አማራ ሆይ! እንኳን በይሁዳዊና በኤፍሬም ይሳቃዊ ሽምግልና በእውነተኛ ሽምግልናም የህልውና ተጋድሎ ከዳር አይደርስም!

#image_title

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com)

እንደ ይህ አድግ ቁጥር አንድ ሁሉ በሕዝብ የቁጣ ማእበል የተጥለቀለቀው ይህ አድግ ቁጥር ሁለት ይሁዳዊ ሽምግልናን የወንበር ማስጠበቂያና የሕዝብ መጨፍጨፊያ መሳሪያ አድርጎ መጠቀም ተጀመረ ውሎ ኣድሯል፡፡  ክርስቶስ አእዋፍዋ የሆነውን ቅድስት ቤተክርስትያን ሳይቀር በይሁዳዊ የሽምግልና መሳሪያ ሊያጠፋ ተቀጣጥሎ የነበረውን ትግል  በይሁዳ ሽማግሌዎች አቀዝቅዞ ቤተክርስትያኗን እንደገና አደጋ ላይ ጥሏል፡፡

በታሪካዊትና መንፈሳዊት ኢትዮጵያ ሽምግልና ከእውነተኛ ችሎት እጅግ የበለጠ ርትኡ ፍርድ የመስጥትና ዘላዊ ሰላምን የማስፈን መለኮታዊ ሀይል ነበረው፡፡ የኢትዮጵያን መንፈሳዊና ባህላዊ እሴቶች እየጠራረገ የሰይጣንን የቅጥፈት፣ የሌብነት፣ የአውሬነትና የጭራቅነት መንፈስ ሲሰራና ሲተክል የኖረው ይሁዳው ይህ አድግ ከመጣ ጀምሮ ሽምግልና ተበዳይን ከበዳይ እግር የሚያስደፋና የሕዝብ መጨፍጨፊያ መሳሪያ ሆኗል፡፡

ይህ አድግ ቁጥር አንድ ኤፍሬም ይስሀቅን የይሁዳዊ ሽምግልና መሪ ተዋናይ አድርጎ እደተጠቀመበት ሁሉ  በአምስት ዓመታት ውስጥ ወድ ሶስት ሚሊዮን ሕዝብ የጨፈጨፈና ያስጨፈጨፈው ከአስር ሚሊዮን ሕህዝብ በላይ ስደተኛ ያደረገው ይህ አድግ ቁጥር ሁለት ደሞ ስለሽምግልና ምንም የማያውቁትን ሆደ ኣደሮች የአማራ ሕዝብ መጨፍጨፊያ መሳሪያ አድርጎ መጠቀሙን እንደ ቀጠለ ነው፡፡

እንደነዚህ ዓይነት ለሕዝባቸው ደንታ የሌላቸው ባንዳ ሆዳሞች ጣሊያንም ሽማግሌ እያደረገ ወደ ፋኖዎች በአምስቱ ዘመን የአማራ ትግል ውስጥ ይልካቸው እንደነበር ታሪክና ትውልድ የሚያውቀው ነው፡፡ እንደነዚህ ዓይነት የታሪክ አተላ የሆኑ ሽማግሌ ነን ባይዎችን መና አርጎ ያስቀራቸው በዘመኑ የነበረው ፋኖና ደጀኑ ሕዝብ ነው፡፡ አማራ የህልውና ተጋድሎ በሚያደርግበት ወቅት የህልውና ትግሉን አደናቅፎ እርስት አልባ የሚያደርግና ተምድረ ገጥ እንዲጠፋ የሚያዘናጋ ሊያጠፉት ከተነሱት ጭራቆችም የከፋ ነው፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  “ታላቋ ትግራይን” የመመስረት የ 21 ዓመታት ጉዞ

እምነት ቀርቶ የአውሬ ያህል እንኳ የደመነፍስ ባህሪ ካልፈጠረባቸው የይህ አድግ አረመኔዎች በሽምግልና በኩል እርቅን፣ ፍትህንና ሰላምን መጠበቅ ከሳጥናኤል በረከትን ተጭራቅ ርህራሄን እየጠበቁ ሲንዘላዘሉ እንደመኖር ነው፡፡

አማራ ሆይ! እንኳን በይሁዳዊያን በኤፍሬም ይሳቃዊ ሽምግልና በእውነተኛ ሽምግልናም የህልውና ተጋድሎ ተዳር አይደርስም፡፡  በሽምግልና ህልውናውም ሆነ ነጣነቱን ያረጋገጠ ሕዝብ በዓለም የለም፡፡ አያቶችህም ይኸንን አላሳዩህም፤ አላስተማሩህም፡፡ ህልውናን የማረጋገጥ ትግል እንኳን ሰው ከትል እንደ አንበሳ ያሉ እንሰሳት የሚያደርጉት መንፈሳዊና አካላዊ ትግል ነው፡፡ አማራን እርስት አልባ ለማድረግና ለማጥፋት እየተኪያሄደ ያለው የአረመኔዎች ዘመቻ እንቅልፍ ሳይነሳው ሆዱን ሲቆዝር ኖሮ ትቢያ የሚሆን አማራ ከትልም ያነሰ ነው፡፡ አማራ እየደረሰበት ያለው እርስት አልባ የመሆንና የመጥፋት አደጋ እንኳን በቁም ያለን የሞተን አማራም ተመቃብር የሚቀሰቅስ ነው፡፡

 

ግንቦት ሁለት ሺ አስራ አምስት ዓ.ም.

 

 

 

2 Comments

  1. አማራ አካባቢ ይሄ ሽምግልና የሚባል ቀልድ ከየት የመጣ ነው? አሳምነው ጽጌ የኢትዮጵያ ልጅ ነገር ከጅምሩ የገባው አባቶች ተሰብሰቡ ይሄ ሽምግልና የሚባለውን እያነሳችሁ ትግሉ ላይ ውሃ አታፍስሱ ብሎ አስጠንቅቆ ነበር ቀጥሎም ሲሆን እንደ ትግሬዎች ጦሩን አደፋፍሩ ከህዝባችሁ ጎን ቁሙ ነበር ያለው ይህ ቀድሞ ነገር እንደገባው ወገናችን ሆኖም ሃሳቡን ቀድሞ የተረዳው አብይ ቀድሞ ቀለበው “ያስተላለፈው መልእክት በህይወት እንዳይያዝ” የሚል ነበር። አብይ ወንጀሉን እየጨመረበት በህይወት አለ አሳምነው ግን ለተቀደሰ አላማ ቁሞ ነብሱ በግፈኞች ቢነጠቀም ነብሱ በህዝብ ልብ ውስጥ ሰፍራለች። አብይ በዚህ ደረጃ አማራውን ከጠላው ወ/ሮ ዝናሽ ታያቸው የጎንደር ኦሮሞ
    ካልሆኑ እንዴት ህዝባቸው እንዲህ ሲሰቃይ እንደ አዜብ መስፍን ምንም ያልመሰላቸው? ያንን የወንጀል ቤተ መንግስት ለቅቀው አገሩንም ጥለው ነብሳቸውን ያሳርፉ የሰውዬው ነብስ በተለዩ ሃይሎች ተይዟል ካሁን በኋላም ጥፋት ላይ ጥፋት ይጨምር እንደሁ እንጅ ወደ ሰውነት አይመለስም። ደቀ መዝሙሩ እንደ መምህሩ ነው ነገሩ የመለስ፤የስብሃይት ነጋ፤የበረክት ስሞን የነብስ ልጅ አይደል። አብይ በወ/ሮ ዝናሽ ላይ ያለውን ጥላቻ ቀደም ሲል ፕሮፌሰር መስፍን አረጋ በምሁራዊ ትንታኔው አቅርቦታል ጎግሎ መመልከት ነው።

  2. አማራና የሰብአዊ መብት ተከራካሪዎች (የኢትዮጵያ ሰብ አዊ መብትን ጠባቂ አላልኩም የነሱ ስራ ተከድኖ ይብሰል) እነ ስብሃት ነጋ ተለቅቀው አቶ ታዲዮስ ታንቱ በዚህ እድሜያቸው መከራቸውን እየበሉ ስለሆነ ዝም ማለታችን ከምን የመጣ ነው? አቶ ታዲዮስ ታንቱ አማራ ያልበደለኝ በደል የለም እያሉ ሌት ከቀን ቢያጎኑት አዳነች አቤቤ የተንጣለለ ቤት ሽመልስ አብዲሳ ቪ8 መኪና ጁዋር መሃመድ ተቆራጭ ባደረገላቸው ነበር ነገር ግን እኝህ አባት ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ ስላሉ በዚህ እድሜያቸው እግራቸውን አፍታተው እንዳይኖሩ ይህ ሁሉ ግፍ ደርሶባቸዋል ጀግኖቻችንን ካልቆምንላቸው ለኢትዮጵያ ማን ይቆምላታል?

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share