ያማራ ፋኖ ሆይ፣ ውሻን በርግጫ መምታት እንካ ሥጋ ማለት ነው

ጭራቅ አሕመድ ባምስት ዓመት የስልጣን ዘመኑ ከወያኔ ጋር በሕቡዕ በመተባበር በቀጥታና በተዛዋሪ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ አማሮችን ጨፍጭፏል፣ አስጨፍጭፏል፡፡  ጭራቁ ግን በኦነጋዊነት ያበደ፣ በልቶ የማይጠግብ የቀን ጭራቅ ስለሆነ፣ አማራን ሙልጭ አድርጎ እስከሚብላ ድረስ አይጠረቃም፣ አይረካም፡፡  ስለዚህም ከወያኔ ጋር በስውር መተባበሩ ቀርቶ በግልጽ በመተባበር በአማራ ሕዝብ ላይ ግልጽ ጦርነት ከፍቷል፡፡

ግልጽ ጦርነቱን የከፈተው ደግሞ ምዕራባውያን ጌቶቹ በተለይም ደግሞ አሜረቃና እንግሊዝ በሰጡት ቀጭን ትዕዛዝና በሚያደርጉለት ከፍተኛ ቁሳዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ዲፕሎማሲያዊና ፕሮፓጋንዳዊ ድጋፍ በመተማመን ነው፡፡  የጦርነቱ ዓላማ ደግሞ ቢቻል አማራን ሙሉ በሙሉ በማጥፋት ከኢትዮጵያ ፖለቲካ ሙሉ በሙሉ ማስወገድ፣ ባይቻል ደግሞ ትልቁን የአማራን ሕዝብ ሕዳጥ (አናሳ) ብሔረሰብ በማድረግ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ላይ የሚጫወተውን ሚና ኢምንት ማድረግ ነው፡፡

ምዕራባውያን ነጭ ላዕልተኞች አማራን ከኢትዮጵያ ፖለቲካ ማስወገድ የሚፈልጉበት ምክኒያት ደግሞ አምርረው የሚጠሉትን ኢትዮጵያዊ ብሔርተኝነትን ድርና ማግ ሆኖ ያስተሳሰረው ያማራ ሕዝብ በመሆኑ ነው፡፡  ኢትዮጵያዊ ብሔርተኝነትን አምርረው የሚጠሉት ደግሞ የጦቢያን ሕዝብ በነቂስ በማነሳሳት ያድዋን ድል ያስገኘው፣ የጥቁር ሕዝብ ኩራትና ልዕልና መሠረት የሆነው፣ ይህ አጼ ምኒሊክ ዋና ምልክቱ የሆኑት አፍሪቃዊ ብሔርተኝነት በመሆኑ ነው፡፡  ያማራ ሕዝብ ከኢትዮጵያ ፖለቲካ ከተወገደ፣ ኢትዮጵያዊ ብሔርተኝነት ይሞታል፡፡  ኢትዮጵያዊ ብሔርተኝነት ከሞተ ደግሞ ኢትዮጵያ የነጭ ላዕልተኞች መጫወቻ ትሆናለች፡፡  ያፍሪቃ መዲና የሆነችው ኢትዮጵያ የነጭ ላዕልተኞች መጫወቻ ከሆነች ደግሞ መላዋ አፍሪቃም የነጭ ላዕልተኞች መጫወቻ ትሆናለች፡፡

ስለዚህም ያማራ ሕዝብ ሆይ፣ ግልጽ ጦርነት የከፈተብህ ጭራቅ አሕመድ ቢሆንም፣ የጦርነቱ የበላይ አዛዦች ግን ምዕራባውያን በተለይም ደግሞ እንግሊዝና አሜሪቃ ናቸው፡፡  ጦርነቱን ሊያካሂዱት ያሰቡት ደግሞ ለኦነግና ለወያኔ ፀራማራ ጥምር ጦር ቀጥተኛ የሳተላይት መረጃ (real time satellite information) በመስጠት ያማራን ሕዝብ በከባድ መሣርያ እየደበደቡ፣ በተለይም ደግሞ በንቦቴ (drone) እየነቦድምጥማጡን ለማጥፋት ነው፡፡   በመሆኑም፣ ይህን ባሜሪቃና በእንግሊዝ ጀነራሎች የሚመራ ፀራማራ ጥምር ጦር ፊት ለፊት መግጠም፣ የእሳት ራት ከመሆን ውጭ ፋይዳ የሌለው አጉል ጀብደኝነት ነው፡፡

ስለዚህም ያማራ ፋኖ ይህን ፀራማራ ጥምር ጦር መግጠም ያለበት በደፈጣና በደፈጣ ብቻ ነው፡፡  ለዚህ የደፈጣ ውጊያ ግብአት ይሆነው ዘንድ ደግሞ ያያቶቹን ያርበኝነት ዘመን ትግል ማስታወሱ ብቻ ይበቃዋል፡፡  ያርበኝነት ዘመን ፋኖወች ጣልያንን ያርበደብዱ የነበሩት፣ ያገራቸውን ዱር፣ ተራራና ሸንተርር ተገን በማድርግ መሠረታዊ የደፈጣ ውጊያ ስልቶችን በመጠቀም ነበር፡፡  እነሱም (1) ጠላት ሲበረታ አፈግፍግ፣ (2) ጠላት ሲዳከም አጥቃ፣ እና (3) ጠላት ሲያርፍ አውክ የሚሉት ናቸው፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ለአዲስ ዓመት ቅድመ ዝግጅት- በራሳችን ላይ እንዝመት፣- ይገረም አለሙ

ያርበኝነት ዘመን ፋኖወች ከመደበኛ ውጊያ ወደ ደፈጣ ውጊያ የዞሩት ጣልያን አዲሳባን ከተቆጣጠረ በኋላ ነበር፡፡  ባሁኑ ጊዜ ደግሞ አዲሳባን የተቆጣጠረው አማራን ከምድረግፅ ለማጥፋት ቆርጦ የተነሳው የጭራቅ አሕመድ ኦነግ ነው፡፡  ይህ ፀራማራ አውሬ ካዲሳባ የሚወጣው ደግሞ ከገጠር ወደ አዲሳባ በሚያመራ፣ በደፈጣ ውጊያ ጀምሮ እያደገ ሂዶ ወደ መደበኛ ውጊያ በሚሸጋገር የነጻነት ጦርነት ነው፡፡

 

ሳትና ፋኖ

በደፈጣ ውጊያ ላይ የፋኖ የመጀመርያ ተልዕኮ መሆን ያለበት፣ ገጠሩን ያማራ ክልል መሠርት አድርጎባስፈላጊው መቸት (መቸ እና የት) አስፈላጊውን ጥቃት እያደረሰ፣ ፀራማራው ጥምር ጦር ያለ አጃቢ (ኮንቮይ) እንዳይጓዝ በማስገደድ፣ የሰው ኃይል፣ የስንቅና የትጥቅ አቅርቦቱን በከፍተኛ ደረጃ ማስተጓጎል ነው፡፡  በድንገት እየተወረወረ ባስፈላጊው መቸት አስፈላጊውን ጥቃት የሚፈጽመው የፋኖ ክፍል ደግሞ ሳተና ፋኖ (commando fanno) ሊባል ይችላል፡፡

ሳተና ማለት የሚሳትን፣ ብርቱ፣ ሯጭ፣ ፈጣን፣ ቀልጣፋ ማለት ነው፡፡  በመሆኑም ሳተና ፋኖ (commando fanno) ማለት ተወርዋሪ ፋኖ ወይም ፈጥኖ ደራሽ ፋኖ ማለት ነው፡፡  ሳተና ፋኖ ባውሎ ነፋስ ይመሰላል፡፡  አውሎ ነፋስ ባልታሰበበት ሰዓት ካልታሰበበት አቅጣጫ በድንገት ነፍሶ፣ የሚጠራርገውን ጠራርጎ ወዳልታሰበበት አቅጣጫ  ይነጉዳል፡፡  ሳተና ፋኖም እንደዚሁ፡፡  ሳተና ፋኖ በመብረቅም ሊመሰል ይችላል፡፡  መብረቅ ሲበርቅ እንጅ መቸና በየት በኩል እንደሚበርቅ አይታወቅም፡፡  ከበረቀ በኋላ ደግሞ ዓይን ቢጨፍኑ ዋጋ የለውም፡፡  ሲበርቅ ቢጨፍኑ ከመወጋት አይድኑ፡፡

 

ደመላሽ ፋኖ

የፋኖ ሁለተኛው ተልዕኮ አማራን እያረዱና እያሳረዱ ያሉትን የኦነግ፣ የወያኔና የብአዴን አመራሮች መውጫ መግቢያቸውን አጥንቶ ባስፈላጊው መንገድ ማስወገድ ነው፡፡  በተለይም ደግሞ ከጭራቅ አሕመድ ጋር እጅና ጓነት ሁነው አማራን የሚጨፈጭፉትንና የሚያስጨፍጭፉትን ብአዴኖች ማስወገድ፣ ይዋል ይደር ሊባል አይችልም፡፡  እነዚህ ብአዴናዊ ጉዶች አማራን ደም እያስበሉ በሚከፈላቸው የደም ገንዘብ እነሱ ማኛ እየበሉ ጦቢያ ውስጥ በሰላም መኖር የለባቸውም፡፡  ይህን ተልዕኮ የሚፈጽመው የፋኖ ክፍል ደግሞ የደመላሽ ፋኖ ሊባል ይችላል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  እረ ለመሆኑ ከአንድነት ወዲያ ለኦሮሞ ማን ሊመጣ ነው? 

ደመላሽ ማለት የደም ብደር ከፋይ፣ ተበቃይ፣ ገዳይን ገዳይ ማለት ነው፡፡  ስለዚህም ደመላሽ ፋኖ ማለት ሻቢያ ፈዳይ ይለው የነበረው ዓይነት ነው፡፡  የደመላሽ ፋኖ ሚና የአማራን ደም በደም ማጠብ ነው፣ ደም የሚጠራው በደም ነውና፡፡  ሊገድልህ የመጣን መግደል አልሞት ባይ ተጋዳይነት የሚባል የተፈጥሮ ሕግ ስለሆነ፣ በምድርም አያስወነጅልም፣ በሰማይም አያስኮንንም፡፡

ደመላሽ ፋኖን በተመለከተ ያብራሃም ደቦጭን እና የሞገስ አስገዶምን ገድል በመድገም ዳግማዊ አብርሃም ደቦጭና ዳግማዊ ሞገስ አስገዶም መሆን ያስፈልጋል፡፡  አብራሃም ደቦጭ እና ሞገስ አስገዶም ማለት የሞሶሎኒ አገረ ገዥ የነበረውን ግራዚያኒን ቦንብ ጥለው ለመግደል የሞከሩ፣ በዚህ ሙከራቸው የሞሶሎኒን ቅኝ አገዛዝ መሠረቱን በማናጋት ባጭር ጊዜ ውስጥ እንዲፈራርስ ወሳኝ ሚና የተጫወቱ፣ በሚሞት ሥጋቸው የማይሞት ስማቸውን ተክለው ለዘላለም ሲታወሱ የሚኖሩ ወጣት ጀግኖች ናቸው፡፡

ጭራቅ አሕመድ ያማራን ወጣቶች እያረደ መግደል ስላላረካው፣ በዲንጋ እየፈጠፈጠ መግደል ጀምሯል፡፡  ስለዚህም፣ ጦቢያ ውስጥ ያላችሁ ያማራ ወጣቶችአንዳችሁም ሳትቀሩ ሁላችሁም ወደዳችሁም ጠላችሁም ያላችሁ ምርጫ ሁለትና ሁለት ብቻ ነው፡፡  ወይ ጭራቅ አሕመድን በማስወገድ፣ የጀግና ሞት ሙታችሁ የቀረውን ወገናችሁን ከጭራቁ በመታደግ፣ በሚሞት ሥጋቸሁ የማይሞት ስማችሁን ተክላቸሁ፣ ባማራ ሕዝብ ዝንታለም እየተዘከራችሁ መኖር፡፡  አለያ ደግሞ ወርተራችሁ ሲደርስ በጭራቅ አሕመድ ዲንጋ እየተፈጠፈጣችሁ የውሻ ሞት መሞት፡፡

 

ደጀን ፋኖ

ሦስተኛው የፋኖ ትልዕኮ ነጻ በወጡ ቀጥናወች ላይ ተሰማርቶ የቀጠናወቹን ሰላምና መረጋጋት ማስከበር ነው፡፡  ይህን ተልዕኮ የሚፍጽመው ፋኖ ደግሞ ደጀን ፋኖ ሊባል ይቸላል፡፡  ደጀን ማለት በስተኋላ ሁኖ የሚጠብቅ፣ የኋላ ዘበኛ፣ ረዳት ሠራዊት ማለት ነው፡፡  ስለዚህም የደጀን ፋኖ ተጨማሪ ሚና ለተወርዋሪ ፋኖ እና ደመላሸ ፋኖ የሠራዊት ምንጭ መሆን ነው፡፡

 

ዳያስፖራ ፋኖ

ከሳትና ፋኖ፣ ደመላሽ ፋኖ እና ደጀን ፋኖ በተጨማሪ በውጭ አገር የሚኖር ላማራነቱ የቆመ ያማራ ተውላጅ በሙሉ የዳያስፖራ ፋኖ አባል መሆን አለበት፡፡  የዳያስፖራ ፋኖ ሚና አቅም ግንባታን፣ ዲፕሎማሲን፣ ፕሮፓጋንዳንና የመሳሰሉትን ያጠቃልላል፡፡

ከዳያስፖራ ፋኖ ሚናወች ውስጥ አንዱ ደመቀ መኮንንና መሰሎቹ አማራን አስጨፍጭፈን በምናገኘው ሐብት፣ ጦቢያ ውስጥ መኖር ባንችል ከቤተሰባችን ጋር ውጭ አገር ሂደን፣ የሰላም አየር እየተነፈስን ተሞላቀን፣ ተንደላቀን እንኖራለን ብለው ማለም ቀርቶ እንዳያስቡት ማድረግ ነው፡፡  ሊዝናኑም ሆነ ሊታከሙ በመጡ ቁጥር እግር በእግር እየተከታተሉ ማሽማቅቅ ነው፡፡  ውጭ አገር ቤት ገዝተው ከሆነ ደግሞ ማነነታቸውን የሚያጋለጡ ጽሑፎችን በመያዝ በቤታቸው አቅራቢያ በየዕለቱ በመሰለፍ መቆሚያ መቀመጫ ማሳጣት ነው፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  የኢህአዴግ ቀጣይ የፖለቲካ ሴራዎች - (ተመስገ ደሳለኝ)

የዲያስፖራ ፋኖ ሚና፣ በተለይም ደግሞ የፕሮፓጋንዳው ዘርፍ ሚና እንደ ሌሎቹ ፋኖወች ሚና የሂወት መስዋእትነት ባይጠይቅም፣ ወሳኝነቱ ግን ከሌሎች ፋኖወች ሚና ቢበልጥ እንጅ አያንስም፣ ጦር ከፈታው ወሬ የፈታው ነውና፡፡  ሸማ በየፈርጁ፣ ትግል በየደጁ ነው፡፡  ድል ደግሞ የትግሎች ሁሉ ድምር ውጤት ነው፡፡

 

ያማራ ድል አይቀሬነት

ጭራቅ አሕመድ የራሱን ሽንፈት ራሱ ማሕፀን ውስጥ ፀንሷል፡፡  ይህን ያደረገው ደግሞ በሁለት ሁኔታወች ነው፡፡

የመጀመርያው ሁኔታ የጭራቅ አሕመድ ጦር አስኳል የኦነግ ሠራዊት መሆኑ ነው፡፡  የኦነግ ሠራዊት ግን ዕድሜው ከግማሽ ምዕተ ዓመት ያለፈ አዛውንት ሠራዊት ቢሆንም፣ በዚህ ረዥም እድሜው ግን መሳረያ ከታጠቀ ባላጋራ ጋር እንድም ቀን ተዋግቶም ሆን አሽንፎ አያውቅም፡፡  ኦነግ የሚያወቀውና የሚታወቀበት ጨለማን ተገን አድርጎ ተከላካይ አልባ ሕፃናትንና አረጋውያንን በሜንጫ በማረድና በገደል በማንኮታኮት ብቻና ብቻ ነው፡፡  ወያኔው ሰየ አብርሃ ኦነግን ከሳንቲም አንቆጥረውም በማለቱ ምንም አልተሳሳተም፡፡  ጭራቅ አሕመድ የሸኔ ሠራዊቱን እንደ ተምች አብዝቶ አስካፍንጫው ቢያስታጥቀውም፣ የሺዋ ፋኖ ብቻ የዶግ ዐመድ እንደሚያደርገው ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡

ሁለተኛው ሁኔታ ደግሞ ጭራቅ አሕመድ አማራን እጎዳልሁ ብሎ ዘመናዊ ጦሩን ሽሽት ማስተማሩ ነው፡፡  የጦር አዛዦቹን ደግሞ ታንኩን ባንኩን ጣጥለው የሚሸሹ ቱሪናፋወች በመሆናቸው ብቻ እስከ ፊልድ ማርሻልነት አድርሷቸዋል፡፡  አንዴ የሸሸ ሠራዊት ደግሞ መቸም ቢሆን ቁሞ አይዋጋም፡፡

ስለዚህም ፋኖ ጊዜና ቦታ ጠብቆ የጭራቅ አሕመድን ጦር መኻሉ ላይ ደህና አርጎ ከቦቀሰው፣ እንደ እንቧይ ካብ ይፈራርሳል፣ ከፈራርሰበት የፈርጠጠ አዲሳባ ይደርሳል፣ አዲሳባ እንደደርሰ እጁን ያነሳል፣ መሣርያውን ይመልሳል፣ እንደ ወንጀሉ የጁን ይቀምሳል፡፡

ያርበኝነት ዘመን አያቶቻችን አዲሳባን ነጻ ለማውጣት አመስት ዓመት ፍጅቶባቸዋል፡፡  ፋኖ ራሱን ከፀራማሮች አጽድቶ፣ ነጻነቴ ወይም ሞቴ ብሎ ተግዝቶ፣ በተገቢው መንገድ የሞት ሽረት ትግል ካደርገ ግን ያጼ ዳዊትን ከተማ መልሶ ለመቆጣጠር ካመት በላይ አይፍጅበትም፡፡

 

መስፍን አረጋ

mesfin.arega@gmail.com

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share