እባቡ እየተቃረበ መጣ – ዶ /ር ምህረት ደበበ

አንድ ቀን ነው፤ ዶሮ፣ ፍየል፣ በሬና ሰው በአንድ ቤት ውስጥ አብረው ነበሩ። ከዛ እባብ ቀስ እያለ ወደ ቤቱ ሲገባ መጀመርያ ዶሮዋ ነበር ያየችው “እኔ ምን አገባኝ ጣራ ላይ ስለወጣሁ አይደርሰኝም” በማለት እባብ እየመጣ እንደሆነ ሳትነግራቸው ዝም አለች። እባቡ እየተቃረበ መጣ።

በመቀጠል ፍየሏ ነበር ያየችው ። “መቼም ቤትን የምያኽል ትልቅ በሬ እያለ እኔን ይበላኛል ብሎ ማሰብ ሞኝነት ነው ። ስለዚህ ምን አገባኝ መምጣቱን ይሁን መግባቱን የሚያስጨንቀኝ” ብላ ዝምታን መረጠች ።

አሁንም እባቡ እየቀረበ መጣ መጨረሻ ላይ ትልቁ በሬ እባቡን መግባቱ ተመለከተ ። እሱም እባብ ቤቱን እንደገባ ከማሳወቅ ይልቅ በጉልበቱ የሚተማመን ስለነበረ “ቢገባስ ምን አገባኝ ፤ እኔን ምን እንዳይጎድለኝ ፤ ቢነድፍ ሰውዬው እንጂ እኔን ዞር ብሎ አያየኝም ትልቅ መሆኔ እያየ አይደፍረኝም” ብሎ እንደሌሎቹ ሳያሳውቃቸው ቀረ ።

በሚያሳዝን ሁኔታ ግን እባቡ ያሁሉ ክፍተት ስላገኘ ተኝቶ ዓለሙን በእንቅልፍ ልቡ ሲዋኛት ለነበረ ሰውዬው እግሩን ነደፈው ።

በሁኔታው በጣም የተደናገጠ፤ሰውየው ከእንቅልፉ በሰከንዶች ተነስቶ”ኡ ኡ ኡ…” በማለት ጩኸት ማሰማት ጀመረ ። እንዳለ ጎረቤቶቹ ምን አገኘው በማለት ግልብጥ ብለው መጡ ። ታላቆች ተጠርተው እባብ እንደነደፈው ሲነግራቸው ፤ ሰውዬው እንዴት መፈወስ እንዳለባቸው መመካከር ጀመሩ ።

ከዛ አንድ ታላቅ አባት ተነስተው ዶሮዋ በተነደፈው እግሩ እንዲያስቀምጧትና መርዙን በአፏ ስባ እንድታወጣው መከሩ። ትልቁ አባት ያሉትን ሰምተው ነገሩን ሞኮሩት፤ ሰውዬው ግን ተጨማሪ መድኃኒት ሳያስፈልገው አልቀረም ጨርሶ አልዳነም። ዶሮዋም መርዙን ስለሳበችው ሞተች እንጂ “ምን አገባኝ” ማለቱ አልጠቀማትም።

ተጨማሪ ያንብቡ:  " በቢላዋ ቀልድ የለም ፡፡ " መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ

ቀጥሎውም የፍየል መረቅ እባብን የተነደፈ ሰው ከጠጣው ፍቱን መድኃኒት መሆኑ ከመኸል በመነሳት አንድ አባት ተናገሩ ። ድጋሜም እንሞክረው በማለት ፍየሏ ታረደችና በመረቅ መልኩ ለታመመ ሰውዬ አቀረቡለት ። ፍየሏም “ምን አገባኝ” ማለቱ ለራሷ ጥሩ አልገጠማትም።

ታማሚው ባሉት መሠረት መረቁ አንድ ሳያስቀር ጠጣው

“ማን አባቱ ቀና ብሎ ያየኛል”እያለ ሲፎክር የነበረ ታላቁ በሬም ከሞት ልያመልጥ አልቻለም ። ቀኑ መሮጡን አላቆመምና ሟቹ 80(ሰማንያ) ቀኑ ደረሰ። ለተዝካሩ ይሆን ዘንድ እንደባህላችን መሠረት እህልና ውኋ ማጥፋት የግድ ነበረና በሬ መታረድ ስለነበረበት ታላቁ በሬ “ምን አገባኝ ማለት”ቄራ ሳያገባው አልቀረምና ነው።

ለማለት የፈለግሁት ሁላችን ኢትዮጵያውያን እርስ በርሳችን ተግባብተን “አንዱ ሲጎዳ ስናይ” ጉዳቱ የሁላችን መሆኑ እናስብ። ዛሬ አንዱን ሲጨንቀው ሲቸገር አይተን እንዳላየን ሰምተን እንዳልሰማን ችላ ብለን ካለፍነው ፤ ጊዜው ጠብቆ ችግሩ ወደ’ኛም እንደሚመጣ አንዳንረሳ። እንተጋገዝ እንተዛዘን እንተባበር እንመካከር ልዪነታችን ውበታችን ነው።

3 Comments

  1. የእብድ ፓለቲካ የዛሬን እንጂ የነገን አያይም። ዛሬ በሃበሻዋ ምድር ያለቅጥ የጦዘው የዘርና የክልል ፓለቲካ ሰውን ከሰውነት ወደ አውሬነት አሸጋግሮታል። ያለምንም ርህራሄ ሰውን የሚረሽኑ፤ አንገት የሚቆርጡ፤ ሃብትና ንብረት የሚያወድሙና የሚዘርፉ ስመ የነጻነት ታጋዪች ተራ ወንበዴዎች እንደሆኑ ተግባራቸው በግልጽ ያስረዳል። ሰውም እንደ ቄራ ከብት እየተነዳ ከማለቅ ራሱን አደራጅቶ መፋለም እንዳለበት ያኔም ዛሬም ብለናል። ከብሄር ታጣቂዎች ምንም ዓይነት ርህራሄ ይኖራል ብሎ ማሰብ የእነርሱን ስነልቦና በደንብ አለመረዳት ነው። ኢትዮጵያን ለመናድ ያልተፈነቀል ደንጋይ፤ ያልተቀጣጠለ እሳት የለም። በዘርና በክልል ፓለቲካም ቢሆን ተሸንሽና እንሆ አሁንም በመንገዳገድ ላይ አለች። የብሄር ፓለቲካ አራማጆች አሁን የኢትዮጵያ ተዋህዶ ቤ/ክ ለመናድ የሚያደርጉት ተግባር ሆን ብሎ በተሰላ ሂሳብ የሚደረግ እንጂ አሁን የተገለጠላቸው ተንኮል አይደለም። በውጭ ሃገር በተለይም በጀርመን፤በአሜሪካ፤ በለንዶንና በሌሎች ስፍራዎች የኦሮሞ ጠባብ ብሄርተኞች ተሰብስበው ይናገሩ የነበሩትና አሁን ላይ የሚደረገውን ዲስኩርና ሃተፍተፍ ባይነት ከየድህረ ገጽ ለቅሞ ለተገነዘብ ሴራው የይፋ እንጂ የሰውር አይደለም። ኦሮሚያ የምትባልን ሃገር መመስረት ይፈልጋሉ። የበቀለ ገርባን፤ የጫቱ ፕሮፌሰርንና የሌሎችንም ስመ ምሁራን ንግግርና ጽሁፍ ላጤነ ውጊያው የደፈጣ ሳይሆን የፊት ለፊት ነው። በዚህ ላይ የጠ/ሚሩ ውሻላዊ እይታና አፍቃሪ የኦሮሞ ብሄርተኛ መሆኑ ነገሩን የበለጠ አበላሽቶታል። የሚናገራቸው ቃላቶች ከፋፋይና ስልታዊ ሰይፍ በመሆናቸው ከዲስኩሩ ብዛት ሰው ለመታዘብ ይከብደው ይሆናል። ረጋ ብሎ በየጊዜው የሚናገራቸውን ላዳመጠ ግን ሰውዬው እሳት እያነደደ ለመሆኑ ሙሉ መረጃ ያገኛል። ችግሩ ኢትዮጵያ አትፈርስም፤ ኢትዮጵያ ሱሴ ናት የሚሉን ሰዎች ናቸው ሃገሪቱን የሚያሸብሯት።
    ትላንት በወያኔ እልፍ መከራ ያለፈችው ይህቺ ሃገር አሁን ደግሞ ይሻልን ትቼ ትብስን የሚባልበት ጊዜ ላይ ደርሰናል። በሰላሙ ጥሪ ከየስፍራው ተጠራርተው የገቡት የኦሮሞ የቅርብና የሩቅ ታጣቂዎች አሁን በሰው ላይ የሚፈጽሙት በደል ትውልድ አይረሳውም። ጊዜ ሁሉን ይፈታዋል። የጠ/ሚሩ የአመራር መወላገድም ራሱን ጨምሮ ዋጋ ያስከፍለዋል። መሪ የጠራ አቋም ሊኖረው ሲገባ እንዲህ በየጊዜው መልክን እየለወጡ በጣፈጠ ቃል ሰውን የሾኬ ጠለፋ መጣል ለራስም ሆነ ለሃገር ደህንነት መልካም አይደለም። ባጭሩ በመለማመጥ፤ በእርቅ የሚበርድ እሳት አይደለም። ጉዳዪ በአለም ላይ ከሚታየው የፓለቲካ አሻጥርና የእኔን እከክ እኔ ያንተን አይነት የፓለቲካ ስርግብ ጋርም የቀጥታና የተዘዋዋሪ ግንኙነት አለው። ስለሆነም የአጥፊ ሃሎችን ስብስብና እይታ ፊት ለፊት ዘርና ቋንቋን፤ ክልልና ሃይማኖትን ተገን ሳያደርጉ መፋለም ወደፊት የባሰ መከራ በህዝባችን ላይ እንዳይመጣ አንድ የመመከቻ መንገድ ነው። ከሥር ባለው ግጥም ለዛሬው ነገሬን ልዝጋ።
    ይህን ሁሉ ጩኽት ሰብስቦ አስተባብሮ
    አስለቃሽ ፈልጎ መሃል ላይ አቁሞ
    ግጥም እየሰጡ ሰውን አስለቅሶ ድረት እየመቱ
    በህብረት ዋይታ ለሞተ ለቆመው ምሾ እያወረዱ
    ማዘኑ ይሻላል ለሃገር ፓለቲካ
    አየነው ሌላውን አፍራሹን በአፍራሽ ተክቶ እየመጣ
    በቁማችን ጋጠን ለውጥ ሳያመጣ።

  2. ሁሉም እንተባባር ነው እንጅ ንባቡ የኦሮሞን ጥላቻ ማንሳት ምንም አይፋይድም ነው:: እንደ እናንቴ አይናት ነው በጥባጭ:: ለኦሮሞ ፖሎትሽያን ኣያስፈልግም እንዳምትል እናቃሌን አቶ ተስፋ

  3. በነገራችን ላይ የእርሰዎ ፅሑፍና አነቃቂ ንግግሮች አደንቃለው አዳምጣለው በአሁኑ ሰዓት እዬሆነ ያለው ይኸ ነው አማራ ሲታረድ አማራ ሲበላ በተጠናና በተናበበ መልኩ መከረውን ሲያይ በተለይ ወለጋ ከገደሉ በኋላ ሰወ አይደለም የሞተው ነፍጠኛ ነው ይላሉ እርሰዎ እንዳሉት ነገ ለሡማሌው፣ ለጋምቤለው፣ ለጉዙም ይደርሰዋል ይህ ትርክትና ከእኔ አይደርስም ነገ የሁሉም በር ይንኳኳል ኦርቶዶክስም አማራም እራሱን መቋቋም አያቅተውም ጊዜወ አልፎ ተኝነት አልፎ ማዬት መልካም ነው ምድር ላይ ሽመልስ አብዴሳ አማራ በአንድ ቀን ቢያልቅለት ኦርቶ ዶክስ ቢጠፋ የመጨረሻው እርካታው ነው የሚጋሩት የሡን ሀሣብ አዳነች አቤቤ አብይ አህመድ ደመቀ እስከ ጀሌዎቹ ነው

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share