በምዕራብ ወለጋው ጥቃት ወቅት ታግተው የተወሰዱ ሰዎች እንዳሉ ተገለጸ

24 ሰኔ 2022
ኮሚሽነር ሚሸል ባሽሌ
ኮሚሽነር ሚሸል ባሽሌ

በምዕራብ ወለጋው ጥቃት ወቅት ቁጥራቸው ያልታወቀ ሰዎች በታጣቂዎቹ ታግተው መወሰዳቸውን የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽን አመለከተ።

ኮሚሽኑ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች የተገደሉበትን ጥቃት አስመልከቶ ባወጡት መግለጫ ላይ እንዳመለከተው በርካታ ሰዎች ታፍነው መወሰዳቸውንና የት እናዳሉ እንደማይታወቅ ገልጿል።

በምዕራብ ወለጋ ዞን ጊምቢ ወረዳ፣ ቶሌ ቀበሌ ቅዳሜ ሰኔ 11/2014 ዓ.ም ታጣቂዎች በተፈጸመው ጥቃት የሞቱ ሰዎች ቁጥርን በተመለከተ የተለያዩ አሃዞች እየወጡ ቢሆንም በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች መሞታቸውና በሺዎች የሚቆጠሩ ደግሞ ለመፈናቀል መዳረጋቸው ተዘግቧል።

ከጭፍጨፋው የተረፉ ነዋሪዎችና መንግሥት ጥቃቱን የፈጸመው ‘ሸኔ’ በመባል የሚታወቀው ታጣቂው የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት እንደሆነ ሲገልጹ፣ ቡድኑ ግን ለጥቃቱ የመንግሥት ኃይሎችን ተጠያቂ አድርጎ ገለልተኛ ምርመራ እንዲደረግ ጠይቋል።

የመንግሥታቱ ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ሚሸል ባሽሌት በመግለጫው ላይ እንዳሉት የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት በጥቃቱ ዙሪያ ፈጣን፣ ገለልተኛና ዝርዝር ምርመራ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  አብን መከላከያ ሰራዊቱ ይቅርታ እንዲጠይቅ ጠየቀ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share