December 20, 2023
6 mins read

ብርቱ ምስጢር: የድሮን ጥቃትን ለመከላከል ባለፈው ጊዜ በፍኖተሰላም የደረሰ የድሮን ጥቃት – ተግባር ቁጥር ፩

ተግባር ቁጥር ፩-  DOC-20231220-WA0012.

Fano Drones Defence Squad

ህዳር 28 ቀን 2016 ዓ.ም

tegbar

ለፋኖ ታጋዮች ጥንቃቄ ይረዳ ዘንድ

ማህተም ፣ የማይነበብ

ወታደራዊ ድሮን ለመከላከልና ለማምከን ብዙ የተለያዩ በቴክኖሎጂ የተደገፉ ዘዴዎች አሉ ፣ ሆኖም በቴክኖሎጂ እየታገዙ ድሮንን ለመጣል ወይም ተልእኮዋን ለማምከን የሚረዱ መሳሪያዎች በፋኖ እጅ እስከሚደርሱ ድረስ በዩክሬንና በአፍጋኒስታን የነፃነት ታጋዮች እራሳቸውን ከድሮን ጥቃት ለመከላከል እና የጠላትንም ሀይል ለማዳከም የሚያስችል የሚከተሉትን ሚስጥራዊ የማሳሳቻ ዘዴዎች ተጠቅመው ከጠላት የሚሰነዘሩ የድሮን ጥቃቶችን አምክነውበታል ፣

፩) የሚሰሩ የሞባይል ስልኮችን በመሰብሰብ ፣ በተለይም ከዚህ በፊት ለጠላት መረጃ የተጋለጡ ሲም ካርዶችን ወይም ጠላት (መንግስት) የፋኖ ናቸው ብሎ የሚጠረጥራቸው የስልክ ቁጥሮችን (ሲም ካርዶችን) የያዙ የስልክ ቀፎዎችን በዛ ባለ ቁጥር ማዘጋጀት ፣

፪) እነዚህ ለዚህ ተግባር እንዲውል የተሰበሰቡት ስልኮች ባትሪዎቻቸው ሙሉ ሆነው ቻርጅ መደረግ አለባቸው ፣

፫) ጠላት (መንግስት) ቀደም ሲል ፋኖዎች ይኖሩበታል ብሎ በአየር እና በምድር ጭምር የስለላ አሰሳ በሚፈፅምባቸው አካባቢ ወይም በተደጋጋሚ ጠላት በምድርም በመሬትም ጥቃት የሚፈፅምባቸው የፋኖ ወረዳዎች ፣ መንደሮች ወይም አካባቢዎች ለይቶ ለዚህ ግዳጅ እንዲውሉ ማድረግ ፣

፬) የፋኖ ምሽጎች ሊመስሉ በሚችሉ የቋጥኝ ስፍራዎች አካባቢ ከዛፍ የተቆረጡ በሰው ቁመት አካባቢ እርዝመት ያላቸው የግንድ ቁራጮችን በማዘጋጀት የፋኖ ዩኒፎርሞችን በማልበስ ምሽግ፭) ውስጥ የተቀመጡ ፋኖዎች አስመስሎ ማስቀመጥ ፣ በሌላ አነጋገር እውነተኛ የፋኖ ወረዳ ምሽጎች ማስመሰል ፣

፮) ከጥቅም ውጭ የሆኑ ግልጋሎት የሌላቸው መሳሪያዎችን በተዘጋጁት የማሳሳቻ ምሽጎች ውስጥ “ፋኖ ተመስለው” ለተዘጋጁት የግንድ ቁራጭ አሳቻዎች መሳሪያውን አስይዞ በምሽጉ የተዘጋጁ አስመስሎ ማቀናበር ፣

፯) ከፍ ብሎ በተራ ቁጥር ፩ እና ፪ ላይ የተጠቀሱትን ስልኮች ላይ ሞልተው ቻርጅ የተደረጉትን ባትሪዎቻቸውን ከየስልክ ቀፎዎቻቸው ውስጥ መግጠም ። በተራ ቁጥር ፩ ላይ የተገለፁት ስም ካርዶችም በእያንዳንዱ ስልክ ውስጥ መኖራቸውን ማረጋገጥ ፣ የጂ ፒ ኤስ መተግበሪያ መስራቱን (GPS Feature ON) ማረጋገጥ ፣ ቀጥሎም ለአሳቻነት በተሰራው ምሽግ ውስጥ እና አካባቢ ምንም የስልክ ሲግናል ብሎክ መሆን በማይችልበት ስፍራ እየመረጡ ስልኮቹን በተሰባጠረና ዘርዘር ባሉ ስፍረዎች ላይ ማኖር ፣

፱) ከዚህ በሗላ ይህንን ዝግጅት ያደረጉት ፋኖዎች በአስቸኳይ ስፍራውን በፍጥነት ለቀው በርቀት ወደሚገኘው የወገን ወታደራዊ ወረዳና ምሽጎች መሄድ ይኖርባቸዋል ።

ይህንን ተከትሎ ጠላት (መንግስት) በሁለት አይነት መንገድ በሚያደርገው የድሮን አሰሳ ትክክለኛ የፋኖ ተዋጊዎችን የስልክ መስመር ግንኙነት ያገኘ መስሎት ተክለፍልፎ ወደ ተዘጋጀለት ወጥመድ ሊገባ ይችላል ። ድሮኑ የጂ ፒኤስ GPS እና የስልኩን ሲግናል ማሰስ ይችላል ።

በዚህም ረገድ ጠላት አሳቻ በሆነ ኢላማ ላይ በከንቱ የድሮን ተተኳሾቹን ክማባከኑም በላይ ፣ በርቀት ምሽግ ውስጥ የተዘጋጁ የርቀት ተተኳሽ መሳሪያ ያላቸው ድሮኗን ከአየር ላይ መተው ሊጥሏት ይችላሉ ።

ከፍተኛ ጥንቃቄ ፣

በዚህ ፋኖ ባዘጋጀው አሳቻ ምሽግም ሆነ አካባቢ አንድም ፋኖ ወይም የአካባቢው ነዋሪ መገኘት የለበትም ምክነያቱም የደሮን ጥቃት ከኢላማው ውጭ ስቶ ሊያጠቃ ስለሚችል፣ ከዚህ አካባቢ ፈጥኖ ርቆ መሄድ ቸል የማይባል የወታደራዊ ደህንነት ግዴታ ይሆናል ።

ድል ለዐማራ ፋኖ !

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

ከነፃነት ዘገዬ የአራት ኪሎው ኦነግ ሸኔ ከቁጥር ጋር እንደተጣላ ዕድሜውን አገባደደ፡፡ ኦነግ/ኦህዲድ ዛሬም ሆነ ዱሮ፣ በቤተ መንግሥትም ይሁን በጫካ ቁጥር ላይ ያለው አቋም ምን ጊዜም ያስደንቀኛል፡፡ ደግሞም እየባሰባቸው እንጂ ሲቀንሱ አይታዩም፡፡ ጥቂት

80 ቢሊዮን ብር ስንት ብር ነው?

በላይነህ አባተ ([email protected]) መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ ምዕራባውያን የኢትዮጵያን ልጆች እያታለሉና እየደለሉ ከእምነታቸው ለመንጠቅ ሲቃጡ በ1951 ዓ ም ባሳተሙት ‘መድሎተ አሚን ወይም የሃማኖት ሚዛን ጥልቅ መጽሐፍ ሽፋን ላይ ሕዝብ ልቡናውን፣ ዓይኑን፣ ጀሮውንና

ሰው ሆይ!

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

Go toTop