ጀግና ሲወድቅ ጀግና ይተካል

ጀግና ሲወድቅ ጀግና ይተካል
ሰንደቅ አርማውን፣ ዳግሞ ያነሳል።

*ውብ አንተ* ቢያልፍም ውቦች ተነሱ
እግረ መንገዱን ተተኩ በ’ሱ።

የጀግኖች ኮቴ የተከተሉ
በጣይቱ ስም…….
*ቆራጥ እንስቶች* ይህን ፍም እሳት ተቀላቀሉ።

ሊያም በሸዋ በዋና በሩ
፬ ኪሎ ላይ….
ግዜው ተቃርቧል ሊናድ መንበሩ።

እናም…. *ሻለቃ* ሞቷል አትበሉ
*ምኞቱ ይህ ነው…..!*
እሱ ቢሰዋም *አይቀርም ድሉ!*

** ማምሻውን የሻለቃ ው’ባንተ አባተን አሳዛኝ እልፈት ሰምቼ ማለዳ አንድ ወዳጄ ይህንን በሸዋ ጠ/ግዛት የአማራ ፋኖ እዝ የሴቶች ጉዳይ መምሪያ ዘርፍ ጥሪ የሚያሳይ ቪዲዮ ሲያደርሰኝ ትግል እንደ ሩጫ (ዱላ ቅብብሎሽ) ነውና በፅናትና በተስፋ እንድትኖር ያደርግሃል።

*ነብስ ይማር ለጀግናችን!*
*ፅናት ለእህቶቻችን!*

ተጨማሪ ያንብቡ:  ከ አስር በላይ ከተሞች በፋኖ ዕጅ ገብተዋል !| ፋኖ የባህር ዳር ቀበሌ 14 ገብቶ ሰራዊቱን አናወጠ | ም/ ጎጃም ከባድ ትንቅንቅ ጦሩ እጅ ሰጠ|

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share