July 6, 2022
2 mins read

ጊምቢ ኤሎሄ ጊምቢ ቶሌ (ከአሁንገና ዓለማየሁ)

290684552 3309915649279615 7045677791337159006 n

290684552 3309915649279615 7045677791337159006 n
ጊምቢ ኤሎሄ ጊምቢ ቶሌ
ትእዛዝ ወርዶ ከእገሌ
ከሥልጣኑ ሉያ ሃሌ
ለማይካድራ ጅኒ ቆሌ
መስዋእት ሊቀርብ
በንጹሕ ደም መቅጃ አኮሌ
ዱበርቶኒ ፊ ኢጆሌ**
ተጨፍጭፈው
በወለጋ ጊምቢ ፎሌ
ካንዲት ጎጆ አሥር ሞቶ
ለኦነግ ዛር ተሠውቶ
መሬት ጭረው እህል ዘርተው
የሚኖሩ ከብት አርብተው
የማይጽፉ ማያነቡ
ጥያቂያቸው
ወጥተው ወርደው ቤት ሲገቡ
ሰላም ዋለ ቤተሰቡ?
መጣ ቀረ ወይ ዝናቡ?
ብቻ ሆኖ
አራት ኪሎ የሚያውቃቸው
አራት ኪሎን የማያውቁ
እንደ ዶሮ ተከታትፈው
እንደ አውሬ እየታነቁ
እንዲያ ሲያልቁ
ያስተዳድር የተባለው
የመመከት ሥልጣን ያለው
በከፈሉት ግብር ሰብቶ
ባመረቱት ቀለብ ገዝፎ
ካገር ጠላት ዲናር ልፎ
ይሁዳኛ እየሳመ
ሲሰጣቸው አሳልፎ
ጊምቢ ሆና ጎልጎታቸው
ቤትልሄምም ራሷ ጊምቢ
መንደራቸው ድንገት ሆኖ
የቀያፋው ትልቅ ግቢ
አርብ ማልዳ ደርሶባቸው
የኛ ያሉት ወገናቸው
ጴጥሮስኛ ሲክዳቸው
በጥላቻ ጅራፍ ገርፎ
የሮም አሽከር ሲይዛቸው
በክላሽ ጥይት ተቸንክረው
ገና ሳትወጣ ነፍሳቸው
እጣ ወጥቶ በልብሳቸው
ንብረታቸው ሲከፋፈል
ለወራሪ / ጃርት ፍልፈል
አስገርፎ አሰቅሎ
ጲላጦስ እጁን ቢታጠብ
የሌለበት አስመስሎ
የፈሰሰው ደም የወሎ
ያለበደሉ ተገድሎ
በወለጋ ጸሐይ ተንኖ
ሰማይ ጠቅሶ እንደ አውሎ
ገና ይወቅ/ሳል ዘላለም
ገና ይጮ/ኻል ለሁሌ
ጊምቢ ኤሎሄ! ጊምቢ ቶሌ!

* አኮሌ = ማለቢያ ቅል፣ ጮጮ፣ የፈሳሽ ማስቀመጫ
** ዱበርቶኒ ፊ ኢጆሌ = ሴቶችና ልጆች

መታሰቢያነቱ በሰኔ ወር 2022 ዓ.ም. በወለጋ በአማራነታቸው ተለይተው በመንግሥት መራሽ ጭፍጨፋ በጭካኔ ለተፈጁት ሰላማውያን እና ንጹሐን ኢትዮጵያውያን ይሁን።

1 Comment

  1. ሞቼ ቢሆን ያኔ
    የሰማይን ክፋት
    የዝናብን መጥፋት
    ከሰኔ እስከ ሰኔ፤
    ብቻ እንዳማረርኩኝ
    ምነው ሞቼ ቢሆን!
    እያልኩ ነው እኔ።
    እንዲህ አውሬ ሆኖ
    ከታትፎ ሊጥለኝ
    የገዛ ወገኔ፤
    የሚቀብረው አጥቶ
    በጅብ በአሞራ
    ሊበላ አስከሬኔ፤
    በሰባሰባቱ
    በዚያ በከፋው ድርቅ
    በሰው በላው ጠኔ፤
    ምነው በቀረሁኝ
    እዚያቹ መንደሬ
    ባልረዘመ ቀኔ።
    እንዲህ እድሜ ሰጥቶኝ
    የሰው ክፋት ሳላይ
    አውሪያዊ ጭካኔ፤
    ምነው በራብ ጥማት
    በተፈጥሮ ክስተት
    ሞቼ ቢሆን ያኔ።

    ከከፋው የሰሜን ኢትዮጵያ ረሃብ የደርግ መንግሥት በቀረጸው የወገን አድን የርኅራኄ ፖሊሲ ወደ ወለጋ፣ ባሌና ጎጃም ተወስደው ኑሯቸውን ሲገፉ ለነበሩ እና ዛሬ የጭካኔ፤ የእልቂት ጥቃት ዒላማ ለተደረጉ ሰዎች ጥልቅ ሐዘን መታሰቢያ።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

290911697 3240590282925440 1562147288998232031 n
Previous Story

በመንግስት ሚዲያዎች በተላለፈው ፕሮግራም እንደተመለከትሁት የፓርላማ ውይይት ላይ አንስቻቸው የነበሩ 3 የሥነ–ስርዓት አስተያየቶች/ጥያቄዎች ተቆርጠው እንዳይተላለፉ ተደርገዋል

EPRP 1
Next Story

የኢትዮጵያ ሕዝብ አብዮታዊ ፓርቲ የምሥረታ ወርቅ ኢዮቤልዩ ሲፈተሽ (ፕሮፈሶር ኀይሌ ላሬቦ)

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop