May 5, 2023
6 mins read

የሰርፀ ፍሬስብሃት ምስክርነት ለዳዊት ፍሬው

345126033 779679093461791 7138466439801558559 n
#image_title

ይህንን አስደንጋጭ መርዶ ለማመን ሰዓታት ፈጅቶብኛል። ዳዊት ፍሬው ወደ ጣሊያን ለመጓዝ ዝግጅት ላይ እያለ፣ ለጣሊያን ኤምባሲ የድጋፍ ደብዳቤ እንድጽፍለት ሊጠይቀኝ ያለሁበት ድረስ መጣ። በጣም ግሩም በኾነ የተነቃቃ ስሜት ጣሊያን የሚኖሩትን የኮንሠርት መድረኮች ዘረዘረልኝ። ጣሊያን ሀገር ነዋሪ የኾኑ የኢትዮጵያ ‘ኮምዩኒቲ’ አባላት በምን ዓይነት ጉጉት እየጠበቁት እንደኾነም ነገረኝ።

የዳዊትን ጨዋታ ዐዋቂነት የምታውቁት የምትመሰክሩት ነው። ሙዚቃዊ ቀልዶቹን እያከታተለ ነግሮኝ በጣም አሳቀኝ። ደብዳቤውን ጽፌ ሠጠሁት። ከዚያ በኋላ የደወለልኝ ለጉዞው አንድ ቀን ሲቀረው ነበር። ሞቅ ባለ ስሜት እና በመድረክ ጉጉት ስሜት ተሰናበተኝ።

ከዚያች ዕለት በኋላ እጠብቅ የነበረው፣ የመድረክ ቪዲዮዎቹን ነበር። ከቶውንም ያላሰብኩትን የዛሬውን የድንገተኛ ኅልፈቱን ዜና ሰማሁ።

345432688 231672129507861 2870527417254705875 n
#image_title

***

ዳዊት ፍሬው ኃይሉ በያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት የሙዚቃ ትምህርቱ ‘ሜጀር’ ያደረጋትን ክላሪኔትን የምር የሙጥኝ ያለ ድንቅ ሙዚቀኛ ነበር። አልቶ ሳክስፎን እና ክራር የሚጫወት ቢኾንም፣ ለክላሪኔት የነበረው ፍቅር፣ ከጋሽ ወዳጄነህ ፍልፍሉ(ነፈስ ኄር) እና ከጋሽ መርዓዊ ሥጦት ጋር የሚያመሣሰለው ነበር።

በሙዚቃ ትምህርት ቤት ቆይታው፣ የታላላቅ ኮምፖዘሮችን የክላርኔት standard concerto’ዎች’ ተጫውቷል። መምህሩ ፈለቀ ኃይሉ የሚያደንቀው እና የሚያበረታታው ተማሪው ነበር።

ከተማሪ ቤት እንደወጣ፣ኢትዮጵያብሔራዊ ቴአትር ቢግ ባንድ ውስጥ በክላሪኔት እና አልቶ ሳክስ ተጫዋችነት ለተወሰኑ ዓመታት አገልግሏል። በቴአትር ቤት ቆይታው፣ በግሉ፥ የመጀመሪያውን “ኢንስትሩሜንታል” አልበም፣ በፈለቀ ኃይሉ አቀናባሪነት ለማሳተም ችሏል።

ከ2000 ዓ.ም. እስከ 2004 ዓ.ም. ድረስ፣ በግሩም መዝሙር ከተቋቋመው የ”ዐዲስ አኩዊስቲክስ” ባንድ ጋር አልበም እና በበርካታ ሀገራት ኮንሰርት የማቅረብ ዕድል አገኘ። በኢትዮጵያዊ ቅላፄ በተዋበው የክላሪኔት አጨዋወቱ የተደነቁ ጋዜጠኞች “The Guardian” እና “Independent” ጋዜጦች ሰፊ የአድናቆት ዘገባ ጽፈውለታል።

ከ2004 እስከ 2014 ዓ.ም. በተከታታይ ሦስት የመሣሪያ ቅንብር ሥራዎችን በአልበም አሳትሟል። 2006 ዓ.ም. ላይ፣ በታላቁ ሙዚቀኛ እና መምህር በተቋቋመው “Retrieve Ethio Big Band” ላይ በአልቶ ሳክስፎን ተጫዋችነት የተደነቁ ታላላቅ መድረኮች ላይ ተጫውቷል።

ኮቪድ 19 በተከሰተበት ወቅት፣ ወጣቱ ሙዚቀኛ ኢዩኤል መንግሥቱ በልዩ ኹኔታ ባቀናበረው “ቅኔ ነው ሀገር” በተሰኘው የኦርኬስትራ እና ኳየር ቅንብር የሙዚቃ ሥራ ላይ በክላሪኔት ተጫዋችነት ተሳትፏል።

ዳዊት ከዓለም ታላላቅ ክላርኔቲስቶች ጋር በመድረክ የመጫወት ዕድልም ነበረው። ለአብነት ያህል፥ በአሊያን ኢትዮ ፍራኔሲስ የሙዚቃ ፌስቲቫል መድረክ ላይ፣ ከ”Ether Orchestra” አባላት ጋር ተጫውቷል።(የኔ ሐሳብ የተሰኘችው የግርማ ነጋሽን ሙዚቃ የመድረክ ሥራ ያስታውሷል)፣ በዓለም እጅግ ገናና ስም ካላቸው ክላርኔቲስቶች አንዱ ከኾነው ከፓኩዊቶ ዴሪቬራ ጋር በያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት መድረክ ላይ፣ “አምባሰልን” ተጫውቷል።

ክላሪኔትን ኢትዮጵያዊ ዐንደበት ከሠጧት ታዋቂ ኢትዮጵያውያን መካከል፣ የዘመናችን ዕንቁ ሙዚቀኛ ኾኖ በመድረክም በአልበምም የታየው ዳዊት ፍሬው ኃይሉ፣ ብዙ ሊሠራ ባቀደበት፣ ብዙ ውጥኖቹንም ባደራጀበት በዚህ ወቅት፣ በ44 ዓመት ዕድሜው ይህችን ዓለም በሞት መለየቱ ከልብ ያሳዝነኛል። ልብ የሚሰብር ኀዘን ነው የተሰማኝ።

ለወዳጅ ዘመዶቹ፣ ለሙያ አጋር ጓደኞቹ እና የአድናቂዎቹ መጽናናትን እመኛለሁ። ነፍስ ኄር

DireTube

 

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

የድሮ መሪዎች ያላደረጉትን ምሁር ጳጳሳቱ ያላስተዋሉትን ከፈረሰች ጎጆ ከባልቴት ቤት ገብቶ ክብሩን ዝቅ አድርጎ ውሀዋን ጠጥቶ ምግቧንም ተጋርቶ ያላለቀሰ ሰው ያንን ትይንት አይቶ ማን ይኖራል ከቶ? በዉሸት ፈገግታ ፊቱን አስመስሎ ፀሀይ የበራበት

ሰው በሰውነቱ – ከ ይቆየኝ ስሜ

የአማራ ፋኖ በጎጃም ምክትል የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ የነበረው እና አሁን ላይ በአማራ ፋኖ በጎጃም የሁለተኛ (ተፈራ ) ክፍለጦር ሰብሳቢ የነበረው ፋኖ ዮሐንስ አለማየሁ በክብር ተሰዋ። የአማራ ህዝብ የተጋረጠበትን የህሎና አደጋ ለመቀልበስ ያለ

ከአማራ ፋኖ በጎጃም የተሰጠ የሐዘን መግለጫ ታጋይ ይሰዋል ትግል ይቀጥላል !

January 22, 2025
ዳግማዊ ጉዱ ካሣ “ይድረስ ለእገሌ” ማለቱ ሰለቸኝና ተውኩት እንጂ ዛሬም መጻፍ የፈለግሁት የአማራን ዕልቂት ለመታደግና የኢትዮጵያን ትንሣኤ ለማብሰር እየተዋደቁ ላሉት ወገኖቼ ነው – በፋኖም ይሁን በሌላ ስም፡፡ ኢትዮጵያን ወደቀደመ ክብሯ ለመመለስ የነገድና

ጀልባዋ አትሰምጥም፤ የሚሰምጥ ግን አለ!

[ማስታወሻ ከፍል አንድ፣ በዘሐበሻ ድረ ገጽ ላይ ኦፍ ጃዋር አንድ ኢትዮጵያ ተብሎ በእንግልዝኛ ወጥቷል] (https://zehabesha.com/of-jawar-and-ethiopia/) ባለፈው ሰሞን፣ ጃዋር መሐመድ ከደረጀ ኃይሌ ጋር  በነገራችን ላይ ክፍል ሁለት ባደረገው ቃለ ምልልስ ላይ ተመስርቼ ገንቢ አስተያየት ጽፌ በኢንግሊዝኛው ዘሐበሻ ድረ ገጽ ላይ አሳትሜ ነበር። አስተያየቴ በዚህ ቃለ ምልልስ

ስለ ጃዋርና ኢትዮጵያ (ክፍል ሁለት)

January 20, 2025 ጠገናው ጎሹ የአቤ ጎበኛው አልወለድም ለወገኖቹ መብት መከበር ሲል ባደረገው ጥረት ምክንያት እንደ ወንጀለኛ ተቆጥሮ ይሙት በቃ በፈረዱበት ጊዜ በምላሳቸው መልካም  አድርጎ ስለ መገኘት እያወሩ በድርጊት ግን ተቃራኔውን የሚያደርጉ ሁሉ

ወዮ ለመከረኛው የአገሬ ህዝብ እንጅ  ታየማ ታየ ነው

መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ “ ሰው የሰነፎችን ዜማ ከሚሰማ ይልቅ የጠቢባንን ተግሣጽ መስማት ይሻለዋል። ”   — መክብብ 7፥5 እስቲ ቆም ብለን በማሰብ  ራሳችንን እንፈትሽ ።  እንደ ሰው ፣ የምንጓዝበት መንገድ ትክክል ነውን ? ከቶስ ሰው መሆናችንን እናምናለንን ? እያንዳንዳችን ሰው መሆናችንን እስካላመንን ጊዜ ድረስ ጥላቻችን እየገዘፈ

 ለሀገር ክብርና ብልፅግና ብለን ፤ ቆም ብለን በማሰብ ፤ ህሊናችንን ከጥላቻ እናፅዳ

Go toTop