December 19, 2023
3 mins read

እሳትና ውሀ – አልማዝ አሸናፊ

Prisonersከአልማዝ አሸናፊ
[email protected]
WYOMING, USA

ፀሐፊውን ወይም ፀሀፊዎቹን ባላውቅም ኢትዮጵያና ሕዝቦቿ ዛሬ ያሉበትን አስከፊ ሁኔታ የሚጦቁሙትን እነዚህን ገራሚ አጭር ግጥሞች ለዚህ ዌብሳይት አንባቢዎች ማካፈል ወደድኩኝ::

———————————————-

እሳትና ውሀ

የታፈነ ውሀ – በብረት ድስት ገብቶ
በጭቆና ሲኖር – ነፃነቱን አጥቶ

ስንት ስቃይ አይቶ – ታጋሽ ሆኖ ሳለ
አንድ ጉልበተኛ – እሳት የተባለ
ብረት ድስቱን ሊያግል – እየተቀጣጠለ
እራሱን አግዝፎ – ድንገት ከተፍ አለ::

ቃጠሎ ንዳዱ – ውሀው ሲበዛበት
የስቃዩ ማብቂያ – ጊዜው ሲረዝምበት
ትግስቱ ተሟጦ – የሚገነፍል ለት

የእሳቱ ግለት – ምን ያክል ቢከፋ
የታፈነው ውሀ – በምሬት ሲደፋ
ሀያሉም ነበልባል – አብሮት ነው ሚጠፋ::

(እሳት :- የአብይ አህመድ መንግስት
ውሀ:- የኢትዮጵያ ምስኪን ሕዝብ)

———————————————————————————————————————————-

ፓለቲካችን

ፖለቲካው ሆኖ~ቅጥ ያጣ ብልሹ
መስራት ስለሚከብድ~ገብተው ሳይቆሽሹ
ልበ ቀናዎቹ~አዋቂዎች ሸሹ።

ታዲያ ምን አገኘን~እኛ በምላሹ?

ፓለቲካ እያሉ~በግላቸው አሰራር
በዘመድ በገንዘብ~ሚሆኑ አመራር
ለራሳቸው ሚመች~መንገድ ሚቀልሱ
ሀላፊ ሆኑልን~ሰዉን ሊያጫርሱ።

(ሀላፊ የተባሉት አብይ አህመድና ሹማማምንቶቹ)

———————————————————————————————————————————

ጊዜ የሰጠው ቅል

እንዴት አንዘን~እንዴት አንከፋ
አጭሩ ረዝሞብን~ጉራውን ሲነፋ
ቀጭኑ ደረቱን~እኛ ላይ ሲያሰፋ
ሁሉም በየፊናው~ስልጣኑን ሊያሳየን~
ሚያደርገው ሲከፋ።

እኛም እንኖራለን~ጥርሳችን እየሳቀ~
ሁሉን በሆድ ይዘን
ጊዜ የሰጠው ቅል~ትልቁን ድንጋይ (ትልቋን ኢትዮጵያ)~
ልስበር ሲል እያየን።

(ቅል:- አብይ አህመድና ግብረአበሮቹ
እኛም:- የኢትዮጵያ ምስኪን ሕዝብ)

———————————————————————————————————————————

ከድጡ ወደ ማጡ

ሲበሉ አድርሰኝ
ሲጣሉ መልሰኝ
ብሎ ሁሌ ሲመኝ

ምኞቱ ተሰሳክቶ ~ የልቡ ሆኖለት
ከቦታዎች ርቆ ~ ፀቦች ከበዙበት
ሄዶ ይኖር ጀመር~ወደ ሚበላበት
መጥገብ በሌለበት
ሆድ ከማይሞላበት።

እናም የምኞቱ ~ መከራው እየባሰ
ሰላምን ፍለጋ ~ ወቶ እያሰሰ
ባለወንበሮቹ ~ ሲበሉ ደረሰ

ይብላኝልን !!

(ምኞተኛው:- የኢትዮጵያ ምስኪን ሕዝብ
በላተኞቹ :- አብይ አህመድና ሹማምንቶቹ)

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

ዳግማዊ ጉዱ ካሣ “ይድረስ ለእገሌ” ማለቱ ሰለቸኝና ተውኩት እንጂ ዛሬም መጻፍ የፈለግሁት የአማራን ዕልቂት ለመታደግና የኢትዮጵያን ትንሣኤ ለማብሰር እየተዋደቁ ላሉት ወገኖቼ ነው – በፋኖም ይሁን በሌላ ስም፡፡ ኢትዮጵያን ወደቀደመ ክብሯ ለመመለስ የነገድና

ጀልባዋ አትሰምጥም፤ የሚሰምጥ ግን አለ!

[ማስታወሻ ከፍል አንድ፣ በዘሐበሻ ድረ ገጽ ላይ ኦፍ ጃዋር አንድ ኢትዮጵያ ተብሎ በእንግልዝኛ ወጥቷል] (https://zehabesha.com/of-jawar-and-ethiopia/) ባለፈው ሰሞን፣ ጃዋር መሐመድ ከደረጀ ኃይሌ ጋር  በነገራችን ላይ ክፍል ሁለት ባደረገው ቃለ ምልልስ ላይ ተመስርቼ ገንቢ አስተያየት ጽፌ በኢንግሊዝኛው ዘሐበሻ ድረ ገጽ ላይ አሳትሜ ነበር። አስተያየቴ በዚህ ቃለ ምልልስ

ስለ ጃዋርና ኢትዮጵያ (ክፍል ሁለት)

January 20, 2025 ጠገናው ጎሹ የአቤ ጎበኛው አልወለድም ለወገኖቹ መብት መከበር ሲል ባደረገው ጥረት ምክንያት እንደ ወንጀለኛ ተቆጥሮ ይሙት በቃ በፈረዱበት ጊዜ በምላሳቸው መልካም  አድርጎ ስለ መገኘት እያወሩ በድርጊት ግን ተቃራኔውን የሚያደርጉ ሁሉ

ወዮ ለመከረኛው የአገሬ ህዝብ እንጅ  ታየማ ታየ ነው

መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ “ ሰው የሰነፎችን ዜማ ከሚሰማ ይልቅ የጠቢባንን ተግሣጽ መስማት ይሻለዋል። ”   — መክብብ 7፥5 እስቲ ቆም ብለን በማሰብ  ራሳችንን እንፈትሽ ።  እንደ ሰው ፣ የምንጓዝበት መንገድ ትክክል ነውን ? ከቶስ ሰው መሆናችንን እናምናለንን ? እያንዳንዳችን ሰው መሆናችንን እስካላመንን ጊዜ ድረስ ጥላቻችን እየገዘፈ

 ለሀገር ክብርና ብልፅግና ብለን ፤ ቆም ብለን በማሰብ ፤ ህሊናችንን ከጥላቻ እናፅዳ

                                                         ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)                                                       ጥር 12፣ 2017(January 20, 2025) ጆ ባይደን ስልጣናቸውን ለማስረከብ ጥቂት ቀናት ሲቀራቸው በአሜሪካን ምድር በጣም አደገኛ የሆነ የኦሊጋርኪ መደብ እንደተፈጠረና፣ የአሜሪካንንም ዲሞክራሲ አደጋ ውስጥ ሊጥለው እንደሚችል ተናግረዋል።  ጆ ባይደን እንዳሉት በተለይም በሃይ ቴክ

አሜሪካ ወደ ኦሊጋርኪ አገዛዝ እያመራ ነው! ጆ ባይደን ስልጣን ለመልቀቅ ጥቂታ ቀናት ሲቀራቸው የተናዘዙት!!

ከነፃነት ዘገዬ የአራት ኪሎው ኦነግ ሸኔ ከቁጥር ጋር እንደተጣላ ዕድሜውን አገባደደ፡፡ ኦነግ/ኦህዲድ ዛሬም ሆነ ዱሮ፣ በቤተ መንግሥትም ይሁን በጫካ ቁጥር ላይ ያለው አቋም ምን ጊዜም ያስደንቀኛል፡፡ ደግሞም እየባሰባቸው እንጂ ሲቀንሱ አይታዩም፡፡ ጥቂት

80 ቢሊዮን ብር ስንት ብር ነው?

በላይነህ አባተ ([email protected]) መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ ምዕራባውያን የኢትዮጵያን ልጆች እያታለሉና እየደለሉ ከእምነታቸው ለመንጠቅ ሲቃጡ በ1951 ዓ ም ባሳተሙት ‘መድሎተ አሚን ወይም የሃማኖት ሚዛን ጥልቅ መጽሐፍ ሽፋን ላይ ሕዝብ ልቡናውን፣ ዓይኑን፣ ጀሮውንና

ሰው ሆይ!

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

Go toTop