የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ አስተዳደር ከልክሏል! # አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ያለው ልብስም ተከልክሏል!

#ዜና #መረጃ
# የአጼ ምኒልክ ምስል ያለው ልብስ እንዳይለበስ

በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የአጼ ምኒልክ ምስል እና ኮከብ የሌለው አረንጓዴ፣ ቢጫ፣ ቀይ ሰንደቅ ዓላማ እንዳይያዝ በይፋ መከልከሉን ተማሪዎች ገለፁ፡፡ “ ነፍጠኛ ዳውን ዳውን” በማለት ሰሞኑን ቪዲዮ ቀርፀው በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በለቀቁት ኦሮምኛ ተናጋሪ ተማሪዎች ጥያቄ መሠረት፣ የዩኒቨርስቲው አስተዳደር በሰጠው ውሳኔ የዩኒቨርስቲው ተማሪዎች የአጼ ምኒልክ ምስል ያላቸውን ማናቸውም ልብሶች መልበስ የተከለከሉ መሆኑን፣ በተጨማሪም ኮከብ የሌለውን አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ሰንደቅ ዓለማ መያዝ እንደማይችሉ ገልጾ፣ ውሳኔውን በጽሁፍ አስፍሮ በዩኒቨርስቲው ግቢ ውስጥ ለጥፏል፡፡
በዚህ ውሳኔ የልብ ልብ ያገኙ ተማሪዎች፣ “ነፍጠኛ ዳውን ዳውን ” የሚለውን መፈክራቸውን ከማጠናከራቸውም ባሻገር፣ አረንጓዴ፣ ቢጫ፣ ቀይ ያለውን ማንኛቸውን ልብስ ለብሶ የሚያገኙትን ተማሪ እስከ መደብደብ ደርሰዋል፡፡ ሌላው ቀርቶ፣በዊልቸር የሚሄድ አንድ ተማሪ የአጼ ምኒልክ ምስል ያለበትን ቲሸርት ለብሶ በመገኘቱ ከበድ ያለ ድብደባ ደርሶበታል፡፡ ማታ ማታም በየዶርሙ እየዞሩ፣ “የአማራ ተማሪዎች ውጡ” በማለት ከፍተኛ ረብሻ ሲፈጥሩ ሰንብተዋል፡፡
ድብደባውን እና ሁከቱን የሚፈጽሙት ተማሪዎች ይፋዊ ባልሆነ መንገድ “የመንግሥት ድጋፍ አለን” ብለው ስለሚተማመኑ፣ ለሕግ ተገዢ ለመሆን ፈጽሞ ፈቃደኛ አለመሆናቸውን ብዙሃኑ ተማሪዎች ይናገራሉ፡፡ በትላንትናው ምሽት ግቢውን ለቀው የወጡት ተማሪዎች የአማራ ተማሪዎች ብቻ ሳይሆኑ፣ በረባሽ ተማሪዎቹ እና ሕግን ማስከበር በተሳነው የዩኒቨርስቲ አስተዳደር የተበሳጩ ከሁሉም ክልሎች የተውጣጡ ተማሪዎች ናቸው፡፡
በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በዛሬው ዕለት የመማር ማስተማሩ ሂደት ከሞላ ጎደል ቆሟል የሚባልበት ደረጃ ላይ ሲሆን፣ ትላንት አብዛኛው ተማሪ በግቢው ውስጥ አላደረም፡፡ ዛሬም በአብዛኛው ወደ ክፍል ገብቶ ትምህርቱን አልተከታተለም፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  የዘንድሮ ቁልቢ ገብርኤል አከባበር

ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ

2 Comments

  1. የሚጠበቅ ነው የትምህርት ሚንስትር ያልተመረጠው ብርሀኑ ነጋ ነው ሽመልስን ለማስደሰት ብዙ ርቀት ይሄዳል።

  2. I was going to say “Bravo OPDO/OLF/TPLF” but the real congratulations goes to their creator: Fascist Italy and other colonial masters. Their descent into submissive slavery and how readily they are serving their colonial masters should even surprise their ‘creators’. To be against the very symbol of African freedom could only have been achieved via a mental software that the colonizer installed in this outwardly African looking human.

    Yes bravo to colonial Europe that managed to avenge its defeat at Adwa by mentally colonizing the descendants of the victors.

    Our university had always been a hotbed for insurgencies inspired by the enemies of Ethiopia. It should be proud that it is keeping its proud tradition of dismantling the nation.

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share