February 7, 2023
4 mins read

እባቡ እየተቃረበ መጣ – ዶ /ር ምህረት ደበበ

326522618 2100965490100235 4031676535958476022 n 1

አንድ ቀን ነው፤ ዶሮ፣ ፍየል፣ በሬና ሰው በአንድ ቤት ውስጥ አብረው ነበሩ። ከዛ እባብ ቀስ እያለ ወደ ቤቱ ሲገባ መጀመርያ ዶሮዋ ነበር ያየችው “እኔ ምን አገባኝ ጣራ ላይ ስለወጣሁ አይደርሰኝም” በማለት እባብ እየመጣ እንደሆነ ሳትነግራቸው ዝም አለች። እባቡ እየተቃረበ መጣ።

በመቀጠል ፍየሏ ነበር ያየችው ። “መቼም ቤትን የምያኽል ትልቅ በሬ እያለ እኔን ይበላኛል ብሎ ማሰብ ሞኝነት ነው ። ስለዚህ ምን አገባኝ መምጣቱን ይሁን መግባቱን የሚያስጨንቀኝ” ብላ ዝምታን መረጠች ።

አሁንም እባቡ እየቀረበ መጣ መጨረሻ ላይ ትልቁ በሬ እባቡን መግባቱ ተመለከተ ። እሱም እባብ ቤቱን እንደገባ ከማሳወቅ ይልቅ በጉልበቱ የሚተማመን ስለነበረ “ቢገባስ ምን አገባኝ ፤ እኔን ምን እንዳይጎድለኝ ፤ ቢነድፍ ሰውዬው እንጂ እኔን ዞር ብሎ አያየኝም ትልቅ መሆኔ እያየ አይደፍረኝም” ብሎ እንደሌሎቹ ሳያሳውቃቸው ቀረ ።

በሚያሳዝን ሁኔታ ግን እባቡ ያሁሉ ክፍተት ስላገኘ ተኝቶ ዓለሙን በእንቅልፍ ልቡ ሲዋኛት ለነበረ ሰውዬው እግሩን ነደፈው ።

በሁኔታው በጣም የተደናገጠ፤ሰውየው ከእንቅልፉ በሰከንዶች ተነስቶ”ኡ ኡ ኡ…” በማለት ጩኸት ማሰማት ጀመረ ። እንዳለ ጎረቤቶቹ ምን አገኘው በማለት ግልብጥ ብለው መጡ ። ታላቆች ተጠርተው እባብ እንደነደፈው ሲነግራቸው ፤ ሰውዬው እንዴት መፈወስ እንዳለባቸው መመካከር ጀመሩ ።

ከዛ አንድ ታላቅ አባት ተነስተው ዶሮዋ በተነደፈው እግሩ እንዲያስቀምጧትና መርዙን በአፏ ስባ እንድታወጣው መከሩ። ትልቁ አባት ያሉትን ሰምተው ነገሩን ሞኮሩት፤ ሰውዬው ግን ተጨማሪ መድኃኒት ሳያስፈልገው አልቀረም ጨርሶ አልዳነም። ዶሮዋም መርዙን ስለሳበችው ሞተች እንጂ “ምን አገባኝ” ማለቱ አልጠቀማትም።

ቀጥሎውም የፍየል መረቅ እባብን የተነደፈ ሰው ከጠጣው ፍቱን መድኃኒት መሆኑ ከመኸል በመነሳት አንድ አባት ተናገሩ ። ድጋሜም እንሞክረው በማለት ፍየሏ ታረደችና በመረቅ መልኩ ለታመመ ሰውዬ አቀረቡለት ። ፍየሏም “ምን አገባኝ” ማለቱ ለራሷ ጥሩ አልገጠማትም።

ታማሚው ባሉት መሠረት መረቁ አንድ ሳያስቀር ጠጣው

“ማን አባቱ ቀና ብሎ ያየኛል”እያለ ሲፎክር የነበረ ታላቁ በሬም ከሞት ልያመልጥ አልቻለም ። ቀኑ መሮጡን አላቆመምና ሟቹ 80(ሰማንያ) ቀኑ ደረሰ። ለተዝካሩ ይሆን ዘንድ እንደባህላችን መሠረት እህልና ውኋ ማጥፋት የግድ ነበረና በሬ መታረድ ስለነበረበት ታላቁ በሬ “ምን አገባኝ ማለት”ቄራ ሳያገባው አልቀረምና ነው።

ለማለት የፈለግሁት ሁላችን ኢትዮጵያውያን እርስ በርሳችን ተግባብተን “አንዱ ሲጎዳ ስናይ” ጉዳቱ የሁላችን መሆኑ እናስብ። ዛሬ አንዱን ሲጨንቀው ሲቸገር አይተን እንዳላየን ሰምተን እንዳልሰማን ችላ ብለን ካለፍነው ፤ ጊዜው ጠብቆ ችግሩ ወደ’ኛም እንደሚመጣ አንዳንረሳ። እንተጋገዝ እንተዛዘን እንተባበር እንመካከር ልዪነታችን ውበታችን ነው።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

Go toTop