የሰርፀ ፍሬስብሃት ምስክርነት ለዳዊት ፍሬው

#image_title

ይህንን አስደንጋጭ መርዶ ለማመን ሰዓታት ፈጅቶብኛል። ዳዊት ፍሬው ወደ ጣሊያን ለመጓዝ ዝግጅት ላይ እያለ፣ ለጣሊያን ኤምባሲ የድጋፍ ደብዳቤ እንድጽፍለት ሊጠይቀኝ ያለሁበት ድረስ መጣ። በጣም ግሩም በኾነ የተነቃቃ ስሜት ጣሊያን የሚኖሩትን የኮንሠርት መድረኮች ዘረዘረልኝ። ጣሊያን ሀገር ነዋሪ የኾኑ የኢትዮጵያ ‘ኮምዩኒቲ’ አባላት በምን ዓይነት ጉጉት እየጠበቁት እንደኾነም ነገረኝ።

የዳዊትን ጨዋታ ዐዋቂነት የምታውቁት የምትመሰክሩት ነው። ሙዚቃዊ ቀልዶቹን እያከታተለ ነግሮኝ በጣም አሳቀኝ። ደብዳቤውን ጽፌ ሠጠሁት። ከዚያ በኋላ የደወለልኝ ለጉዞው አንድ ቀን ሲቀረው ነበር። ሞቅ ባለ ስሜት እና በመድረክ ጉጉት ስሜት ተሰናበተኝ።

ከዚያች ዕለት በኋላ እጠብቅ የነበረው፣ የመድረክ ቪዲዮዎቹን ነበር። ከቶውንም ያላሰብኩትን የዛሬውን የድንገተኛ ኅልፈቱን ዜና ሰማሁ።

#image_title

***

ዳዊት ፍሬው ኃይሉ በያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት የሙዚቃ ትምህርቱ ‘ሜጀር’ ያደረጋትን ክላሪኔትን የምር የሙጥኝ ያለ ድንቅ ሙዚቀኛ ነበር። አልቶ ሳክስፎን እና ክራር የሚጫወት ቢኾንም፣ ለክላሪኔት የነበረው ፍቅር፣ ከጋሽ ወዳጄነህ ፍልፍሉ(ነፈስ ኄር) እና ከጋሽ መርዓዊ ሥጦት ጋር የሚያመሣሰለው ነበር።

በሙዚቃ ትምህርት ቤት ቆይታው፣ የታላላቅ ኮምፖዘሮችን የክላርኔት standard concerto’ዎች’ ተጫውቷል። መምህሩ ፈለቀ ኃይሉ የሚያደንቀው እና የሚያበረታታው ተማሪው ነበር።

ከተማሪ ቤት እንደወጣ፣ኢትዮጵያብሔራዊ ቴአትር ቢግ ባንድ ውስጥ በክላሪኔት እና አልቶ ሳክስ ተጫዋችነት ለተወሰኑ ዓመታት አገልግሏል። በቴአትር ቤት ቆይታው፣ በግሉ፥ የመጀመሪያውን “ኢንስትሩሜንታል” አልበም፣ በፈለቀ ኃይሉ አቀናባሪነት ለማሳተም ችሏል።

ከ2000 ዓ.ም. እስከ 2004 ዓ.ም. ድረስ፣ በግሩም መዝሙር ከተቋቋመው የ”ዐዲስ አኩዊስቲክስ” ባንድ ጋር አልበም እና በበርካታ ሀገራት ኮንሰርት የማቅረብ ዕድል አገኘ። በኢትዮጵያዊ ቅላፄ በተዋበው የክላሪኔት አጨዋወቱ የተደነቁ ጋዜጠኞች “The Guardian” እና “Independent” ጋዜጦች ሰፊ የአድናቆት ዘገባ ጽፈውለታል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የወያኔ ትግሬዎች ቅዠት ዳግም በጦርነት አዲስ አበባ እንገባለን የሚል ነው - ነዓምን ዘለቀ

ከ2004 እስከ 2014 ዓ.ም. በተከታታይ ሦስት የመሣሪያ ቅንብር ሥራዎችን በአልበም አሳትሟል። 2006 ዓ.ም. ላይ፣ በታላቁ ሙዚቀኛ እና መምህር በተቋቋመው “Retrieve Ethio Big Band” ላይ በአልቶ ሳክስፎን ተጫዋችነት የተደነቁ ታላላቅ መድረኮች ላይ ተጫውቷል።

ኮቪድ 19 በተከሰተበት ወቅት፣ ወጣቱ ሙዚቀኛ ኢዩኤል መንግሥቱ በልዩ ኹኔታ ባቀናበረው “ቅኔ ነው ሀገር” በተሰኘው የኦርኬስትራ እና ኳየር ቅንብር የሙዚቃ ሥራ ላይ በክላሪኔት ተጫዋችነት ተሳትፏል።

ዳዊት ከዓለም ታላላቅ ክላርኔቲስቶች ጋር በመድረክ የመጫወት ዕድልም ነበረው። ለአብነት ያህል፥ በአሊያን ኢትዮ ፍራኔሲስ የሙዚቃ ፌስቲቫል መድረክ ላይ፣ ከ”Ether Orchestra” አባላት ጋር ተጫውቷል።(የኔ ሐሳብ የተሰኘችው የግርማ ነጋሽን ሙዚቃ የመድረክ ሥራ ያስታውሷል)፣ በዓለም እጅግ ገናና ስም ካላቸው ክላርኔቲስቶች አንዱ ከኾነው ከፓኩዊቶ ዴሪቬራ ጋር በያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት መድረክ ላይ፣ “አምባሰልን” ተጫውቷል።

ክላሪኔትን ኢትዮጵያዊ ዐንደበት ከሠጧት ታዋቂ ኢትዮጵያውያን መካከል፣ የዘመናችን ዕንቁ ሙዚቀኛ ኾኖ በመድረክም በአልበምም የታየው ዳዊት ፍሬው ኃይሉ፣ ብዙ ሊሠራ ባቀደበት፣ ብዙ ውጥኖቹንም ባደራጀበት በዚህ ወቅት፣ በ44 ዓመት ዕድሜው ይህችን ዓለም በሞት መለየቱ ከልብ ያሳዝነኛል። ልብ የሚሰብር ኀዘን ነው የተሰማኝ።

ለወዳጅ ዘመዶቹ፣ ለሙያ አጋር ጓደኞቹ እና የአድናቂዎቹ መጽናናትን እመኛለሁ። ነፍስ ኄር

DireTube

 

 

2 Comments

  1. ሞተና ቀበሩት ዓይነት ዜና መስማት ሰልችቶናል። ለምን ሞተ? እንዴት ሞተ? የሚለውን የሚተነትን ዘገባ አስፈላጊ ነው። አውቃለሁ እርግጥ ነው በአፓርታይዷ ኢትዮጵያ እውነትን ፈልፍሎ ማውጣት ዘብጥያ ያስወርዳል። ዋናው ጥያቄ ያመው ነበር ወይ ጉዳዪን ለማጣራት የመጨረሻ ቀኑን (24 ሰአቱን) ወደ ኋላ ተመልሶ ከእነማን ጋር እንደነበረ ማረጋገጥና ነገሩን መመርመር ያስፈልጋል። ከዚህም በዘለለ የአስከሬን ምርመራ ማድረጉ አስፈላጊ ነው። የዳዊትን ህልፈት ከእውቁ የበረሃ ከያኔ ከኢያሱ በርሄ ጋር አመሳስለዋለሁ። የእርሱም አማሟት እንዲሁ ድንገት ነው ተብሎ በዚያው ተለባብሶ ነው የቀረው። በሰው እጅ ወይም በመንግስት ሥራ ዳዊት ተገድሎ ከሆነ ገዳዪ ክፍል ከሞቱ የሚያተርፈው ምንድን ነው በማለት መጠየቅ አስፈላጊ ነው።
    በሃበሻው መሬት ገዳዪና አስገዳዪ፤ የሟች ዘመድና ጎረቤት አብረው የሚያለቅሱበት የዝብርቅ ጊዜ ላይ ነን። ገዳዪ በአልቃሹ በልቡ ሲስቅ ከልቡ የሚያለቅሰው ደግሞ የማያባራ እንባውን እንደ ሃምሌ ዝናብ ያጎርፈዋል። መርጦ አልቃሾችና መርጦ ሃዘን ደራሾች ባሉበት በዚህ በዘርና በቋንቋ በተሰነጠቀ ህብረተሰብ መሃል ሰው ሆኖ ለሰውነት ማልቀስና የእርዳታ እጅ መዘርጋት ውስብስብ እየሆነ መጥቷል። በዘራቸው የሰከሩ የኦሮሞ፤ የወያኔና የአማራ ጥርቅሞች ቆመንለታል በሚሉት ህዝብ እየነገድ ይኸው እንሆ ዛሬም ትላንትም ህዝባችን ምጽዋት ተቀባይ አድርገውታል። በተለይ የኦሮሞው ብልጽግና (ድህነት) ፓርቲ ወደ ስልጣን ከመጣ ወዲህ በሃገሪቱ ካህን በፓሊስ በጥፊ ሲመታ፤ ቤ/ክርስቲያን ሲቃጠል፤ የጳጳስ መቁጠሪያና ቆብ ሽንት ቤት ሲከተት አይተናል/ሰምተናል። ይህ የጅምላ መንጋ የሚያስበው በዘፈቀደ በመሆኑ ሰውን ለስብሰባ ጠርቶ በመትረጌስ የሚጨርሽ ጭራሽ አረመኔ የኦሮሞ ስብስብ በሻሸመኔ የነፍሰጡር ሆድ ቀዶ እናትን የገደለ፤ በአርሲ፤ በሃረር፤ በጂማ እንዲሁም የአማራ ደም እንደ ጎርፍ በሚፈስባት ወለጋ ይህ ነው የማይባል ኢ- ሰብአዊ ግፍ እየፈጸመ የዛሬ መቶ አመት ሚኒሊክ ፈረሳችን ቀማን እያለ የሚቃዥ የእብድ ስብስብ ነው። የዛሬው የኦሮሞ ጽንፈኞች እብደት ከሰው ተራ የወጣ ፍጽም አውሬነት ነው። አሁን በክብር ለሰላም ድርድር ዳሬሰላም ላይ የተጠራው የኦነግ ሸኔ ታጣቂ የጠ/ሚሩን ጅልነት ስለተመለከተና እንዲሁም ከህዋላ ልክ እንደ ወያኔ ለሚገፉት ሃይሎች ለመታዘዝ በኦሮሚያ ክልል ሪፈረንደም ይደረግ በማለቱ ስብሰባው ያለ ውጤት መበተኑን ተባራሪ ወሬዎች አናፍሰውታል። የሃበሻዋ ምድር ግፍ ያለማቋረጥ የሚወርድባት የመናገር፤ የመጻፍ፤ የመሰብስብ የሰው ልጆች መብት የተገፈፈባት እንዲሁ በዲስኩርና የለበጣ ዜና እያጋቱ ህዝቡ የሚያደነዝዙባት ምድር ናት። ዛሬ በመናገራቸው፤ በመጻፋቸው፤ የመንግስት እርምጃ የተሳሳተ ነው በማለታቸው የተገደሉ፤ ታፍነው የተደበደቡ፤ በእስር የሚማቅቁ፤ በስውር የት እንደገቡ የማይታወቁ ስንቶች እንደሆኑ ልብ ያለው ያስተውላል። ስንት የሃገር ንብረት የዘረፉትንና የሰሜን ጦርን በተኛበት እንዲመታ ያደረጉትን መሪዎች አቅፎ አሁን ዘመቻውን አማራ ህዝብ ላይ ያደረገው የአብይ መንግስት የሚይዘው የሚጨብጠውን ያጣ በየደረሰበት ሁሉ ቀለም የተቀቡ ቃሎችን የሚረጭ ኦናውን የቀረ መንግስት ነው። የሞትም ሆነ የመሰደድ ዜናው ሁሉ ከዚህ የጥላቻ ፓለቲካ ጋር የተያያዘ እንደሆነ አርጌ ነው የምቆጥረው።
    ብልጽግና የወያኔ የእንግዲህ ልጅ ነው። የአፈና የግድያ ስልቱ ሁሉ ከዚያው ከልመና ኮሮጆ የተወሰደ ነው። በመኪና ገጭተው ይገላሉ፤ በመርዝ ያጠፋሉ፤ በሃኪም ያስገድላሉ፤ ብቻ የሚገድሉበት መንገድ ብዙ ነው። ስለሆነም የዳዊት ፍሬው ሃይሉ ሞት አስደንጋጭ ቢሆንም በምን ምክንያት እንደሞተ እስካላወቅን ድረስ ሞቱ ሞት ብቻ ሆኖ ነው የሚቀረው።

  2. Tesfa ሁሉንም ጉዳይ በአጭር ጽሁፍ ገልጸሀዋል እናመሰግናለን፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share