September 28, 2022
16 mins read

በሬ ካራጁ …እንዳይሆን መጠንቀቅ ደግ ነው – ሲና ዘ ሙሴ

abiy

abiyየጠላቶቻችንን ሤራ ለማክሸፍ ነገሮችን በጥልቀት ፈትሾ መረዳት እጅግ አሥፈላጊ  የሆነበት ጋዜ ላይ ደርሰናል ።

“ ኢትዮጵያ በጦርነት ድል አትደረግም ። በሹመት ፣ በጥቅምና በመሣሠሉት እንጂ !  እናም ፣ ከፍተኛ   የመንግሥቷን ባለሥልጣናት በመደለል ፤ ግሪን ካርድ በመሥጠት ፤ ምሥጢራዊ አካውንት በአውሮፕና በአሜሪካ እንዲከፍቱ በማገዝ ፣ አገራቸውን እንዲሸጡ ልታደርጓቸው ካልቻላችሁ የኢትዮጵያን ህዝብ ተዋግታችሁ ማሸነፍ ከቶም አትችሉም    ።  ” በማለት  የኢጣሊያ የፋሺስቱ  ሞሶሎኒ ደቀመዝሙሮች ከአድዋ ሽፈንታቸው በኋላ ለመላው አውሮፖ ምክረ መለገሳቸውን ዞር ብለን ማሥታወሥ ይገባናል  ። አንዳንድ የዘመኑ ቅኝ ገዢ አገራት ምሁራንም ፣  የአድዋን ድል ተከትሎ በመጣው የኢትዮጵያውያኑ የልብ ኩራት የተነሣ ተበሣጭተው በየአጋጣሚው ይኽንኑ ሃሳብ በወቅቱ ለነበሩት ቅኝ ገዢዎች ማቅረባቸውንም አነሰዘንጋ  ። የእንግሊዝ ፣ የጀርመን ፣ የፈረንሣይ፣ የአሜሪካ ቅኝ ገዢ የልጅ ፣ልጆችም ዛሬም ይኽንን  መሠሪ ሃሳብ ወደ ተግባር ለመቀየር ፤ኢትዮጵያን ከዓለም ካርታ ላይ ለማጥፋት  በህቡ እና በይፋ  በብርቱ እየሰሩ ነው ። የላታን  ፊደልም አንዱ መሣሪያቸው ሆኖ እያገለገላቸው ነው ። በጀርመን ቅኝ ገዢዎች የተቀነባበረ የሤራ የላቲን ፊደል ፖለቲካ እጅግ አደገኛ እንደነበር ከ27 ዓመት የተገነዘቡት ጥቂት ጋዜጠኞችና በሣል ምሁራን ነበሩ  ። በበኩሌ በግእዙ ፊደል ወይም በራሳችን አማርኛ ፊደል መጠቀም ችግር አልነበረውም ። የቋንቋ ምሁራኑ ሃሳብም  አገረሰኛውን ንቆ በቀኝ ገዢው ፊደል መጠቀም የኋላ ኋላ የበሬ ካራጁ ይውላልን መሠሪ ገቢር ይከሥታል ደ በማለት አሣሥበዋል  ።

በመሠረቱ ፣ ቋንቋ ከመግባብያነት  ውጪ ፋይዳ የለውም ።ይኽ እየታወቀ ግን ከጀርመን ላቲንን  በመዋስ የኢትዮጵያን ቀለም ማጥፋት ተገቢ አይደለም ። ይኽ የላቲን ፊደል ፖለቲካ ፣  ፖለቲካውን ከሰው ፖለቲካ ተራ ከማውጣቱ በሻገር ዜጋውን በአገሩ ላይ እምነት እንዲያጣ በማድረግ በገመድ ጉተታ የፖለቲካ ትግል ውሥጥ ዘፍቆታል ። ተማሪዎች  ላይ ያሥከተለው ጦስ ና ጥንቡሣሥም ቀላል እና እንደዋዛ የሚታለፍ  አይደለም ። ደሞም የላቲን ፊደል አንዱ የከፋፍለህ ግዛ መንገድ መሆኑ በብዙ የቆንቋ እና የፖለቲካ ምሁራን በማሥረጃ እና በመረጃ የተረጋገጠ  እንደሆነ ልብ ማለት በዕወቅት ላይ ለተመሠረተ ክርክር ይጠቅማል  ።

ወደ ነገሬ ልመለሥ  ።ይህ ህቡ ሆኖ በአውሮፖና በአሜሪካ ቱጃሮች የሚሾር  ፣የከፋፍለህ ግዛ   እኩይ አሳብ ከቀዳማዊ ኃይለሥላሤ የንጉሠ ነገሥት መንግሥት አንስቶ እሥከዛሬ በረቀቀ ዘዴ  እየተተገበረ ያለ “ ኢያጓዊ መንገድ ነው ።” ይኽ መንገድ በሐሰተኛ ትርክትና ወሬ ህዝብ ማደናገር ፣ ማጣለት ፣ ቂምና ቁርሾ ማሥያዝ ላይ የተመሠረተ እርስ በእርስ የማጠፋፍያ መንገድ ነው ። ይኽን  መንገድ እሥከዛሬ በአራት ኪሎ ቤተመንግሥት የአገዛዝ  አልጋ ላይ  የተፈራረቁት  ባለሥልጣናት  ቀለምና መልክ ፍንትው አድርጎ ያሣየናል   ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሞትን በሕይወት፣ ጥላቻን በፍቅር የረታ ‹‹ይቅርታ!››

እንደሚታወቀው ከንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለሥላሤ   ውድቀት በኋላ ፤ የተከሰቱት ወታደር መር አገዛዞች  ናቸው ።ሁለቱም  ልምጭ ተኮር አመራሮች ነበሩ ።ይሁን እንጂ  ወታደራዊው ደርግ እጅግ የደመቀ የአርበኝነት መንፈሥ ነበረው ።በተግባር አገር ወደዳ  ነበር ። የወደቀውም በዓለም ላይ ከነበሩት ሁለት የፖለቲካ ጎራዎች አንዱ ሥለተንኮታኮተ ነው ።   በወቅቱ የነበረው  የሶሻሊስቱ ጎራ   ፣ በሩሲያዊው መሪ ጉርቫቾቭ  አማካኝነት  በአሜሪካ መንግሥት ተከታታይነት ባለው ሴራ ፣ በሩሲያ ምድር   ሲቀብሩት ፣ በቀላሉ   ዘረኛው ኃይል  ኢህአዴግ ብሎ ራሱን በመጥራት   ደርግን ከሥልጣኑ ገፍትሮ  ፤ ኢርትራ በቀላሉ ከእናት አገሯ ከኢትዮጵያ እንድትገነጠል በመተባበር ፤ የአራት ኪለውን አልጋ በቀላሉ ተረከበ  ።

የዘረኛው ወያኔ ኢህአዴግ መንግሥት በተራው ፣ በሥልጣን እሥከ ጥግ ባለገ ። በብልግና ፣ ኤርትራን እንድትገነጠል ፣ መንገዱን ጨርቅ ያርግልሽ ብሎ ሲያበቃ ፣ ወደ ጥልቅ ብዝበዛ ጥቂት የእርሱ ሰዎች እንዲሰማሩ አደረገ ። አሜሪካኖቹ እና ምዕራብያዊያን ቱጃሮች ደግሞ ገንዘብን እንዲወድ ፣ የአገሩን ሰው ፣እንዲጠላ አደረጉት ።  የአገሪቱን ወርቅ እና ልዩ ፣ ልዩ ወድ ጌጥ ዘርፎ ፤   በየአገራቸው ባንኮች  ሀብት እንዲያከማች የሌባ ዋሻ ሰጡት ።

ተራው ዜጋ የበይ ተመልካች እንዲሆን ተደረገ ።  እንደነጮች ሁሉ ፣ በሠለጠነ መንገድ  በመርህ ደረጃ ፣ እርስ በእርስ እንዳይረዳ አገዛዙ በቋንቋ እና በዘውግ ከፋፈለው ። በአጭሩ “ ዘመነ ከፋፍልቲ “ ተጀመረ ። ወያኔ የተወሰኑ   ቋንቋዎች   የአትደረሱብኝ ግንብን እንዲያጥሩ አደረገ ።  አንዱ ለአንዱ እንዳይወግን በማደረግም “ የእኛ እና የእነሱ “ የሚል መናቆሪያ መድረክ ፈጠረ ። ጥቂቶችንም  ተጠቃሚ   በማድረግ ፣ በጥቅም እያባላ  በአንድ ቋንቋ ተናጋሪ ሥም ፣እና በክልል ሥም  ፣  የግል ሥርቆትን እያጧጧፈ ፣ ለ27 ዓመት ኢትዮጵያን በህገ አራዊት ሲገዛ ቆይቶ በድንገት ከወንበሩ ላይ እብሥ ብሎ መቀሌ መሸገ ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  “ላጉርስህ ሥትለው ልንከሥህ ካለህ ምን ትለዋለህ ??… “  መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ

ከዛስ  ፤ እንደምታውቁት ፤ ኢህአዴግ  ፣ ወደ ብልፅግና ተቀየረ ። ብልፅግናም ፣ ከወያኔ በሥተቀር ” አጋር ድርጅቶችን ” በሙሉ ወደ እራሱ አካቶ “ ብልፅግና “ የተሰኘ ፓርቲ መሠረተ   ። እናም በምርጫ መንግሥት ሆነ ። መሪውም አሻጋሪው አብይ አህመድ ሆኑ ። ( ጠቅላይ ሚኒሥቴር ዶ/ር  አብይ አህመድ ፤ የኢህአዴግ ጠቅላይ ሚኒሥቴር ፣ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ፣ የሚኒሥትሮች ምክርቤት ሰብሳቢ … እንደሆኑ አትዘንጋ )

ዶ/ር አብይ አህመድ ( ክ/ጠ/ሚ ) ፤ ለምዕራባውያን አልገዛም ባይ አፈንጋጭ መሪ ናቸው ። ይላሉ ብዙዎች  ። እርሳቸውም ይኽንን ባህሪያቸውን አልሸሸጉም ። እንደ ጥንቶቹ  ኢትዮጵያዊያን ጀግና አባቶቻችን   ለነጭ ተበርካኪ ወይም የበታችነት ሥሜት ያለማሳየታቸው አገርን ያኮራል ።በነጭ ማሥፈራርቾ የሚናጥ   መሪ ያለመሆን እጅግ የሚያኮራ ነው  ።  ይኽንን ባህሪያቸውን  ኢትዮጵያዊው ቢደግፈውም ፣ ተንበርካኪው እና ፈረንጅ አምላኪው ይጠላዋል ። ተበርካኪውና ፈረንጅ አምላኪው ፤ ሆድ አደር ፤ በብልፅግና ውስጥ ያለው ጭምር ፤  ይኽንን ኩሩነት ፈፅሞ አይወደውም    ። እናም ይኽ ሆዳም ቡድን ፣ ከምዕራባውያን ሰላዮች ጋር በህቡ ፣ በተደራጀ መልኩ  በእቅድ እየሰራ ሰውየውን ከኢትዮጵያ ህዝብ ለመነጠል ተከታታይ ሤራዎች እየገነጎነ በህቡ እየተገበረ እንዳለ የሚያሳዩ ብዙ ጠቋሚ ምልክቶች ዛሬ በግልፅ እየታዩ ናቸው ።  የተመሥገን ደሣለኝም ሆነ የዘመነ ካሤ እሥር ከእነዚህ አስብቶ አራጆች ሤራ ጋር   የተሰናሰለ ነው ። ( ብዙ የፖለቲካ ተንታኞችና ፣ በዕውቀት ጭቅላቶየመጠቁ የደህነነት ባለሙያዎች   በዚህ አሣብ ይስማማሉ ። )

በዚህ  ወቅት ፣ ይኽቺን  አገር ወደፊት ለማራመድ ቅን ፍላጎት መሪው ቢኖረውም አብረው የሚሠሩት ምን ያህል ቁርጠኛ ና ፆመኛ ናቸው ? ምን ያህል ከብዝበዛ የነፁ ናቸው ? የሚል ጥያቄ አንስቶ የባለሥልጣናቱን ገበና መፈተሽም በዚህ ወቅት  እጅግ አሥፈላጊ  ይመሥለኛል ። በአሉባልታ ሳይሆን በተጨባጭ የባለሥልጣናቱን  ጨዋነትም ሆነ ያልተገባ በህሪና ተግበር የሚገመግሙ የቅርብ ሰዎች ወይም ውሥጥ አዋቂዎች ብቻ እንደሆኑም አንዘንጋ ። ከዚህ አንፃር የሚመሩትን ህዝብ የሚመጥን ንፁህ ህሊና ያላቸውን የብልፅግና ከፍተኛ ፣ መካከለኛና ዝቅተኛ  አመራሮች ፣ እነዚህ ውሥጥ አዋቂዎች ሊጠቁሙን ይችላሉ  ። እንደ ማንኛውም ህዝበ ፣ ከግል ኑሯቸው አኳያ ከመዘንናቸው  ግን  ሥልጣን ቢሊዮነር ያደረጋቸው በጣት የሚቆጠሩ ባለሥልጣናት የሉም ብለን መናገር አንችልም  ። …

ተጨማሪ ያንብቡ:  ከመንግስት የቤቶች ግንባታ ጀርባ ያለው ትክክለኛ ዓለማ ሲገለጥ

ይኽንን አገር አውዳሚ የባለሥልጣናት  ብዝበዛ   ለማጋለጥ ደግሞ እንደ ባዓሉ ግርማ አይነት ደፋር  ጋዜጠኛ  ያሥፈልገናል ። ለሃቀኛ መንግሥት እና ለህዝቡ እንደ ተመሥገን ደሣለኝ እና እንደታዳዮስ ታንቱ አይነት ጋዜጠኞች እጅግ  አሥጸላጊ እንደሆነም መዘንጋት የለብንም ። “ሃቅን  ተናግሬ ና አሣውቄ ፣ ዛሬ ልሙት የሚሉ ጋዜጠኞች ይኽቺ አገር ከሌላት  ዴሞክራሲ እና የህግ የበላይነት በመላ አገሪቱ ሊንሰራፋ አይችልም ። የህግ የበላይነት እና ዴሞክራሲ ከሌለ ደግሞ አናርኪዝም ይሰፍናል ። የአናርኪዝም መሥፈን ደግሞ ለምዕራባውያን እና ለአሜሪካ በዝባዦች ጥርጊያ መንገድ ይከፍታል ። ለዚህም ነው የአውሮፖ  አንዳንድ ሚዲያዎች እና መንግሥታቱ ፣ ከአሜሪካ ሚዲያና መንግሥት ጋር ተቀናጅተው  ፣ የአገራችንን ገፅታ ለማበላሸት ፣ በትህነግ /ወያኔ አማካኝነት  proxy war የከፈቱብን ።

ይህ የውክልና ጦርነት በትህነግ አማካኝነት የተከፈተብን ፣ ኢትዮጵያውያን በጦርነት ማሸነፍ እንደማይቻል ከመቶ ዓመት በፊት በተጨባጭ በአደዋ ተራሮች  በማረጋገጣቸው  ነው ። እናም ይኽንን ጦርነት ልክ እንደ አደዋ  በድል ማጠናቀቅ ለአገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን በሙሉ እጅግ አሥፈላጊ ነው ። ለወደር የለሹ ና ህዝብን እፎይ ለሚያሥብለው ድል   መበሰረ  ደግሞ ፣ የአገሬ መንግሥት ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ውሥጡን በዓይነ ቁራኛ መከታተል እና ራሱን ከጥፋት ኃይሎች መጠበቅ  ይኖርበታል  ።  ኃቀኛ ጋዜጠኞችም ፣   በቀኃሥ ዘመን እንደነበሩት የህዝብን ብሶት ለመንግሥት አቅራቢ እረኞች  መሆናቸውን መገንዘብ አለበት ። እረኛህን እንዴት ታሥራለህ ? ራስህን በራስኽ እንቀህ አሰንድታጠፋ በመሠሪ የውጪ ጠላቶቻችን ለምን በየዋህነትህ ትገደዳለህ ?

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Untitled44444rrrr
Previous Story

የአማራ ዜጎች ከወለጋ የሰው ማረጃ ቄራ በሰላም እንዲወጡ የብልጽግና ፌዴራልና፣ የኦሮሚያና የአማራ ክልላዊ መንግሥቶች ግዴታና ተጠያቂነት አለባቸው

117095980 gettyimages 1174864672 1
Next Story

“በሥመ አብ! ” በሉ የኑሮ ውድነቱ የማይቀለበስ አደጋ ሊያሥከትል ይችላልና! – መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop