገጠመኝ።

  2. ወቸው ጉድ! የሃሳብ እጥረት ገጠመኝ አልክ አስተያየት ሰጭ አካሌ። ምን ቀረ። ሁሉን በደምና በጭቃ ቀብተህ አንተው ግራ ገብቶህ ሰው ግራ ታጋባለህ። “ትግሉ አፋፍ ላይ ሲደርስ የሚፈጠሩ ውጥንቅጦችና አዙሪቶች” በሚል ርዕስ የቀረበውን ተመለከትኩት። ነገር አፋፍ ከደረሰ እኮ ገደልና ውድቀት ነው የሚገጥመው? ወደ ሜዳው አይሻልም ነበር? ወይስ አማርኛው ለዘመናት እንዲሞት ስለተፈረደበት አዲሱ አማርኛ እኔን ስላልገባኝ ነው። የሃበሻ ፓለቲካ ራሱን መብላት ሲጀምር በእርግጥ ሞቱ እንደተቃረበ ካለፈው ታሪካችን ተምረናል። ነጻ አወጣሃለሁ የሚለውን ህዝብ ከብልጽግና ጋር አብራቹሃል በማለት ሴት፤ ሽማግሌ ካህንና ቄስ ሳይለይ ተንበርክከው በጉልበታቸው እንዲፏቀቁ የሚያደርግ ይህ ስብስብ ለማን ነው የቆመው? ይህ አድራጎታቸውስ ካህኑ መታወቂያ ለማሳየት ኪሱን ሲዳብስ በጥፊ ከመታው ባለጊዜ ፓሊስ ተግባር ጋር ምን ይለየዋል? ሲጀመር እኔን ምሰሉ የሚል የፓለቲካ ፈሊጥ ለአናብስት እንጂ ለሰው ልጅ አይመጥንም። ሰው አመዛዝኖ፤ ራሱን አሳምኖ ይህንም ያንም ሊመስል ይችላል። ይህ የፓለቲካ የእንቁራሪት ጭኽት አገር ከማመስና ህዝባችን ለባሰ ገመና ከመዳረግ ሌላ ትርፍ አያስገኝም። እስቲ ያለፉ የፓለቲካ ሽር ጉዶችን እንመልከት።
    ጠ/ሚ አብይ ከወያኔ የክፋት ጆኒያ አምልጦ ጠ/ሚ ሲሆን ግርግሩና ሆይ ሆይታው እንዴት እንደነበር ዘወር ብሎ ማየት ተገቢ ነው። ዛሬ ላይ ደግሞ ፎቶውን ከሂትለር ጎን ተለጥፎ ማየት የተለመደ ነው። በዚህ ላይ ባድሜን ለሻቢያ እንካችሁ ካለ በህዋላ በሁለቱ ሃገር መሪዎች የታየው ሽርጉድና ጉብኝት ልብ ያለው ይህ ነገር ይዘልቃል ብሎ መጠየቅ ግድ ይል ነበር። ያ ሁሉ የመተቃቀፍና የጉብኝት ግርግር ያስከተለው የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው በሚል ፈሊጥ የወያኔን ግባተ መሬት ለማስፈጸም የሻቢያ የፓለቲካ የሾኬ ጠለፋ ነበር። ያ ግን አልሆነም። አይሆንምም። ይህ ያስኮረፈው የሻቢያው የእድሜ ልክ መሪ አሁን ከራሺያ ከቱርክ ከግብጽ ጋርና ከሌሎችም የዓረብ ሃገሮች ጋር በማበር ፊቱን ወደ ሶማሊያ በማዞር ይኸው እንሆ የኢትዪጵያ አየር መንገድ በረራ እንዲያቆም ጠይቋል። የሻቢያ ክፋት መስፈሪያ አይችለውምና ገና ብዙ መከራ ይጎርፋል! በምትኩ የግብጽ፤ የቱርክና ሌሎችም የአየር መንገዶች ፈቃድ ሰጥቷል። ይህ ራስንና የራስ የሆነን እየጠሉ ነጭና አረብን ማምለክ ታላቁ የጥቁር ህዝቦች በሽታ ነው። ግን ለህዝብ ሳይሆን ለራስ ብቻ ለቆመ መንግስት ይህ ተግባሩ አስገራሚ አይሆንም።
    እንግዲህ የፋኖና የሌሎችን የብሄርተኞች ፊልሚያ የምንመዝነው አለም አቀፋዊውን የፓለቲካ ነፋስ ከከባቢው እሳት ጋር በማገናዘብ ነው። አንኮላው የብሄርተኞች ፓለቲካ ለትግራይ ህዝብ፤ ለኤርትራ ህዝብ፤ ለኦሮሞ ህዝብ ለአማራውና ለሌሎችም ያመጣውን ቱሩፋት አይተናል። ሞት፤ እስራት፤ መፈናቀል፤ ስደትና መከራን ብቻ ነው። ለዚህ ነው ህበረ ብሄር ያልሆነ የፓለቲካ ድርጅት ድርቡሽ እንጂ ነጻ አውጭ አይደለም የምንለው። ባይገባን፤ ባንረዳው ነው እንጂ ዓለም ሁሉ የተሰፋው ያለውድ በግድ ነው። ግን ከጦርነት ሰላም ይሻላል በማለት ያለፈውን ትቶ ሰው በሰላም ገብቶ ይወጣል። የቋንቋው ጦርነት ከንቱ መሆኑን የሚያመላክተው ያለውድ በግድ 21 ሃገሮች ስፓንሽ ሲናገሩ ወደ 10 የሚሆኑት ደግሞ ፓርቺጊዝ ይናገራሉ። ይህ በፈቃደኝነት የሆነ ሳይሆን በወራሪዎች ሃይል የተፈጸመ ነው። እኛ ግን የፈሰሰ ውሃ ላይ ስናለቃቅስ ሌላው ዓለም ጥሎን ነጉዷል።
    ፋኖ ለአማራ ህዝብ የሚያስብ ከሆነ የአማራን ህዝብ ተገን አርጎ እንደ ገና ዳቦ ከላይና ከታች በእሳት እንዲለበለብ ምክንያት መሆን የለበትም። የትምህርት ተቋሞች፤ የህክምና ስፍራዎች፤ እርሻዎች፤ የመገናኛ አውታሮች ወዘተ ሥራ አቁመው ምን አይነት ትግል ነው ለአማራ ህዝብ የሚባለው? ይልቅስ የጠራ አጀንዳ ይዞ ከመንግስት ጋር ተደራድሮ በሰላም ለሰላም ሲባል ብቻ ነገርን ማርገብ ተገቢ ነው እላለሁ። መንግስትም ትጥቅ ፍቱ እያለ ደፍ ደፍ ከሚል የታጠቀ ማን ለምን እንዴት በሚል ሂሳብ መዝግቦ በመያዝ በህግ እንዲኖሩ የጠራ ህግ ማውጣት ተገቢ ነው ። ትግሉ አፋፍ (ከፍታ) ቦታ ላይ ደረሰ ከተባልን ደግሞ የመከራው ቋጠሮ ሊላላ ይገባል እንጂ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየከረረ ሊሄድ አይገባም። ባጭሩ ጦርነት የኋላ ቀርነት ምልክት ነው። ሁሉን ነገር በመሳሪያ ሃይል እፈታለሁ ማለት የኖርንበት፤ ያየነው የውሻል ፓለቲካ ዛሬም ላይ በቆሻሻ ክምር ላይ ቆሞ ይዳክራል። ለማንም አይረባም። ዋ በህዋላ ሃገሪቱን ለከፋ መከራ አሳልፋችሁ ትሰጡና እየየ ብትሉ ዋጋ ይብሉን። ቀን እያለ ከመንግስት ጋር ተደራድራችሁ ህዝባችን በሰላም ውሎ እንዲያድር አድርጉ።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

192146
Previous Story

አርበኛ አሰግድን በተመለከተ ጥብቅ መልዕክት | በጎንደር ሁሉም ተማረኩ | በጎጃም አመራሮቹ በሙሉ አለቁ | በሸዋ ባንዳወች ተደመሰሱ. | የፋኖ መሪዎች ምላሽ በአርበኛ አሰግድ ዙሪያ ጎንደር ድል በድል ሆነች “ክልሉን እከፍለዋለሁ” አብይ

192151
Next Story

ዘመነ ካሴ ስለ አሰግድ ዝምታውን ሰበረ | “እዚህ ቁጭ ብለን ሞት አንጠብቅም” የሰራዊቱ አባላት| ጄ/ሉ እውነታውን አወጣ | ኢንጅነር ደስአለኝ ቢያስብ በአርበኛ አሰግድ መኮንን ምትክ ተመረጠ

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop