የሕወሓቱ ልሳን ወይን ጋዜጣ አዘጋጅ ደብዛው ጠፋ

አብርሃ ደስታ ከመቀሌ

የወይን ጋዜጣ አዘጋጅ በመሆን ህወሓትን ለረጅም ግዜ ሲያገለግል የነበረው ጋዜጠኛ ሐገዞም መኮነን አዲስ አበባ ከሚገኝ ቤቱ ከጠፋ ሁለት ሳምንታት አለፉ። ጋዜጠኛ ሐገዞም መኮነን ወይን ጋዜጣ ሲያዘጋጅ ቆይቶ ከቅርብ ግዜ ወዲህ የህወሓት የዓፈና ተግባራትና አካሄድ በግልፅ መቃወም ከጀመረ ወራት አስቆጥሯል።

ከወይን ጋዜጣ አዘጋጅነት ለቆ የወይን ጋዜጣና የህወሓት የዓፈና ስትራተጂዎች የሚያጋልጥ መፅሓፍ ፅፎ ሊያስመርቅ በዝግጅት ላይ እያለ ያልታወቁ የፀጥታ አካላት በሌሊት ከቤቱ እንደወሰዱትና እስካሁን ያለበት እንደማይታወቅ ተገልፀዋል። ከወራት በፊት ማህተመስላሴ ገብረእግዚአብሄር የተባለ የሰሜን የፌደራል ፖሊስ የሎጂስቲክስና ፋይናንስ ሓላፊ በመቐለ ከተማ 16 ቀበሌ በፀጥታ ሃይሎች መገደሉ ይታወሳል።

በፀጥታ ሃይሎች የተፈፀመ ሙስና እንዳያጋልጥ በሚል ምክንያት ነው የተገደለው። በህወሓት አባላት ላይ ተደጋጋሚ ዓፈናና ግድያ ይፈፀማል፤ ግን አይጋለጥም። የማይጋለጥበት ምክንያት ግልፅ ነው።

ተጨማሪ ያንብቡ:  አየር ኃይል ላይ ጥቃት ሊያደርሱ ነበር የተባሉ ተከሳሾች ተበየነባቸው

2 Comments

  1. Aberha desta ,I am tired of your fugera.the person might be in Europe for vacation or in America to work for Esat radio.esat is busy hiring so called journalist ffrom weyane medias like sheger radio,radio fana,reporter or addis neger gazeta and so on we might see or hear him on Esat .

Comments are closed.

Share