ብልግናዎች: ፍላጎታችሁ ምን ይሆን?

ህሩይ እስጢፋኖስ

ገዳይ አብይ አህመድ መመለስ ያለበት ጥያቄ
ገዳይ አብይ አህመድ መመለስ ያለበት ጥያቄ

ይድረስ ለብልጽግና መንግሥትና ፓርቲ ባለሥልጣኖች!

ሕዝብ እናንተን አስተምሮ እሱ ሳይኖር እናንተን አኑሮ በድግሪ በማስተር አስመርቆ ለዚህ ሥልጣን ሲያበቃችሁና ኢትዮጵያን ያህል ታላቅ የሀገር መምራት ሐላፊነት ሲያስረክባችሁ በእየምነታችሁ በገባችሁት ቃል መሠት መልካም ውለታውን መመለስ ይጠበቅባችሁ ነበር፣ በእውነት የተማረ ሰው ሰብእና ቢኖራችሁ ኖሮ ውለታውን  መመለስ ባትችሉ ከድህነት የሚወጣበትን የሥራ ፈጠራ ክህሎትን  ባታመቻቹለት እንኳን በድህነቱ እንዲኖር ሰላሙን ልትሰጡት ይገባ ነበር።

ሕዝቡንም ባትበድሉት እና ባትገድሉት ባታጣሉት እና ባታፈናቅሉት ኖሮ ወደ ሥልጣን በመጣችሁበት ጊዜ እንዳሳያችሁ ፍቅሩን ባሳያችሁ ድጋፉንም ባልነፈጋችሁ ነበር።

ሁሉም ብሔር ብሔረሰብ ያለምንም ልዩነት በዘር በጎሳ ልዩነት ሳይኖረው በአንድ ተጋብቶ እና ተዋልዶ ሲኖር ያሰባችሁት የሙስና እና የሥልጣን ማራዘሚያን ስልት ለመጠቀም ስትሉ አንተ የምሥራቅ አንተ የምዕራብ አንተ የደቡብ አንተ የሰሜን በማለት የማያውቀውን የዘር ጥላቻን በመስበክና በማስተማር የተንኮልና የጥላቻን ዘር ብትዘሩበትም ሕዝቡ ግን አሁንም የእናተን ሴራና ተንኮል ሰምቶ እንዳልሰማ በማለፍ አሁን በፍቅርና በመቻቻል ለመኖር ቢሞክርም እናንተ ግን በሽፍታ ስም ገዳይ ቡድን በማቋቋም እና በማዘጋጀት የዚህን ድሀ ሕዝብ ቤቱን እና ንብረቱን በማቃጠል ከቀየው ከአካባቢው አፈናቀላችሁት።

በገዳም የሚኖሩ መናንያን ባህታውያንን እና መነኰሳትን እንዲሁም ጉባዔ ዘርግተው የሚያስተምሩ መምህራንን እና የሚማሩ ደቀመዛሙርትን በከባድ መሳርያ በመደብደብ ገደላችሁ ገዳማቱንና የጉባዔ ቤቶችንም አቃጠላችሁ ይህ አይነቱ አረመኔያዊ እና ታሪክ ይቅር የማይለው ድርጊት በነ ዮዲት ጉዲትና በእነ ግራኝ አህመድ እንዲሁም በእነ አጼ ሱስንዮድ ዘመንም አልተፈጸምም። የሕዝብ ጥያቄ ተስማምታችሁ ግዙን እንጂ እንግዛ አላልንም።

ይህ የዋህ ሕዝብ ሳይኖር ባኖራችሁ እንዳይኖር አደረጋችሁት ሳይማር ባስተማራችሁ የሚማሩ ልጆቻቸውን በተለይ ማንነትን ተኮር ባደረገ መልኩ የአማራውን ሕብረተሰብ ልጆች ከትምህርት ቤት እያገታችሁ 20 እና 30 ሚሊየን ብር ካልሰጣችሁ ልጆቻችሁ አይለቀቁም በማለት እንኳንስ በምሌን የሚቆጠር በመቶም የሚቆጠር የሌለው ከእጅ ወደ አፍ በሆነ ኑሮ  የሚኖር ድሀ ሕብረተሰብ በመሆኑና የተጠየቀውን ከፍሎ ልጆቹን ማስለቀቅ ባለመቻሉ  የታገቱትን ልጆች በመግደል ወላዶቻቸውን የደም እንባ እያሰለቀሳችሁ በግፍ ቀጥላችኋል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  በማይካድራ ንጹሀን ዜጎች ላይ በተፈጸመው ድርጊት እጅግ ማዘናቸውን የሐረር ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ

ይሁንና በተለይ የአማራውን ሕብረተሰብ መግደልና ማግለል ስር ነቀል የዘር ማጥፋት ብሎም ቅርሱን እና ወጉን ባህሉን  ማንነቱን ለማጥፋት እየተሰራበት የቆየው ቀደም ያለነ 3 አሰርተ ዓመታትን ያሳለፈ ቢሆንም ነገር ግን በጉልህና በግልፅ የአማራው መጠቃትና በማንነቱ መገደል መፈናቅል እንዲሁም ከቀየውና ከቦታው ከመኖሪያው መባረርና መሳደድ እየባሰ የመጣው በዘመነ ኢሀዲግ ነው

በመቀጠልም ኢሀዲግ ወልዶ ያሳደገው የኢሀዲግ ልጅ የብልጽግና መንግሥትና በእሱ ፈቃድ የተመለመሉ ፓርቲዎች ገዢ ሆነው በወንበር ላይ ከተቀመጡ በኋላ የኢሀዲግን የሴራ ፖለቲካ በእጅጉ ክፋቱንና ተንኮሉን እንዲሁም አንዱን ካንዱ ማገዳደሉን እና ማጣላቱን በ10 እጥፍ በማስበለጥ ከአባታችሁ ኢሀዲግ የተቀበላችሁትን እና የወረሳችሁትን የተንኮል ቃል ኪዳን ለማስፈጸም ስትሉ ይህንን ምኪን እንግዳ ተቀባይ ለወገኑና ለሀገሩ ከራሱ በላይ የሚያስበውን በኢትዮጵያዊነቱና በእናት ሀገሩ ኢትዮጵያ እንዲሁም የሉዓላዊነቱ መገለጫ በሆነው በሰንደቅ አላማው የማይደራደረውን አማራ ለማጥፋት በጠላትነት ተነስታችሁ ትገድሉትና ታፈናቅሉት ጀመር።

በእውነት ይህ ደጉ የአማራ ሕዝብ ሁሉን አቀፍና የብሔር ብሔረ ሰብ እህት ወንድሞቹን ወዳድና ሁልን አቀፍ እንዲሁም እንኳንስ የሀገሩን ዜጋ ከውጭ ሀገር የመጣውን ዜጋ እንደወንድሙ በመቁጠር እግር አጥቦ ምግብ መግቦ አጠጥቶና በአልጋው አስተኝቶ የሚያስተናግድ ደግ ሕዝብ ሆኖ ሳለ መገደሉ ለምንድ ነው ከተባለ ምክንያቱ ማንነትን ማጥፋት ነው የኢትዮጵያ የማንነቷ መገለጫ የሆኑት መንፈሳዊና ቁሳዊ ቅርሶች በይበልጥ የሚገኙት በዚሁ በአማራው ክልል ስለሆነ እና እንዲሁም ሁለቱ የኦርቶዶኮስና የእስልምናም ሃይማኖቶች በመቻቻል ለሌላው ክፍላተ ዓለማት እንደምሳሌ ሆነው በሰላምና በፍቅር በልዕልናና በክብር ማንነታቸው ጠብቀው የሚኖሩት በዚሁ በአማራው ክልል ስለሆነ ይህንን ማንነት ለማጥፋት ነው።

እንዲሁም ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዊነት እዚህ ለመድረሱ እና ወደፊትም በቀጣይነ ሳይደበዝዝና ሳይጠፋ ጎልቶ እንዲኖ ምክንያቱ ይሄው አስተዋዩ የአማራ ሕዝብ ስለሆነ ይህ እንዳይሆንና ኢትዮጵያ የሚለው ስሟና ማንነቷን እንዲሁም የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነቷን ለማጥፋት ሳያርፉ ሌት ከቀን የሚሰራ የውጭ ጣልቃ ገብ ጠላቶች እጅ ስላለበት መሆኑ ግልፅ ነው።ከሁለትና ከሦስት ዓመት በፊት ከራሱ ክልል ውጭ እና በሌላው ክልል የሚኖረውን ይህንን ደጉንና ሁሉን አቀፍ የሆነና ከሌላው ብሔር ብሔረ ሰብ ጋር ተዋልዶና ተዛምዶ የሚኖረውን የአማራ ሕዝብ ቀስ በቀስ በማጥፋት ከዚያም ወደራሱ ክልል በመግባት ቀስበቀስ እርስበርሱ በማጣላትና ደም በማቃባት በማገዳደል በቁጥር በሁለተኛ ደረጃ የያዘውን የአማራ ሕዝብ በቁጥር የማሳነስና ብሎም የማጥፋት ፖሊሲ ታቅዶበት እየተሠራ ነበር።

ተጨማሪ ያንብቡ:  "እባብ ለመደ ተብሎ በብብት አይያዝም" | ከጃል መሮ - እስከ ጀዋር መሐመድ | ዳኛቸው ተሾመ

ለዚህም በአንድ ወቅት የሚርጫ ወቅት እየደረሰ ስለነበር አንድ ጋዜጠኛ የኦፌኮ ሊ/ር የሆኑ አንድን ግለሰብ ኢንተርቪ በሚያደርግበት ሰዓት የጠየቃቸው ጥያቄ እንዲህ የሚል ነበር ጋዜጠኛው ይጠይቃል “የተከበሩ ……. አሁን ሰሞኑን ምርጫ እየደረሰ ነው እናንተ መላው የኦሮሞን ሕዝብ ወክላችሁ ነው የምትወዳደሩት ነገር ግን በተለይ በአሩሲና በወለጋ በጅማና  በሻሸመኔ ብዙ የአማራ ማኅበረሰብ ነዋሪዎች አሉ ውክልናችሁ ለእነሱ ሁሉ ነው ወይስ ለኦረሞ ብሔረሰቦች ብቻ ነው?” ብሎ ሲጠይቃቸው የመለሱት መልስ በሚገርም ሁኔታ እንዲህ የሚል ነበር።

የተጠያቂው ግለሰብ መልስ  “አሁን አንተ በጠቀስካቸው ቦታዎች እና አካባቢዎች ያለን መሬት እንጂ ሰው የለንም” ብለው መለሱ።

በእውነት ይህ መልሳቸው አንድ ተምሬያለሁ ብሎ ዜጋን ይቀርጻል ተብሎ ታምኖበት ትልቅ ኃላፊነት ተሰጥቶት በዩንቨርስቲ ከሚያታስተምር ፕ/ር ይህ ሲሰማ  ሀገሪቱ በገደል አፋፍ ላይ እንዳለች የሚያሳይ ነው።

እኚህ ግለሰብ በዚያን ጊዜ ይህንን ያሉት ለካ ያቀዱትን እቅድና ፕላን ስለነበር ከዚያ በኋላ በነበሩት ዓመታት መሬት ነው ያለን እንዳሉት ከክቡሩ የሰው ልጅ መሬትን በማስበለጥ የሰው ልጅ ይጠቀምበት ዘንድ ለሰው ልጅ የተፈጠረውን መሬት የኛ ነው ብለው በማሰ ለማስለቀቅ እንዲሁም የተከበረውን የአማራ ሕዝብ እንደሰው ባለመቁጠር በመናቅና በማቃለል መሬት እንጂ ሰው የለንም በሚል ኢሰብአዊ እና ኢምሁራዊ በሆነ መልስ ክቡሩን የአማራ ሕዝብ ከመሬት አሳንሰው  መግለጻቸው ሳያንስ፣

እንዳሉትና እንዳቀዱት ያለማቋረጥ በአለፉት ስድስት ዓመታት በእነዚህ በተጠቀሱት በተለይ በአራቱ አካባቢዎች የሚኖሩ የአማራ ብሔር ተወላጆችን  ሌሊት በተኙበት ቀን በተሰማሩበት በአሰቃቂ ሁኔታ ጨፍጭፎ በመግደል ደማቸውን እንደጎርፍ አፈሰሳችሁ። አጥንታቸውንም እንደ ድንጋይ ከሰከሳችሁ፣

የእርጉዞች እናቶችን ማሕፀን ሰንጥቃችሁ የተረገዙትን ብዙ ሕፃናትንና እናቶችን በመግደል እና ዘቅዝቃችሁ በማቃጠል በዓለም ላይ ታይቶም ተሰምቶም የማይታወቅ የጭካኔያችሁን ጥግ አሳያችሁ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  በኢትዮጵያ አየር መንገድ ትሰራ የነበረች አንዲት ቻይናዊት ሆስተስ በፖሊስ ከአገር ተባረረች

እንዲሁም ሁሉን ከሚኖርበት ከቀየውና ከአካባቢው በማፈናቀላችሁ ይኸው በሚሊዮን የሚቆጠር ሕዝብ በማሳደድ ያለ ምግብ ያለልብስና ያለመጠለያ አስቀራችሁት።

በዚህም ባለመርካታችሁ በእውነት ከሞት አምልጦ ነፍሱን ለማዳን በቤተ ክርስቲያን እና በተለያዩ ተቅዋማት ተጠግቶ እና ተጠልሎ ሲኖር የነበረውን ተፈናቃይ የአማራ ሕዝብ አሁን ሰላም ሆኗል ወደቀያችሁ ተመለሱ ብላችሁ መልሳችሁ ልምን ከሞት ተርፈው አመለጡ በሚመስል መልኩ በድጋሜ አስፈጃችኋቸው።

የመጀመሪያውን ፕላናችሁን በዚህ መልኩ ሸኔ በምትሉት ገዳይና አስገዳይ ቡድናችሁ አስፈጅታችሁ ከጨረሳችሁ በኋላ፣በሁለተኛው ፕላናችሁና እቅዳችሁ መሠረት በመላው የአማራ ክልል እና የአማራ ሕብን ጨርሶ የማጥፋት ጀኖሳይድ ለመፈጸም በመላው የአማራ ሕዝብ ላይ ጦርነት ተከፈተበት። ይህም ሕዝብ ከ3 አስርት አመታት ለቅሶና ዋይታ በኋላ ከፈጣሪውና ከነፍጡ በስተቀር የሚታደገው ቢያጣ በአልሞት ባይ ተጋዳይነት ነፍጡን አንስቶ ለመፋለም ከአሁን በኋላ ፋኖ ነኝ ብሎ ጫካ ገብቶ ይታገል ጀመረ።

እንዲሁም ቅድስት ቤተክርስቲያን ለሀገር እና ለወገን ሰላምን እንዲሁም ለሞተው ዕረፍተ ነፍስን በሕይወትም ለሚኖረው ዕድሜና ጤናን ለመግሥትም ማስተዋልን ስጥ እያለች በሌሊትና በቀን የምትጸልይን ቤተ ክርስቲያን ጳጳሳቶቿን በመከፋፈልና እንደ አርዮስን እንደነ ሰባልዮስ እንደነ ንስጥሮስና መቅዶንዮስ  ከሀድያን ጳጳሳት ነን የሚሉ አስመሳዮችን ከውስጥ በማስነሣትና በመከፋፈል ቅዱስ ሱኖዶሱን እና የቅዱስ ሲኖዶሱ ሰብሳቢ የሆኑትን ቅዱስ ፓትርያርኩን በመቃወም በድፍረትና በማን አለብኝነት በመነሳሳት የዘርና የጎሳ ጳጳሳት እንዲሾሙ በማድረግ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ሰላም በመረበሽ ፈተናዋ እንዲበረታ አደረጋችሁ። ነገር ግን መሥራቿ የሰላም ባለቤት ሰላማዊ ኢየሱስ ክርስቶስ ስለሆነ የሲኦል ደጆች አያናውጿትም።

ስለዚህ አሁንም ይህንን የበደላችሁትን በተለይ በማንነቱ ጀኖሳይድ እየፈጸማችሁበት ያለውን የአማራ ሕዝብ ይቅርታ ካልጠየቃችሁ የሕዝብንም ሥልጣን ለሕዝብ ካላስረከባችሁ  ከእግዚአብሔርም ከተገፋውም ሕዝብ ይቅርታ የሌለው ፍርድ የሚጠብቃችሁ መሆኑን ከወዲሁ ልታውቁት ይገባል።

 

እግዚአብሔር  ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ

እግዚአብሔር  ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ

2 Comments

  1. ውድ ወንድሜ ከእነዚህ ሰዎች ይቅርታ እንዲጠይቁ መማፀን ተገቢ አይደለም። እነዚህ ሰዎች በከፍተኛ መቀጣት አለባቸው። ለመኖር የሚፈልጉና ስንትና ስንት ምኞት ያላቸውን መግደላቸው ብቻ አገርን እንዳለ አውድመዋል፣ ባህል አርክሰዋል። ስለሆነም እንደማንኛውም ወንጀለኛ ተገቢውን ቅጣት ማግኘኘት አለባቸው። ከዚህች ዓለም በሞት እስኪለዩ ድረስ ወህኒ ቤት ገብተው ስቃያቸውን ማየት አለባቸው። ይቅርታ ጠይቁ ማለት የሰሩትን ስንትና ስንት ወንጀል አቃሎ እንደማየት ይቆጠራል።

    ፈቃዱ በቀለ

  2. የሃገራችን አሸሸ ገዳሜ ፓለቲካ ራስንም ህዝብንም አይጠቅምም። ኑረንበት ያየነው ስለሆነ ለዚህ ሃሳብ ምስክር አናቆምም። የሚያሳዝነው ሁልጊዜ በለውጥ ስም ትሻልን ትቼ ትብስን መሆኑ ነው። ወያኔን የኢትዮጵያ ህዝብ አክ እንትፍ ያለው የትግራይ ልጆች ስለሆኑ አይደለም። ከትግራዋይ የበለጠ ኢትዮጵያዊ ማን አለና! ግን ከበረሃ እስከ ከተማ ደም አፍሳሾችና ከፋፋይ የዘር ፓለቲከኞች ስለሆኑ ነው። ያ ዘፈን ቀርቶ አሁን የአማራና የኦሮሞ ጥምረት ተብሎ የተጀመረው የኦሮሞ የፓለቲካ የሾኬ ጠለፋ ስልት አማራውን እየበላና እያስበላ፤ ትግሬውን በዚህም በዚያም እየወቀጠና እያስወቀጠ ዛሬ ለምንገኝት የአስረሽ ሚቸው ፓለቲካ ዳርጎናል። ይህ የግፍ ድርጊትም ልክ እንዳለፈው ሁሉ ማቆሚያ አለው። በ 27 ዓመት ወያኔ ካደረሰው ሰቆቃ 100 ጊዜ እጥፍ መከራ ህዝባችን ያየው በእነዚህ 6 ዓመታ ውስጥ ነው። ግን እንዘነጋለን።
    በብልጽግና ዘመን የተሰራውንና እየተሰራ ያለውን ግፍ ይህ ነው ብሎ ለሰሚ ለመናገር በድን መሆን ይጠይቃል። ይሰቀጥጣል። የሰው ልጅ ይህን ይሰራል እንዴ ያሰኛል። ሰው አውሬ ሆኖ በዘሩ ተልክፎ ሌሎችን እየለከፈ በዚህም በዚያም የተዳፈኑ እሳቶችን በመለኮስ የምድሪቱ ኗሪዎችን መፈናፈኛ በማሳጣት የቁም እስረኛ እንዲሆኑ አድርጓል። የሄደ የመጣው ጠበንጃ አንጋችና የዘር ሰካራሞች ሁልጊዜ የሚነግሩን ያለፈው መንግስት የሰራውን ክፋትና ተንኮል ነው። ከወያኔ የክፋት ጆንያ አፈትልኮ የወጣው የድህነቱ መንግስት ብልጽግና ጅምሩ ሽወዳ ፍጻሜው ኦሮማይ እንደሚሆን ቀደም ብለን የምናውቅ አውቀናል። ለዚህም ነው በተደጋጋሚ የሃበሻ ፓለቲካ ማለት የመበላላትና የመጠላለፍ ትርኢት ነው ያልነውና የምንለው። ግን የሚበዛው የሃገሬ ህዝብ እየተሸወደ እንደሆነ የገባው ዘግይቶ ነው። ቀድሞ ማወደስና መጎንበስም የሚያስከትለውን ጉዳት አሁን የተረድ ይመስላል። ሃብትና ስልጣን ተጨምሮላቸው በጊዜአዊ የስልጣን ኮርቻ ላይ ቁጢጥ በማለት ህዝብን የሚያበራዪት ከብሄር ታጣቂ ሃይሎች ጋር በማበር አንድ አንድን እንዲገደልና እንዲዘርፍ የሚያደርጉት ሁሉ የቁም ሙቶችና በብሄር ስም የሰከሩ ወስላቶች ናቸው። ሰው እንደ አፓርታይድ ክልል አበጅቶ ሰላም ሊኖር አይችልም። የሚያጋጨንን ነገር ለማራባት ግን የክልል ፓለቲካ ይጠቅማል። እኛ ስንገዳደል እነርሱ በሩቅና በቅርብ እያዪን ይስቃሉ። የቀጣፊ ፓለቲካ እንዲህ ነው። እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል አይነት።
    ሲጀመር የሃበሻ ፓለቲካ ሰውን ፈጥኖ ለመኳል ወይም ለማጠልሸት አይኑን አያሽም። ተግባራቸውንና ታሪካቸውን ተርከውና ከፍለው አስተርከው የቆየ ታሪክን ለማጣመም ከፈረሱ ጋሪው ቀድሞ የሚሄድበትን ዓለም በምናባዊ እይታቸው ፈጥረዋል። የተፈጥሮን ሂደትና ኡደት ክደዋል። በሽወዳና በዘርና በቋንቋ ፓለቲካ ተሳክረዋል። የሚያይ አይን የሚሰማ ጀሮዎቻቸውን ተነጥቀዋል። የውሸት ወሬ ማድራትና መንዛት የዘመኑ የፕሮፓጋንዳ ቅስቀሳ ፍሬ አፈራ አላፈራ ንዋይ እየፈሰሰበት ይዘረገፋል። እንዳለ የሰለቀጠው ማወራረጃ አጥቶ ሲንፈራገጥ የነቃው ራሱን ከውሸት ቱልቱላ ያርቃል። ለዚህ ነው የብልጽግና መንግስት ፍላጎቱ ምን እንደሆነ ማንም ሰው የማያውቀው። ራሱንና ሌሎችን እየሰለቀጠ ይጓዛል።
    በትግራይ ህዝባችን ሃበሳ ይቆጥራል፤ የአማራ ክልል በሚባለው ህዝቡ በሁለት በኩል ይሞታል። የብልጽግና ደጋፊ ተብሎ በፋኖ ይገደላል። መንግስት ደግሞ ፋኖ ነህ ብሎ አሰልፎ ይረሽነዋል። የአማራ ህዝብ አሁን ላይ እንደ ገና ዳቦ በሁለት እሳት መካከል ገብቶ የሚጠበስ ህዝብ ነው። በወለጋና አካባቢው ሰዎች ለህክምና ለትምህርት መንቀሳቀስ አይችሉም። የዘር ሰካራሞች ዛሬም ሰው አፈና፤ ባንክ ዘረፋ፤ የሰው መኖሪያ ቤትና የህዝብ መገልገያ አውታሮችን እያወደሙ ለኦሮሞ ህዝብ ነው የምንታገለው ይሉናል። ድንቄም ትግል። ሰው በዘሩ ከተሰለፈ ጤና የለውም። ለዚህ ነው ትግራይም ይሁን አማራ ኦሮሞም ይሁን ሌላ የዘር ፓለቲካን አክ እንትፍ የምለው። ሰውን በሰውነቱ የሚመዝን የፓለቲካ ድርጅት በኢትዮጵያ ውስጥ ገና አልተፈጠረም። ድሮ ድሮ ሽታው ኢህአፓ ላይ ነበር። አሁን ያ ተረት ነው።
    ቤተሰብን በትነው፤ የሰው ደም አፍሰው፤ የንጽሃንን ገላ በጉልበትና በሥልጣን ሳቢያ አርክሰው ዘርፈውና ገድለው ባጠራቀሙት ሃብት የሚፈነጩት የአሁኖቹ አለቆቻችን ዋ ጊዜ ለኩሉ እንዲሉ ውድቀታቸው የሮም አወዳደቅ እንደሚሆን ጠንቋይ ወይም ነብይ እንዲነግረን ልንጠብቅ አይገባም። የራሳቸው የክፋት ስራ ስር ሰዶ ጠልፎ ሲጥላቸው ማየታችን አይቀሬ ነውና! ግን ጊዜ እያለ ነገሮችን ማስተካከልና እንበለ ፍርድ የታሰሩትን መፍታት፤ ከተቆራቋሽ ሃይሎች ጋርም መመካከርና ሰላምን ማስፈን እጅግ አስፈላጊ ነው። ብቀላ ብቀላን ይወልዳል። እኔ የወያኔም ሆኑ የብልጽግና ዘመን ባለስልጣኖች ይሰቀሉ፤ ይፈለጡ ከሚሉት አይደለሁም። ሰው የሚታሰረው ወይም ከከፋም በሞት የሚቀጣው ሌላው እንዲማርበት ነው። እኛ ሃገር ግን ቆሞ የሰቀለው በሌላ ጊዜ ተሰቃይ እየሆነ ተቸግረናል። መገዳደል፤ በዘር ሰውን መፈረጅ፤ ኢትዮጵያዊ ነኝ ከማለት ይልቅ አማራ፤ ትግራይ፤ ኦሮም ወዘተ ማለቱ ይቁም። ድር ቢያብር አንበሳ ያስር ይላሉ አበው። እንተባበር። ህዝባችንም ልክ እንደ ድሮው በፈለገው የሃገሪቱ ክፍል በመሄድ ሰርቶና አካባቢውን መስሎ እንዲኖር መንገድ ይመቻች። የክልል የጠባብ ብሄርተኞች ፓለቲካ ይናድ። ፍክክሩና ጊዜው የእኛ ነው ማለቱ ይብቃ። ዋ በህዋላ መውጫ ይታጣል። ጊዜ እያለ ለህዝባችን አንድነትና ሰላም በህበረት እንስራ። ማን እንደጻፈው አላውቅም። ግን አንዲት የግጥም ስንኝ ልዋስና ነገሬን ልዝጋ።
    የፉክክር ቅሚያ በረሃብ እየናጠን
    ከደፋነው ጠግቦ ውሻችን በለጠን።
    አይ አማርኛ እንዳበጅሽ ትበጃለሽ ያለው ፌዘኛ ማን ነበር። የሚገርም ስንኝ ነው። በቃኝ!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share