July 1, 2022
5 mins read

ገጣሚ በላይ በቀለ ወያ እስካሁን ያለበት አለመታወቁ እንዳሳሰባቸው ቤተሰቦቹ ገለፁ

291872148 5301770716606252 3757963387040603635 nገጣሚ በላይ በቀለ ወያ እስካሁን ያለበት አለመታወቁ እንዳሳሰባቸው የገጣሚው ቤተሰቦች ገለፁ።

 

ገጣሚ በላይ በቀለ ወያ ባሳለፍነው ማክሰኞ ሰኔ 21 ቀን 2014 ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ፈረንሳይ ለጋሲዮን ከሚገኘው ጊዮርጊስ ምግብ ቤት ” ትፈለጋለህ?!” ተብሎ እንደተወሰደ እህቱ ሰላም በቀለ ወያ ተናግራለች።

ማክሰኞ ዕለት ሰሌዳ በሌላቸው ተሸከርካሪዎች ውስጥ በነበሩና ሲቪል በለበሱ የፀጥታ አካላት ታፍኖ መወሰዱ እንደነገሯት ያስረዳችው ሰላም፤”በፌዴራል እና በየአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ቢሮ እንዲሁም በየካ ክ/ከተማ ውስጥ በሚገኙ ፖሊስ ጣቢያዎች ብንጠይቅም አድራሻው ሊገኝ አልቻለም“ ስትልም በማህበራዊ ሚዲያ ባስተላለፈችው የቪዲዮ መልዕክት ተናግራለች።

እህቱ አክላም “ፈረንሳይ ለጋሲዮን አካባቢ ወደ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን መሄጃ ባለ ፖሊስ ጣቢያ በዕለት መዝገብ አስመዝግበናል” ብላለች።

እናት እና አባቱ በድንጋጤ መታመማቸውን የገለፀችው ሰላም፤ እናቱ ጽጌ ገ/እግዚአብሔርም “ልጄ የት ነው ያለው?” ሲሉ አገር እና ሕዝብን መጠየቃቸውን ተናግራለች።

በመጨረሻም የወንድሟን ድምፅ ከሰማች ሦስት ቀናት እንዳለፉትና ያለበት አለመታወቁ መላው ቤተሰቡን ለከፍተኛ ጭንቀት እና ድንጋጤ መዳረጉን በመግለፅ፤ ጥፋተኛም ከሆነ በህግ አግባብ እንዲጠየቅና እንዲቀጣ ጠይቃለች።

– ምንሊክ ሳልሳዊ


288862105 1168003987113159 8003135180205440265 nBelay Bekele Weya
እርር ድብን አርጎ ፣ አንጀቴን ሚያቆስለኝ
መርጦ እየገደለ ፥ “መርጦ አልቃሽ” የሚለኝ!!!


ለግፍ ጥያቄ ፣ “በቃ!” ነው መልሱ
መፍትሔ አይኖርም ፣ እያለቀሱ !
——————————————————————
በጀግኖች ሀገር ላይ ፣ ለፈሪ ቀን ወጥቶ
“ጀግና ነኝ” ይለናል ፣ ንፁሃንን ፈጅቶ !!!
————————————————————
ሀቻምና በኦነግ ፣ አምና በወያኔ
ዘንድሮ በሸኔ
ሰበብ እያረጉ ፣ ያርዱኛል አቅደው
እኔን ካልገደለ
ሚኖር አይመስለውም ፣ የመጣ የሔደው።
።።
የመጣ የሔደው
ህመምህን ሳይሽር ፣ ቁስልህን ሳያክም
ሬሳህ ላይ ቆሞ
ማን እንደገደለህ ፣ ሊያስረዳህ ሲደክም
እንዳልቀረ አውቀህ ፣ ይቀራል ያልከው ግፍ
ወይ ለመኖር ታገል ፣ ወይ ሞትህን ደግፍ!!!
—————————————————————
በየቦታዉ ታርደህ ፣ ደምህ የትም ፈሷል
ጅምላ መቀበሪያ ፣ ጉድጓድህ ተምሷል
በየ ደረስክበት ፣ ሞትህ ተደግሷል
ይህንን እያወክ
ቀን በቀን ማላዘን ፣ ምን ይጠቅማል ለቅሶ?!
ትመር እንደሆነ ፣ ምረር እንደ ኮሶ!
——————————————————————
እያመመው መጣ “እያመመው መጣ
እያመመው መጣ ” እያመመው መጣ
ደሜ ባይገደብ ፣ ግፉ ባያባራ
ሁለት ስም አለኝ ፣ በሀገሬ ስጠራ
ስኖር “ኢትዮጵያዊ” ፣ ሲገድሉኝ “አማራ!”
———————————————————-
ዝናብ ባይኖር እንኳን
ቆስጣና ሰላጣ ፣ ችግኙን ትከሉ
አይቀርም በኔ ደም ፣ በኔ እምባ መብቀሉ !
—————————————————————
“መግደል መሸነፍ ነው” ፥ ብለው የነገሩን
በጅምላ በጅምላ ፣ አርገው ከሚቀብሩን
ምነው ማሸነፍን ፣ ሞተው ቢያስተምሩን?
———————————————————–
ልጄ…
ዝናብ ባይሰጥ እንኳን ፣ ሰማይ ተቆጥቶ
ችግኝ ለመትከል ፣ ተስፋ አትቁረጥ ከቶ።
አይቀርም ማደጉ ፣ የሰው ደም ጠጥቶ !
——————————-
ይነጋል ባልነው ቀን ፣ ጨለማው ገነነ
“አሻጋሪ” ያልነው ፥ አሸባሪ ሆነ !
=——————————————————-
አራት ዓመት ሙሉ
በወለጋ በኩል ፣ ጅምላ ስንቀበር
ለምን መንግስታችን
ዘመቻ አልጀመረም ፣ ህግ ለማስከበር?!????
እንጃ!
————————————————————-

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

Go toTop