ጀግና ሲወድቅ ጀግና ይተካል
ሰንደቅ አርማውን፣ ዳግሞ ያነሳል።
*ውብ አንተ* ቢያልፍም ውቦች ተነሱ
እግረ መንገዱን ተተኩ በ’ሱ።
የጀግኖች ኮቴ የተከተሉ
በጣይቱ ስም…….
*ቆራጥ እንስቶች* ይህን ፍም እሳት ተቀላቀሉ።
ሊያም በሸዋ በዋና በሩ
፬ ኪሎ ላይ….
ግዜው ተቃርቧል ሊናድ መንበሩ።
እናም…. *ሻለቃ* ሞቷል አትበሉ
*ምኞቱ ይህ ነው…..!*
እሱ ቢሰዋም *አይቀርም ድሉ!*
** ማምሻውን የሻለቃ ው’ባንተ አባተን አሳዛኝ እልፈት ሰምቼ ማለዳ አንድ ወዳጄ ይህንን በሸዋ ጠ/ግዛት የአማራ ፋኖ እዝ የሴቶች ጉዳይ መምሪያ ዘርፍ ጥሪ የሚያሳይ ቪዲዮ ሲያደርሰኝ ትግል እንደ ሩጫ (ዱላ ቅብብሎሽ) ነውና በፅናትና በተስፋ እንድትኖር ያደርግሃል።
*ነብስ ይማር ለጀግናችን!*
*ፅናት ለእህቶቻችን!*