ዐብይ አሕመድና የኦነግ አራጅ ሠራዊት – መስፍን አረጋ

ከጦርነት ዝግጅቶች ውስጥ አንዱና ዋናው ጠላትህን ጭራቅ አድርገህ በመሳል፣ ተዋጊወችህ የሚዋጉት ከሰው ጋር ሳይሆን ከጭራቅ ጋር እንደሆነ፣ የሚገድሉትም ሰው ሳይሆን ጭራቅ እንደሆነ እንዲያስቡ በማድረግ፣ በጠላታቸው ላይ ማናቸውንም ዓይነት ጭካኔ ቢፈጽሙ ምንም ዓይነት የህሊና ወቀሳ እንዳይሰማቸው ማድረግ ነው፡፡    የወያኔና የኦነግ  አመራሮች መሠረታዊ ጠላታችን ነው ብለው ጦርነት ባወጁበት በአማራ ሕዝብ ላይ ያደረጉትም ይሄንኑ ነው፡፡

የኦነግ ወንበዴወች አማራ ሲያርዱ ምንም አይሰማቸውም፣ ምክኒያቱም በነሱ እይታ መሠረት የሚያርዱት ሰው ሳይሆን አማራ ነውና፡፡  የኦነግ ሽፍቶች የአማራን ሕጻናት ጎጆ ውስጥ ሰብስበው ሲያንጨረጭሩ ምንም አዘኔታ አይሰማቸውም፣  ምክኒያቱም በነሱ እይታ መሠረት የሚያንጨረጭሩት ሕጻናትን ሳይሆን የአማራ ሕጻናትን ነውና፡፡  የኦነግ ቄሮወች ከአማራ አስከሬኖች በተቆረጡ እጆና እግሮች ሲጨፍሩ ደስታውን አይችሉትም፣ ምክኒያቱም በነሱ እይታ መሠረት እነዚህ እጆችና እግሮች የሰው ሳይሆኑ የአማራ እጆችና እግሮች ናቸውና፡፡  የኦነግ አክራሪወች የአማራ ሬሳወችን በሞተር ሳይክል ሲገትቱ ምንም አይሰቀጥጣቸውም፣ ምክኒያቱም በነሱ እይታ መሠረት ሬሳወቹ የሰው ሳይሆኑ የአማራ ናቸውና፡፡  የኦነግ ታጣቂወች የአማራ ነፍሰጡሮችን ማሕጸኖች ሲዘረክቱ ድሪቶ የቀደዱ አይመስላቸውም፣ ምክኒያቱም በነሱ እይታ መሠረት የሚዘረክቱት የሰው ነፍሰጡሮችን ሳይሆን፣ የአማራ ነፍሰጡሮችን ነውና፡፡

ባጠቃላይ አነጋገር የአነግና የወያኔ አመራሮች በአማራ ሕዝብ ላይ ማናቸውንም ዓይነት ጭፍጨፋና ውድመት ሲፈጽሙና ሲያስፈጽሙ ደስታውን አይችሉትም፣ ምክኒያትም በነሱ እይታ መሠረት የሚጨፈጭፉትና የሚያወድሙት ሰውን ሳይሆን አማራን ነውና፡፡  ዐብይ አሕመድ ደግሞ ከነዚህ ዓይነት የኦነግና የወያኔ አመራሮች ጉያ ሥር የአማራን ጥላቻ እየተጋተ ያደገ የኦነግና የወያኔ ዲቃላ ነው፡፡  አወ፣ ዐብይ አሕመድ አማራን በጭራቅ አምሳል እንዲመለከት ተደርጎ የተቀረጸ የኦነግና የወያኔ ቅጥቅጥ ነው፡፡  አማራ ጭራቅ አድርጎ እንዲመለከት ስለተደረገ ደግሞ እጅጉን ይጠላዋል፣ በዚያው ልክ ደግሞ አጅጉን ይፈራዋል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሁሉንም መንግሥታዊ ጉዳዮች ከህዝብ እና ከሀገር ጥቅም አንፃር መመልከት ይበጃል። (ትህዳ ኃሣኤ ዘ ኢትዮጵያ)

በወለጋ አማሮች ላይ የሚካሄደው ዘግናኝ ጨፍጨፋ ለዐብይ አሕመድ ዴንታ አይሰጠውም፣ ምክኒያቱም በዐብይ አሕመድ እይታ መሠረት የሚጨፈጨፉት ሰወች ሳይሆኑ አማሮች ናቸውና፡፡  ለዚህ ነው በጭፍጨፋው ማዘኑን ለይምሰል ያህል እንኳን አንድም ጊዜ ያልገለጸው፡፡  በተቃራኒው ግን በጭፍጨፋው ዕለት ወይም ማግስት ሕንጻ እየመረቀ ወይም አበባ እየተከለ በጭፍጨፋው መደሰቱን በተግባር ይናገራል፡፡

ዐብይ አሕመድ የአማራን ሕዝብ በምን ዓይን እንደሚመለከት ፍንትው አድርጋ የምታሳየው ግን የኦነግ ጨፍጫፊወችን የወለጋ አርሶ አደሮች ለምን ይደግፏቸዋል ብለን መጠየቅ አለብን በማለት በፓርላማ ውስጥ እንደዋዛ የተናገራት ንግግር ናት፡፡  በዚች ንግግሩ ዐብይ አሕመድ ለማለት የፈለገው የአማራ ሕዝብ በዘግናኝ ሁኔታ በኦሮምያና በመከተል የሚጨፈጨፈው፣ በዘግናኝ ሁኔታ እንዲጨፈጨፍ የሚያበቁትን ወንጀሎች ስለሠራ ነው ነው፡፡  በሌላ አባባል በዐብይ አሕመድ እሳቤ መሠረት ኦነጋውያን አማራን የሚጨፈጨፉት ምክኒያት ስላላቸው ስለሆነ፣ ጥፋተኞቹ ተጨፍጫፊወቹ እንጅ ጨፍጫፊወቹ አይደሉም፡፡

ከሱማሌ ክልል ‹‹ተፈናቀሉ›› በሚል ሰበብ በመቶ ሺ የሚቆጠሩ ኦሮሞወችን አዲስ አበባ ላይ ኮንዶሚኒየም እየሰጠ በማስፈሩ ተኩራርቶ የተናገረው ዐብይ አሕመድ፣ ከኦነግ ጭፍጨፋ የተረፉትን የአማራ ተፈናቃዮች (በተለይም ደግሞ ሕጻናትንና አረጋውያንን) ግን በረኻ ለበረኻ እያንከራተተ በጠኔ እየጨረሳቸው ነው፡፡  ምክኒያቱም በሱ እይታ መሠረት ተፈናቃዮቹ ሰወች ሳይሆኑ አማሮች ናቸውና፡፡

ዐብይ አሕመድ ተራ ኦነጋዊ ቢሆን ኖሮ፣ በከረረ (chronic) የስነልቦና በሽታ የሚሰቃይ በሽተኛ ነው ተብሎ ተንቆ ይተው ነበር፡፡  ዐብይ አሕመድ ግን የጦቢያን በትረ መንግሥት የጨበጠ፣ አፉና ምግባሩ ሐራምና ቆቦ የሆነ፣ የኦነግ ኦቦ ነው፡፡  የአማራ ሕልውና ጥያቄ ውስጥ የገባው ደግሞ ይህ የአማራን ሕዝብ እንደ ሰው ሳይሆን እንደ ጭራቅ የሚመለከት፣ የአኖሌን ሐውልት ለማስገንባት ከፍተኛ ሚና የተጫወተ፣ ኦነጋዊ አውሬ የጦቢያ መሪ በመሆኑ ነው፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  የኮነሬል አብይ የነፍስ ገበያ በኢትዮጵያ!!! አንድ ሐሙስ የቀረው ጊዜ የሠጠው ሲሶ መንግሥት!!!

ስለዚህም የአማራ ሕዝብ ሕልውናውን ማስቀጠል የሚችለው ከዚህ ኦነጋዊ አውሬ ጋር ጉሮሮ ለጉሮሮ ተናንቆ አውሬውን ከጫንቃው ላይ ካወረደ ብቻና ብቻ ነው፡፡  የአማራ ሕዝብ ዐብይ አሕመድን ከጫንቃው ላይ ካወረደ ደግሞ፣ ዐብይ አሕመድ ያዘላቸው ኦነግና ወያኔ አብረው ስለሚፈጠፈጡ፣ ባንድ ዲንጋ ሦስት ወፎች ያረግፋል፡፡

የአማራ ሕዝብ የሕልውናው ዋናው ጠላት ከሆነው ከዐብይ አሕመድ ጋር የሞት ሽረት ትግል የሚያደርገው ግን የሕልውናው ዋና ጠላት እሱና እሱ ብቻ መሆኑን ያለ ምንም ጥርጥር ተገንዝቦ፣ ውጉዝ ከመ አርዮስ እያለ፣ በጽኑ ሲያወግዘው ነው፡፡  በጽኑ ያላወገዝከውን በጽኑ አትታገለውም፡፡

ስለዚህም ለአማራ ሕልውና በጽኑ እየታገላችሁ ያላችሁ የሚዲያ ሰወች እባካችሁ ይሄን ጽኑ ጉዳይ በጽኑ አስቡበት፡፡  ለአማራ ሕዝብ አርዮስ የሆነውን ዐብይ አሕመድን፣ ጠቅላይ ሚኒስትር፣ ዶክተር፣ እርስወ እያላችሁ በማይገባው ከበሬታ በመጥራት የሰውነት ባሕሪ እየሰጣችሁ፣ የአማራ ሕዝብ በዚህ አርዮስ ላይ ጨርሶ እንዳይቆርጥበት አታድርጉት፡፡

የአማራ ሕዝብ ዋና የሕልውና ጠላት በዐብይ አሕመድ ላይ የቆሙት ኦነግና ወያኔ ሳይሆኑ ራሱ ዐብይ አሕመድ መሆኑን የአማራ ሕዝብ ከገጠመኙ ቢያውቅም፣ እናንተ የሚዲያ ሰወች ስታንቆለጳጵሱት ግን ጥርጣሬ እንዲገባበትና ዋና ትኩረቱን ከዐብይ አሐመድ ላይ እንዲያዞር ታደርጋላችሁ፡፡  ዐብይ አሕመድ ደግሞ ሲዞሩበት እየትጥመለመለ ሲዞሩለት የሚናደፍ መሠሪ ዕባብ ስለሆነ፣ ፊቱን ወደ መናኛ ጠላቶቹ ያዞረውን የአማራን ሕዝብ ከጀርባው እየነደፈ መጨረሱን ይቀጥላል፡፡

በሕልውና ጦርነት ላይ ጨዋነት ትርጉም የለውም፣ ለዚያውም ደግሞ ጨዋ የሚለው ቃል በቋንቋው ውስጥ ስለሌለ ጨዋነትን ከፈሪነት ለሚቆጥር ኦነግንና ወያኔን ለመሰለ የሕልውና ጠላት፡፡  ዐብይ አሕመድ መጠራት ያለበት በተቀመጠበት መንበር ሳይሆን በግብሩ ነው፡፡  አይሁዶች የናዚ ጨፍጫፊወችን የሚጠሯቸው የኦሽዊትዝ አራጅ (the butcher of auschwitz)፣ የምንትሴ ቀርዳጅ እያሉ በስማቸው ሳይሆን በግብራቸው እንደሆነ ሁሉ፣ አነጋዊው ናዚ ዐብይ አሕመድም መጠራት ያለበት የወለጋው አራጅ፣ የመተከሉ አወራራጅ እየተባለ ነው፡፡  ኢትዮ360ወችና አዲስ ድምጾች ሰማችሁኝ?

ተጨማሪ ያንብቡ:  ምርኮኛ - አገሬ አዲስ

 

መስፍን አረጋ

mesfin.arega@gmail.com

9 Comments

  1. አምባቸው በቀለና እውነቱ ፕሮፌሰሩ ጽፏል የወንጀል ብር በልቶ መተኛት የለም ውጡና ባዶነታችሁን አሳዩን። መሀይም እውነትም ደፋር ነው።

  2. “ጠላትህን ጭራቅ አድርገህ በመሳል፣ ተዋጊወችህ የሚዋጉት ከሰው ጋር ሳይሆን ከጭራቅ ጋር እንደሆነ፣ የሚገድሉትም ሰው ሳይሆን ጭራቅ እንደሆነ እንዲያስቡ በማድረግ፣ በጠላታቸው ላይ ማናቸውንም ዓይነት ጭካኔ ቢፈጽሙ ምንም ዓይነት የህሊና ወቀሳ እንዳይሰማቸው ማድረግ ነው።”
    ~ ዲባቲት መስፍኔ

    የተለከፈ ያህል፣ “ዐብይ፣ ዐብይ” ማለቱ ለምን ይሆን ለሚለው አሁን ግልጽ ሆኖልኛል።
    መስፍኔ፣ ጠላቱን ዐብይን ጭራቅ አድርጎ በመሳል፣ ተከታዮቹም ጭራቅ እንደሆነ እንዲያስቡ በማድረግ፣ ማናቸውንም ዓይነት ጭካኔ ቢፈጸም ምንም ዓይነት የህሊና ወቀሳ እንዳይሰማው ማድረግ ነው!

    መንግሥት ገልብጦ የአማራ መንግሥት ለመመሥረት ሲያሤር ተይዞ የተገደለው ያገር ልጅ አሳምን ጽጌ ምሬት ዲባቲት መስፍኔን በዐብይ ላይ ብርቱ ጥላቻ እንደ ፈጠረበት አንዘንጋ!

  3. አለም ዛሬም ደፍረህ ጻፍክ መሀይምን ካሳደገ የገደለ ጸደቀ ለሚሉት ብሂል ማረጋገጫ ነህ።

  4. አለም፦ አንተኮ ለምን እንደምትጽፍ እኔ በደንብ ይገባኛል፡፡ ኑሮህ ነው፡፤ ገንዘብህ የማግኛ መንገድህ ነው፡፤ እንደነ ሲሳይ አጌና ማለቴ ነው፡፡ ችግሩ አንተም የኢሳቱ ሲሳይ አጌናም ሌሎች ሆድ አደሮችም አብይን በህዝብ ከመጠላት፣ ቆይቶም ተዋርዶ ከስልጣኑን ከመውረድ ከስልጣኑም ወርዶ በህግ ፊት ከመቅረብ ናፍርዱንም ከማኘት ልታድኑት አትችሉም፡፤ ምክንያቱም ሰውየውን የጠላው ህዝብ ነው፡፤
    ይሄ አጭበርባሪና ሳሙና የሆነ ሰውዬ ብዙ ንጹሀንን ነው ያሳረደው፡፡ እንዳይታረዱ ማድረግ ሲችል፡፤ ታዲያ ይህ ሰው ነውን ወይንስ በሰው አምሳል የሚንቀሳቀስ ሰይጣን? የታረዱትን ሰወችኮ በቴሌቪዥን ቀርቦ አስክሬናቸውን በዘራቸው ነው የቆጠረልን፡፡
    ታዲያ ይህ ሰው በቁመናው ልክ ራሱ ጉድጓድ እንንድቆፍር ተድርጎና በዚያ ጉድጓድ ውስጥ አንገቱን ብቻ ውጭ እንዲቀር ሆኖ እዚያ ቢቀበር ምን ያሳዝናል?? የብዙ ሽህወች ንጹሀን ደምኮ ይጮሀል!

  5. አይ እውነት ቢሆን የዋህ ነህ። እውነቱ፤አምባው በቀለ፤አለም ወደው አይደለም እዘንላቸው በህይወት አጋጣሚ መተዳደሪያቸው ይኸው ሁኗል እነሱን ሰው ለማድረግ አትድከም ደግነቱ መስፍን ሰው አይደሉም ሰው ለመሆን ብዙ ይቀራቸዋል ብሎ ስለደመደም የነሱን ስም ሲያይ ይዘለዋል፤ያዝንላቸዋል ስለማይገባቸውም ይስቅባቸዋል። አስተሳሰባቸው ቀሊል ከምክንያታዊንት በእጅጉ የራቁ በመሆኑ እንደእኔ እንደእኔ ቢቻል መስፍን ከጥላሁን ይልማ ጋር በመሆን ወድ ምርምር ክፍሉ ወስዷቸው በአይጥ ጥናት ከማድረግ በነሱ ላይ ቢካሄድ ለህብረተሰቡ ጥቅም ይመስለኛል መቼም ቁመው ከሚሰጡት ጥቅም በላይ በዚህ ሁኒታ የተሻል ጥቅም ሊሰጡ ይችላሉ የሚል እሳቤ አለ።

  6. አይ ጉድ ስምና ተግባር።እንደ ፊዚክሱ ሊቅ ፕሮፊሰር መስፍን አርጋ ያሉ ዘረኛ እና ደካሞች ባይኖሩ ኖሮ ፤እንደ እነ ቢረጋ እና እውነቱ ቢሆን ቱልቱላ ነፌ ገበረ አይጦች በሀገር ውሥጥ ባይኖሩ ኖሮ ኢትዮጵያ ሰላም ትሆን ነበር። የፊዚክስ ሊቀ ሊቃውንት መስፍን አርጋ እንኳን እንዲህ መከራውን የሚያይ የአማራ መንግሥት ቢገለበጥ ትርፍራፊ የማግኘት ህልሙ በመክሸፉ እና ተይዞ ሳይሆን በበጃጃ ሲሮጥ የተገደለው አሳምነው ጽጌ ቁጭት እንቅልፍ በማጣቱም እንደሆነ አይዘንጋ።

  7. አምባው በቀለና አለም፦
    ሁለታችሁም የውሸታሞች እንግደ ልጆች ናችሁ፡፤ ወይ በደንብ አትዋሹ ወይ በደንብ አታቀረሹ፡፡ ጭንጋፎች ናችሁ፡፤ ኢትዮጵያ እንዲህ ቢሆን ኖሮ…… እንዲያ ቢሆን ኖሮ…. በሚል ሰበብ ሰላሟን ታገኝ ነበር ብሎ ቀልድ የለም፡፡ ሰላሟን የምታገኘው ወያኔን አሽቀንጥራ እንደጣለች ሁሉ ኦሮሙማን አሽቀንጥራ ጥላ ሁለቱንም ስትቀብራቸው ብቻ ነው፡፡ አብይ አህመድ በቀኝ እጁ የኦነግን ባንድራ በግራ እጁ የወያኔን መፈክር ይዞ አገሪቱን ወደማትወጣበት አዘቅት እየወሰዳት ስለሆነ ከሁሉ በፊት እርሱ መወገድ አለበት፡፡ እርሱ ስልጣን ላይ ሆኖ አገሪቱ ሰላሟን በጭራሽ አታገኝም; ሰውየው ሰይጣንን ያስንቃልና!
    ይህ የሚሆንበት ቀኑ ሩቅ አይደለም፡፡ተጀምሯል፡፡ እስከዚያው እናንተም ጌታችሁ ባለጌው አብይ በስልጣን እካለ ድረስ የሚወረውርላችሁን ሳንቲሞች እየለቃቀማችሁ ተቀደዱ፡፤ መቼስ እንደ ሰው የሚቆጥራችሁ ስለሌለ!!

  8. ገጽታ?
    ገጸ ከለባት ሲገዙ ባላህ ቁጣ አለንጋ
    ያለ አበሳው በጎጆው ሲወድቅበት አደጋ
    ደሃ በካራ ታርዶ ተጨፍጭፎ ወለጋ
    መውጫ መግቢያ መንገዱ በታጣቂ ሲዘጋ
    ተሽሎክሉኮ በጫካ በቆላ መሬት በደጋ
    ፍትህ ይሰጠኛል ብሎ የተቀመጠው በአልጋ
    ከጭፍጨፋ ትራፊ የአማራ ትውልድ ቢመጣ
    ቤተክርስትያን ደጅ ወድቆ ለተጠለለው በታዛ
    ይቆሽሻል ተባለ የከተማችን ገጽታ
    ምን ገጽ አለው ከተማሽ የ”ፈርስ ከርስ” ስልቻ
    አላለውም ወይ ተረኛ አንዱ የፓርቲሽ ጉልቻ
    አንቺ ነሽ እንጂ ቆሻሻ የጎሳ ኮተት መክተቻ
    አለቃሽን ታምራት “ገተት” ነው ያለው “ግትቻ?”
    እነሱማ ንጹሐን እንዳልቀለመ ብራና
    በፖለቲካ እንቶ ፈንቶ ያልቆሸሸ ኅሊና
    ሃሳባቸው ያርሷደር በሬ እርሻ ደመና
    ውሎ መግባት በሰላም ወጥቶ መግባት በጤና
    ገጽታ አልሽ? ገጸ ቢስ! የሸገር ታሪክ አተላ
    ግብራቸው ነው ቀለብሽ ከጉቦ ውጭ ሲሰላ

  9. አይ የኔ መኮንታው በረደድ፡እውነት ብለሃል እንዲያው ለመሆኑ የውሸታሞች እና የእውነተኛ እንግዴ ልጆችን በምን ለየሃቸው? ነው ወይስ የውሸታሞች እንግዴ ልጅ ማህበርተኛ ፕሪዘዳንት መሆንህን ልትነግረን ነው? ከፊዚክሱ ሊቅ ቆንጽለህ ከሆነም አሳውቀን እንጂ፤ በላባችን ሰርተን የምንኖር፤ሳንቲም ተወርውሮልን የማንኖር ሲሆን እንደአንተ በአንድ ፍንጃል ቡና ሱቅ በረንዳ ላይ እያንቃረርን ቱሪ ናፋ አወዳሾች አለመሆናችን አይዘንጋ።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share