በሰሜን አሜሪካ ለምትኖሩ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን (በሰሜን አሜሪካ የፍኖተ ነጻነት አስተባባሪ ኮሚቴ)

ቀደም ሲል በአገር ቤት የምትታመውንና በአሁኑ ጊዜ በገዥው ስርአት በነጻ ፕሬስ ላይ በሚደረገው ዘመቻ የመጨረሻው ሰለባ በመሆን ላይ ያለችውን  ፍኖተ ነጻነት ጋዜጣን ህይወት ለመስጠት እንቅስቃሴ መጀመሩ ይታወሳል።

ከእንቅስቃሴው አንዱ መገለጫ የህትመት መሳሪያ ግዥ ፕሮጀክት ሲሆን ለዚህ ፕሮጀክት መሳካት በሀገርም ሆነ በውጭ በርካታ ወገኖቻችን ለጥሪው ምላሽ በመስጠት ላይ መሆናቸው እጅግ አበረታቶናል ።በተለይ በውጭ የሚገኙ ወገኖቻችን ምላሽ ለዚህ ፕሮጄክት መሳካት ቀዳሚውን ስፍራ ይዞ ይገኛል ብለን እናምናለን።

ይህንኑ ጥረት ለማሳካትና እንዲሁም አገራችን የምትገኝበትን ወቅታዊ ሁኔታ ከኢትዮጵያውያን ወገኖቻቸው ጋር ለመወያየት አቶ ግርማ ሰይፉ የአንድነት ፓርቲ ም/ሊቀ መንበርና በፓርላማ ብቸኛው ተቃዋሚ  በሰሜን አሜሪካ አንዳንድ ከተሞች ከወገኖቻቸው ጋር ውይይት የሚያደርጉ ሲሆን ለመጀመሪያ ጊዜ በሚደረገው በዚህ ዙር የተካተቱት በሚከተሉት ከተሞችና ቀናት ይሆናል።

April 7/2013      Huston

April 10/2013      Lasvegas

April 10, 2013 —-  Las Vegas

April 14/2013      Washington DC

April 20/2013     Los Angeles Via Skype

April 21/2013      Atlanta

April 27/2013      Minesota

April 28/2013      Boston

በመሆኑ በነዚህ ከተሞች የምትገኙ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን በአስተባባሪዎች በሚዘጋጁ መድረኮች ተገኝታችሁ በሃገር ቤት ውስጥ ስለሚደረገው ትግል ውይይት እንድናደርግና በዚሁ አጋጣሚም  ፍኖተ ነጻነት ተመልሳ ህያው መሆን አጋርነታችሁን እንድታረጋግጡልን በታላቅ ትህትና እንጠይቃለን።

በዚህ ዙር በተዘጋጀ መድረክ ውይይት በማይካሄድባቸው ከተሞች ያላችሁ ወገኖቻችንም ያለንን የአቅም ውሱንነት ተገንዝባችሁ ቀደም ሲል በጀመራችሁት መሰረት በፍኖተ ነጻነት አካውንት  በፔይፓል፤  በቼክ ፤ ወይም ቀጥታ በባንክ ሂሳብ ድጋፋችሁን እንድትቀጥሉ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

በተባበረ ክንድ የጀመርነውን ጥረት እናሳካለን

ተጨማሪ ያንብቡ:  የኢትዮጵያ ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ክለቦች ተቀጡ

በሰሜን አሜሪካ የፍኖተ ነጻነት አስተባባሪ ኮሚቴ

Share