August 1, 2023
5 mins read

አማራ ነቅተህ ጠብቅ!  የከሀዲዎች አንድነት ፓርቲ ጆቢራ አማራን አዘናግቶ ለማስጨረስ ዛሬም  እየዞረ ነው!

በላይነህ አባተ ([email protected])

Amhara 2 1

በመላእክትነት ተመርጦ የነበረው ሳጥናኤል እግዚአብሔርን ከድቶና ክርስቶስን ወደ ተራራ ወስዶ ከተማ እያሳዬ በንብረት ሊደልለው ሞከረ፡፡ የሳጥናኤል ተከታዮች ደግሞ ከዓለም በፊት እግዚአብሔርን እያመለከ የኖረውን አማራ አንድነት፣ ህዳሴ፣ ግድብ፣ ዓባይ፣ ኢትዮጵያ ሱሴ ወዘተርፈ በሚሉ የቁማር ካርታዎች ሲያታልሉ ኖሩ፡፡  አማራ ክርስቶስን ስላለሆነ  ተታለለ፡፡

በቁማር መጫዋቻ ካርታ መደለሉ የሰለቸው አማራ ራሱን ለማዳን መሰባሰብ ሲጀምር ደሞ እንደተለመደው ከሀዲዎች የአንድነት ፓርቲ ያስፈልጋል የሚል ሌላ የክህደት ወጥመድ በማጥመድ ላይ ይገኛሉ፡፡

ሳጥናኤል አዙሮ የምያይበት አንገትና ይሉኝታ እንደሌለው ሁሉ እነዚህ የአንድነት ድስኩር አቀንቃኝ ከሀዲዎችም ትናንት የሰሩትን ዞር ብለው የሚያዩበት አንገት፣ እንደ አቡጀዲ የሸረከኩትን ውሽት የሚያፍሩበት ህሊናና ይሉኝታ የሳጥናኤል ያህል እንኳ የላቸውም፡፡

አማራ በእነዚህ ከሀዲዎች የአንድነት ድስኩር እየተታለለ ለሃምሳ ዓመታት ሳይደራጅ በምቅረቱ እየደረሰበት ያለውን የዘር ፍጅት ሰው ቀርቶ በደመ ነፍስ የሚንቀሳቀሱት እንሰሳትም ሊረዱት የሚችሉት ግፍ ነው፡፡

እነዚህ ድርጅት በማፍረስ ሰይጣን እንኳን የማይሰተካከላቸው ጉዶች ዛሬም እንደ ወትሮው አዙሮ የሚያዩበት አንገትና ሊያፍሩ የሚችሉበት ህሊና ወይም ይሉኝታ ስለሌላቸው ከምድር ላለመጥፋት በመዋደቅ ላይ ያለውን አማራ ሊያዘናጉ የአንድነት ፓርቲ የምትባል ቁማር እንደተለመደው ይዘው ብቅ አሉ፡፡ ዳሩ ዛሬም በዚህ ከሀዲዎች እንደገና ተጠልፎ የሚወደቅ  የአማራ የእንግዴህ ልጅ ምሁር ያጣሉ አይባልም፡፡ ህዳሴ፣ ግድብ፣ ዓባይ፣ ኢትዮጵያ፣ ሱሴ  አንድነት በሚሉ ይሁዳዊ ሰባኪያን የተንዘላዘሉና የተከንከረፈፉ ጅላጅል ምሁራን በዛሬው የአንድነት ፓርቲ ስብከትም እንደ ገለባ ተጠርገው የአማራ ማሳሳቱን አይቀጥሉም አይባልም፡፡

መጃጃል የማይሰለቻችሁ ምሁራን ሆይ! የወቅቱ የአማራ ትኩረት የመኖር ያለመኖር ትግል ነው፡፡ ህሊናና ይሉኝታ በሌላቸው ከሀዲዎች በአንድነት፣ በኢትዮጵያ፣ በአባይና በወደብ ስብከት መታለልና መጭበርበር በቃው!! አማራ ጊዜውን፣ እውቀቱን፣ ጉልበቱን፣ንብረቱንም ሆነ መንፈሱን ማዋል ያለበት ለራሱ ህልውና ብቻ ነው፡፡ አማራ እንደ ማርያም ጠላት በሚዋከብበት በዚህ ክፉ ዘመን የራሱ ልጅ እየተራበ ሌላውን አጎርሳለሁ የሚል፣ የራሱ እያረረበት የሌላውን የሚያማስል የእንግዴህ ልጅ ነው፡፡ ህዳሴ፣ ግድብ፣ ኢትዮጵያ፣ ሱሴ፣ አንድነት እያሉ የአማራ ምሁራንን ሲያጃጅሉ የኖሩት ቁማርተኞች ዛሬ ደሞ ለሃምሳ ዓመታት ሲጠለፍበትና ሲታረድበት የኖረውን የአንድነት ማዘናጊያ ወጥመድ አጥምደው አማራን ለመጥለፍና ለማስጨረስ እየተቅበዘበዙ  ነው፡፡

አማራ ነቅተህ ጠብቅ!  የከሀዲዎች አንድነት ፓርቲ ጆቢራ አማራን አዘናግቶ ለማስጨረስና ለመብላት ዛሬም እየዞረ ነው!

ዓባይን ማን መቼ ይገድበው? http://amharic.zehabesha.com/archives/126545

ፈንድ ፈንዳጅ ዲያስጶራ እባክህ ስማ! ለዘራፊዎች የማይነጥፍ ጥገት መሆንህ ይብቃ!  http://amharic.zehabesha.com/archives/176751

https://zehabesha.com/the-genesis-of-ethiopian-problems-the-ghion-river-and-eyerusalem/

ነሐሴ ሁለት ሺ አስራ አምስት ዓ.ም.

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

ከነፃነት ዘገዬ የአራት ኪሎው ኦነግ ሸኔ ከቁጥር ጋር እንደተጣላ ዕድሜውን አገባደደ፡፡ ኦነግ/ኦህዲድ ዛሬም ሆነ ዱሮ፣ በቤተ መንግሥትም ይሁን በጫካ ቁጥር ላይ ያለው አቋም ምን ጊዜም ያስደንቀኛል፡፡ ደግሞም እየባሰባቸው እንጂ ሲቀንሱ አይታዩም፡፡ ጥቂት

80 ቢሊዮን ብር ስንት ብር ነው?

በላይነህ አባተ ([email protected]) መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ ምዕራባውያን የኢትዮጵያን ልጆች እያታለሉና እየደለሉ ከእምነታቸው ለመንጠቅ ሲቃጡ በ1951 ዓ ም ባሳተሙት ‘መድሎተ አሚን ወይም የሃማኖት ሚዛን ጥልቅ መጽሐፍ ሽፋን ላይ ሕዝብ ልቡናውን፣ ዓይኑን፣ ጀሮውንና

ሰው ሆይ!

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

Go toTop