July 2, 2022
1 min read

በሸዋሮቢት በንፁሃን ላይ የመንግሥት ታጣቂዎች በከፈቱት ተኩስ የተሰው ሰዎች ቁጥር ከጊዜ ጊዜ እየጨመረ ነው

291897445 619922073032385 8076187310552108346 n
291897445 619922073032385 8076187310552108346 n ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ ሰባት ሰዎች መሰዋታቸው ይፋ ሆኗል።
ከጤና ተቋማት እየወጡ ያሉ ምስጢራዊ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ደግሞ፣ የሟቾች ቁጥር ወደ 12 ከፍ ሊል ይችላል። ከሃያ በላይ ቁስለኞችም በመታከም ላይ ናቸው።
“የመንግሥት ታጣቂዎች ቁስለኛ ለማሳከም የሄደን ሰው ሁሉ በጥይት ገድለዋል። ባጃጅ ውስጥ ነው የገደሏቸው። ሕዝቡ እያለቀሰ ነው” ብለዋል ያነጋገርናቸው የዓይን ምስክር።
“መንግሥት መምራት አቅቶታል። የሕዝቡን ጥያቄ መመለስ ባይችል እንኳን፣ ማወያያት ሲገባው በንፁሃን ላይ ተኮሰ። የመንግሥት እንቅስቃሴ ከዕለት ወደ ዕለት የሕዝቡን ቁጣ እየጨመረው ነው” በማለትም ያነጋገርናቸው የመረጃ ምንጭ ጨምረዋል።
አገዛዙ በሸዋሮቢት ተኩሶ የገደላቸውን ሰዎች ለመደበቅና ቁጥሩን ለማሳነስ እየሞከረም ይገኛል።
ዘገባው—-ሰሜን አሜሪካ ባልደራስ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

289658634 3235484913360632 6991151912790405950 n
Previous Story

ከትግራይ የመጡ የሽብር ቡድኑ አባላት በቁጥጥር ሥር ዋሉ

OLF
Next Story

አዲስ አበባ ያለው የኦነግ ቢሮ በኦነግ ሸኔ ላይ እየተወሰደ ነው ያለው ወታደራዊ እርምጃ እንዲቆም ጠየቀ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop