በጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ ጉዳይ የአማራ ክልል መንግስትና የአማራ ብልፅግና እጃቸዉን ሊያስገቡ ይገባል!! – ቹቹ ታደሰ

በዚህ አጀንዳ ዙሪያ ተመልሸ የመጣሁት የጋዜጠኛው መታፈን ያለንበትን አገራዊ ሁኔታ የሚያሳይ በመሆኑ ነው። እንዴት አንድ ታዋቂ ጋዜጠኛ ታፍኖ ለቀናት ያህል ደብዛው ጠፍቶ ይቆያል? ይህ አገራዊ የዜጎች የደህንነት ስጋት ማሳያ ነው።

ለዚህም ነው ዛሬም ይሄን እንቁ የአማራ ጋዜጠኛ ማን ነው የሰወረው? ብለን ለመጠየቅ የምንገደደው።

በጋዜጠኛው መታፈን ዙሪያ ብዙ አስተያየቶች እየተሰጡ ሲሆን፤ ቀላል ግምት የማይሰጣቸው ሰዎች ጋዜጠኛው የተሰወረው በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች ነው የሚል ቢሆንም መንግስት በጉዳዩ ዙሪያ ያለው ነገር የለም።

እንደሚገመተው አፈናው የተፈፀመው በመንግስት የፀጥታ አካላት ከሆነ፤ ልጁ በህጉ መሰረት በ48 ሰዓታት ውስጥ ወደ ፍ/ቤት መቅረብ ይገባው ነበር። ነገር ግን ይህ ሲሆን አልታየም።

መንግስት ስለ ጎበዜ እገታ ምንም አይነት እጁ ከሌለበት ደግሞ በዝች አገር ሌላ አካል ችግር እየተፈጠረ አለ ማለት ነው። ይሄም ማለት የአማራን ጉልሃን (elites) የሚያጠፋ ድብቅ ቡድን አዲስ አበባ ላይ ተቋቁሟል ማለት ነው። ይህ ከሆነ እጅግ አደገኛ ነገር ውስጥ መግባታችን ነው።

ያም ሆነ ይህ ጋዜጠኛ ጎበዜ የታፈነው በመንግስት አካላትም ሆነ በኢ-መደበኛ አካላት፣ ጋዜጠኛው የተጠቃው የአማራ ድምፅ በመሆኑ ስለመሆኑ ቅንጣት ታክል አልጠራጠርም።

ስለሆነም በአማራ ህዝብ ስም ስልጣን ላይ ያለ ማንኛውም አካል በተለይም የክልሉ መንግስትና መሪ ድርጅቱ የጎበዜ ጉዳይ አጀንዳቸው ሊሆን ይገባል።

የጎበዜ ጉዳይ ተጣርቶ ችግሩና የችግሩ ምንጭ በጊዜ ካልታወቀ፤ ለአማራ ጉልሃን በተለይም የአማራ ድምፅ ለመሆን ለሚሞክሩት ወቅቱ ከባድ እንዳይሆን እሰጋለሁ።

በመጨረሻም የአማራ ጉልሃን ‘ያንተ ቤት ሲንኳኳ ይሰማል እኔ ቤት’ የሚለውን የንቁ አባቶች አባባል ማስታወስ እወዳለሁ። ዛሬ ተከላክለን ያላቆምነው አደጋ ነገ በየቤታችን መግባቱ አይቀርምና ዛሬ ነው ነገም-በኔ ብለን መነሳት ያለብን።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የተቃውሞ ሰልፍ ጥሪ ለኢትዮጵያኖች በሙሉ: ቦታ: ዋይት ሀውስ ፊት ለፊት ቀን: ሰኞ8, 2013 ሰዓት: ከጠዋቱ 9 ሰዓት ጀምሮ

የጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ መታፈን የኛም የነገ ዕጣ እንዳይሆን ዛሬ እንጠይቅ! ይህ መልዕክት ለግለሰቦች ብቻ ሳይሆን ለተቋማት ጭምር የሚሰራ ነው!

1 Comment

  1. Surprise! Surprise!

    AL is writing about a library without even once mentioning his budy – the No. 1 guy in the country. Given the bad administration which is getting worse by the day, It seems AL has lost hope on the said guy and picked a neutral subject – a library. A good sign I would say. Next time he might write the TRUTH about the suffering of millions particularly Amaras.

    Nobody in his right mind will oppose the country and Addis having a serious library. But Al knows that a library of this size is established by law even before its construction begins. AL, a lawyer by profession – appears to me to have retired now – should have told us about what law created it including its objectives.

    That said, I would think Addis needed ten or twelve smaller libraries throuhout the city than one huge, fancy library which might not be accessible to the public. I wonder what the criteria would be to have access to the library. Even if open to the public, payment will hinders many from using it. It should be made free for all.

    Finally, I can’t hide my disappontement about AL’s reference to the Library of Congress which is not comparable to ours.

    And the books! Is MEDEMER a must reading for visitors? I hope not.

    AL! Writing about the new library is good, but how adding your voice to the call to end the suffering of millions in the country? You can’t pretend not to have seen or heard anything.

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share