የአቡነ ጳውሎስ መኖሪያ ቤት ውስጥ የተገኘው ሃብት አነጋጋሪ ሆኗል

ከሰሞኑ በአዲስ አበባ ታትሞ የተሰራጨው ቁምነገር መጽሔት እንደዘገበው ከሟቹ የአቡነ ጳውሎስ መኖሪያ ቤት ውስጥ የተገኘው ገንዘብ አንጋጋሪ ነው ይላል። እንደ መጽሔቱ ዘገባ ከሆነ “ፓትርያርኩ በየዓመቱ በዓለ ሲመታቸውን ሲያከብሩ ከየአብያተ ክርስቲያናቱ የሚበረከትላቸው ከጣት ቁጥር በላይ የሆኑ የወርቅ መስቀሎችና ከልዩ ልዩ ሀገር እህት አብያተ ክርስቲያናት የተበረከቱላቸው ውድ ውድ ስጦታዎችስ የት እንደደረሱ ባይታወቅም፤ የሞቱ እለት ታሽጎ የነበረው ቤት ሲከፈት የተገኘው አንድ የወርቅ መስቀል፣ 1 ሺህ የኢትዮጵያ ብር፣ 50 ዶላርና ጥቁቂት ብሮች የተመዘገቡበት የባንክ ደብተር ብቻ መሆኑ በከተማው መነጋጋሪያ” ሆኗል። ቁምነገር መጽሔት “ይልቅ ወሬ ልንገርህ” በሚለው አምዱ ያቀረበውን ሽሙጣዊ ዘገባ ያንብቡት።
የቀድሞው ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሐይማኖት… የቀድሞው የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ህብረት ፕሬዚዳንት…የቀድሞው የዓለም ሀይማኖቶች ለሰላም የክብር ፕሬዚዳንት… እነሆ ካረፉ ስድስት ወር ሆነ አይደል? እናስ? ታዲያ ምን አዲስ ነገር አለ? አልክ?
ምን መሰለህ? የፓትርያርኩ መኖሪያ ቤት ታውቀው የለ? የቱን? ቅድስተ ማርያም ቤተክርስቲያን አጠገብ የሚገኘው ነዋ፡፡

እናልህ ያ መኖሪያ ቤታቸው የታሸገው ፓትርያርኩ ያረፉ ዕለት ነበር፡፡ እናስ? እናማ ቤቱ ከታሸገበት ጊዜ ጀምሮ በጥብቅ ጥበቃ ስር ነበር፡፡ ለምን መሰለህ? ያው የሚወራውን አንተም ሳትሰማ አልቀረህም፡፡
ፓትርያርኩ ባለፉት 20 ዓመታት ቤተክርስቲያኒቱን ሲያስተዳድሩ ከየዓድባራቱና ከየገዳማቱ ፈሰስ የሚደረጉ ገንዘቦች ነበሩ ይባላል….. ከየአብያተ ክርስቲያናቱ የሚገባው (በተለይም ከነግሸን ማርያም፣ አክሱም ፂዮን ማርያም እና ቁልቢ) የሚገባው ወርቅና ሌላም ሌላም የከበረ ሀብት በቀጥታ የሚላከው ወደ እሳቸው ነበር ይባላል፡፡ ያው ይባላል ነው፤ እንጂ መቼም የተረጋገጠ ነገር የለም፡፡ ታዲያ ለምንድነው ፓትርያርኩ እንደሞቱ ቤቱ ታሽጎ በፌዴራል ፖሊስ ጥበቃ ስር የወደቀው? ጥርጣሬ ይፈጥራል፡፡ እናልህ አዲሱ ፓትርያርክ ብፁዕ አቡነ ማትያስ ባለፈው ሳምንት በዓለ ሲመታቸውን እንዳከበሩ የት ይግቡ? ቤቱ መከፈት አለበት በመባሉ ለዚሁ ተብሎ የተቋቋመው ኮሚቴ ባለበት ቤቱ ተከፍቶ ‹‹አሉ›› የተባሉትን ንብረቶች ተቆጥረው ምዝገባ ይካሄዳል በመባሉ ቤተሰቦቻቸው ሳይቀሩ ተገኝተው ነበር ተብሏል፡፡ እናልህ ቤቱ ሲከፈት ምን ቢገኝ ጥሩ ነው?
አንድ ወርቅ መስቀል…አንድ ሺህ የኢትዮጵያ ብር……50 ዶላር….ጥቂት ብሮች የተመዘገቡበት የባንክ ደብተር……በቃ….ሌላስ አልክ? ሌላው የብፁዕነታቸው አልባሳትና ቆብ ብቻ ነው የተገኘው፡፡ ሌላው የሳቸው ንብረት ያልሆነ የቤተክርስቲያኒቱ ስዕሎች መስቀሎች መቋሚያዎች አልጋና ወንበር ብቻ……
ፓትርያርኩ በየዓመቱ በዓለ ሲመታቸውን ሲያከብሩ ከየአብያተ ክርስቲያናቱ የሚበረከትላቸው ከጣት ቁጥር በላይ የሆኑ የወርቅ መስቀሎችና….ከልዩ ልዩ ሀገር እህት አብያተ ክርስቲያናት የተበረከቱላቸው ውድ ውድ ስጦታዎችስ…..አልክ? ይሄ የሁሉም ሰው ጥያቄ ነበር….
ከዚህ ሁሉ በኋላ ግን ብፁዕ አቡነ ማትያስ የጠየቁት አንድ ጥያቄ ነበር፡፡ ምን መሰለህ? ‹‹ፓትርያርክ መያዝ ያለበት የወርቅ መስቀል በመሆኑ የተገኘውን የወርቅ መስቀል ስጡኝ›› ብለው ፎቶ ላይ ገጭ አሉ፤…..በል ቻዎ

ተጨማሪ ያንብቡ:  ካሁን ቀደም በነፃ ከተለቀቁት ሙስሊሞች ውስጥ 2ቱ እንደገና እንዲከላከሉ ተወሰነ

7 Comments

  1. Dear Zehabesha Editor,

    You guys are awsome. Every day u guys comes up with new info. That’s why i keep follow you every day.

    God Bless Your Good Work!

    • I don’t know how you manage to have the guts to call the almighty’s name while condoning this awful article…do you even understand the meaning of ‘Bless’? please read the great book attentively and understand the meanings of the words that you use dear brother…the great book is your only salvation my brother!

      “Rise in the presence of the aged, show respect for the elderly and revere your God. I am the LORD.” Leviticus 19:32

  2. ዘ-ሐበሻዎች እናመሰግናለን ስለመረጃው። የአቡነ ጳውሎስ ገንዘብ ወደ ውጭ ሃገር እንደሸሸ እኔ ካሉኝ መረጃዎች አውቃለሁ። በዘመዶቻቸው ስም ሁሉ ነገር ተመዝግቧል። ያ ሁሉ የሃገሬ ኦርቶዶክስ አማኝ ስም የተሰበሰበ ወርቅ ግን እንዲህ መቀለጃ መሆኑ ያሳዝናል። የትግሬዎች ዝርፊያ በቤተክርስቲያንም ውስጥ ጠንክሮ መቀጠሉን አንድ በሉ። ለዚህ እክ ነው ትግሬን ዋልድባ ፈረሰ ስትለው ጆሮ የሌለው

  3. Woyane ethnic fascits terrorize their People so as to promote their looting but not while terrorizing is a prerequisite for development. Look at the homes of Azeb and other looters and you will wonder what you will find. Say no to These home grown fascists and build a free and democratic Ethiopia. That is why they are imprisoning Ethiopian heroes like Eskinder Nega so that nobody speaks about their evil deeds. http://vimo.com/18242221
    http://www.genocidewatch.org/ethiopia.html
    http://www.ecadforum.com/2012/12/19/from-ethnic-liberator-to-national-atrocities-the-tale-of-tplf

  4. Now, he is going to do the same thing, even more. He already took a picture with the Gold gross…what is next?

  5. Maferiyawoch hulum beterawu mewaredu ayekerm. Me.Tazabiw The Bible didn’t say I am the arch bishop instead I am the lord, don’t fool your self.

Comments are closed.

Share