March 6, 2023
3 mins read

ኮሚዩኒኬሽን ወይስ ፎልሲፊኬሽን? – ከመርሐጽድቅ መኮንን አባይነህ

እንደሀገራችን የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስቴር ሰሞነኛ መግለጫ ከሆነ 127ኛው የአድዋ ድል በአል ባለፈው የካቲት 23 ቀን 2015 ዓ.ም አዲስ አበባ ውስጥ በወጉ ተከብሮ በሠላም ተጠናቋል፡፡

ይህ የሚኒስቴር መስሪያ ቤት በጊዜው አይኑን በጨው አጥቦ ለህዝብ በለቀቀው መግለጫ መሰረት አዲስ አበባ ውስጥ ዳግማዊ አጼ ምኒልክ አደባባይ አካባቢ የዚህኑ በአል አከባበር ሆነ ብለው ለማወክ የተነሳሱ አንዳንድ ጸረ-ሠላም ወገኖች በአቅራቢያው ወደሚገኘውና ሀይማኖታዊ የአምልኮና የምስጋና ስነ-ስርአት ወደሚፈጸምበት የገነተ-ጽጌ አራዳ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ-ክርስትያን ቅጥር ግቢ ዘልቀውና ከምእመናን ጋር ተቀላቅለው ወደውስጥ በመግባት የፈጠሩትን አመጽና ግርግር ለመቆጣጠር የጸጥታ ሀይሎች በወሰዱት ሕግ የማስከበር እርምጃ ጥቂት ምእመናን ከመጎዳታቸው በስተቀር ያጋጠመ ችግር አልነበረም፣ የለምም፡፡፡

እውነቱ ግን እርሱ አልነበረም፡፡ በዘመናዊው አለም በአደባባይ ይቅርና በህቡእ ተፈጽሞ ሊደበቅ የሚችል አንዳች ነገር ሊኖር ከቶ አይችልም፡፡

ተፈጠረ በተባለው በዚያ ሁከት በስፍራው የደረሱ የጸጥታ አስከባሪዎች ተመጣጣኝ ያልሆነ ሀይል ሲጠቀሙ ታይተዋል፡፡ በፈረስ ጀርባ ላይ የተቀመጠን የበአሉ ታዳሚ ጭካኔ በተመላበት የአፈሙዝ ምት ደብድበው በሚዘገንን ሁኔታ መሬት ላይ ሲጥሉና ሲያንፈራፍሩት ተስተውለዋል፡፡ በዚህ ሳይወሰኑ የቤተ-ክርስትያኗን ልእልና ያለአግባብ በመዳፈርና ቅጥር ግቢዋን ጥሰው በመግባት መንፈሳዊ አገልግሎት ይሰጡ በነበሩ ካህናትና አምልኮ ይፈጽሙ በነበሩ ምእመናን ላይ አስለቃሽ የጭስ ቦንብ ተኩሰው የንጹሃንን ህይወት ከመቅጠፍና በብዙኃኑ ላይ አካላዊና ስነ-ልቡናዊ ጉዳት ከማድረሳቸውም በላይ ይካሄድ የነበረው አገልግሎት እንዲቋረጥ አድርገዋል፡፡፡

በርግጥ የቅጥፈት ፖለቲካ እንደብልጠት በሚቆጠርባት አለማችን አያሌ መንግሥታት ዜጎቻቸውን በአደባባይ መዋሸታቸው ያን ያህል እንግዳ ነገር አይደለም፡፡ ያም ሆኖ ግን ውሸትን በዚህ ደረጃ ይፋዊና ተቋማዊ ማድረግ የጤና ሊሆን ከቶ አይችልም፡፡

አንድዬ በቸርነቱ ይቅር ይበለን ከማለት በስተቀር ሌላ ምን ሊባል እንደሚችል እኔ በበኩሌ ግራ መጋባትን እንደፈጠረብኝ ለመደበቅ አልፈልግም፡፡

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

Go toTop