June 24, 2022
2 mins read

በምዕራብ ወለጋው ጥቃት ወቅት ታግተው የተወሰዱ ሰዎች እንዳሉ ተገለጸ

ኮሚሽነር ሚሸል ባሽሌ
ኮሚሽነር ሚሸል ባሽሌ
24 ሰኔ 2022
ኮሚሽነር ሚሸል ባሽሌ
ኮሚሽነር ሚሸል ባሽሌ

በምዕራብ ወለጋው ጥቃት ወቅት ቁጥራቸው ያልታወቀ ሰዎች በታጣቂዎቹ ታግተው መወሰዳቸውን የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽን አመለከተ።

ኮሚሽኑ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች የተገደሉበትን ጥቃት አስመልከቶ ባወጡት መግለጫ ላይ እንዳመለከተው በርካታ ሰዎች ታፍነው መወሰዳቸውንና የት እናዳሉ እንደማይታወቅ ገልጿል።

በምዕራብ ወለጋ ዞን ጊምቢ ወረዳ፣ ቶሌ ቀበሌ ቅዳሜ ሰኔ 11/2014 ዓ.ም ታጣቂዎች በተፈጸመው ጥቃት የሞቱ ሰዎች ቁጥርን በተመለከተ የተለያዩ አሃዞች እየወጡ ቢሆንም በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች መሞታቸውና በሺዎች የሚቆጠሩ ደግሞ ለመፈናቀል መዳረጋቸው ተዘግቧል።

ከጭፍጨፋው የተረፉ ነዋሪዎችና መንግሥት ጥቃቱን የፈጸመው ‘ሸኔ’ በመባል የሚታወቀው ታጣቂው የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት እንደሆነ ሲገልጹ፣ ቡድኑ ግን ለጥቃቱ የመንግሥት ኃይሎችን ተጠያቂ አድርጎ ገለልተኛ ምርመራ እንዲደረግ ጠይቋል።

የመንግሥታቱ ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ሚሸል ባሽሌት በመግለጫው ላይ እንዳሉት የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት በጥቃቱ ዙሪያ ፈጣን፣ ገለልተኛና ዝርዝር ምርመራ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

289657069 1443797642739351 1345654371750229589 n
Previous Story

ኢትዮጵያ በወሳኝ የሽግግርና የታሪክ መታጠፊያ ምእራፍ ላይ: የአብይ አህመድ ስልጣን መልቀቅ አስፈላጊነት – ገለታው ዘለቀ

290220971 5226566900790931 7998295253129720750 n
Next Story

ይነበብ «ወላሂ ሁለተኛ አማራ አልሆንም» የ 6 ዓመቷ ህፃን ከወለጋ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop