የትግራይ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መግለጫ “ከፍትፍቱ አጉርሱኝ ከመረቁ ግን ጾመኛ ነኝ!”

አቻምየለህ ታምሩ_የታሪክ ተመራማሪ!

የታሪክ ተመራማሪው እና ተንታኙ አቻምየለህ ታምሩ የትግራይ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ያወጣውን መግለጫ — “ከፍትፍቱ አጉርሱኝ ከመረቁ [ግን] ጾመኛ ነኝ!” እንደማለት ነው ሲል የሚከተለውን ሰፋ ያለ ምላሽ ሰጥቷል:_

የፋሽስት ወያኔ የሃይማኖት ክንፍ “የሀገረ ትግራይ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን” የሚል ሰም በሰጠው ድርጅት በኩል ከወደ መቀሌ በትግርኛ ቋንቋ ያወጣውን መግለጫ አነበብኩት።

“የሀገረ ትግራይ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን”ተብዮውን የፋሽስት ወያኔ የሃይማኖት ክንፍ ያልኹት “የሀገረ ትግራይ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን” ለማቋቋም የመሰረት ድንጋይ የተጣለው በፋሽስት ወያኔ መሆኑና ፋሽስት ወያኔ ሲፈጠር ጀምሮ የነበረ ፕሮጀክት መሆኑ ብቻ ሳይሆን የሃይማኖት ክንፉ በትግርኛ ቋንቋ ያወጣው መግለጫም በቤተ ክርስቲያን ስም ከመሰጠቱ በስተቀር ፋሽስት ወያኔ በዋናው ጽሕፈት ቤቱ በኩል ከሚያወጣቸው መግለጫዎች ጋር ምንም ልዩነት የሌለው በመሆኑ ጭምር ነው።

ፋሽስት ወያኔ ራሱን ማሌሊት ነኝ እያለ በገብረ ኪዳን ደስታ በኩል ግን የማሌሊቶች ቤተክርስቲያን ለመቋቋም ሲንቀሳቀስ የነበረ ጉድ ነው። እነሆ ያ እንቅስቃሴ ፍሬ አፍርቶ የማሌሊቶች ቤተ ክርስቲያን ስለመቋቋሙ ከወደ መቀሌ ሰምተናል!

መግለጫው በበርካታ የቂል ተረቶች፣ ነውረኛ ዲስኩሮችና አስቂኝ ጥያቄዎች የተሞላ ነው።

የፋሽስት ወያኔው የሃይማኖት ክንፍ አክሱምን ማዕከል ያደረገውን የኢትዮጵያ ቀደምት ስልጣኔ የትግራይና የትግሬ ብቻ ለማድረግ ያልሞነጨረው ቅራቅንቦ ተረትና የፕሮፓጋንዳ ዲስኩር የለም።

መግለጫው ስለ አክሱም ስልጣኔና ስልጣኔ የትግራይና የትግሬ ብቻ እንደነበር የታወቀ ነው ይላል።

የመግለጫው ጸሐፊዎች የአክሱምን ስልጣኔ ስልጣኔው በነበረበት ወቅት ላልነበሩት ለትግሬና ለትግራይ ለመስጠት ያን ያህል ሲኳትኑ አክሱም ውስጥ ዛሬም ድረስ ቆመው የሚገኙት የድንጋይ ላይ ጽሑፎችና በቁፈራ የተገኙ የጥንት ሳንቲሞች ስለ አክሱም ስልጣኔ ባለቤቶች ማንነት ከያዙት ማስረጃ ጋር መቃረናቸው ግድ አይሰጣቸውም።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ፲፩ኛ ስዓት፡ ዕድል እና ገደል= ገድል + ድል

በአክሱም ዘመን የነበረው ስልጣኔ ባለቤቶች፣ የንጉሠ ነገሥት መንግሥቱ ልዩ ልዩ ክፍሎች፣ ነገዶችና አሰፋፈራቸው እዚያው አክሱም ውስጥ በቆሙና በተቀበሩ ድንጋዮች አልፎም እስከ ደቡብ አረቢያ ድረስ በውጭ አገር ቋንቋዎችና የአገር ውስጥ ቋንቋዎች በሆኑት በግዕዝና በአማርኛ ቋንቋ ተጽፏል።

ስለዚህ ታሪክ ማስረጃ የሚሻ ቢኖር የአክሱምን የድንጋይ ላይ ጽሑፎችና የጥንት ሳንቲሞች በቦታው በመገኘት ከ110 ዓመታት በፊት ያጠናው ጀርመናዊን የታሪክ ፕሮፈሰር ኢኖ ሊትማን እ.ኤ.አ. በ1913 ዓ.ም. “Deutsche-Aksum Expedition” በሚል ርዕስ በአራት ቅጾች ያሳተመውን መጽሐፍ ማንበብ ይችላል።

አክሱም ውስጥ በሚገኙት የድንጋይ ላይ ጽሑፎችና ሳንቲሞች ላይ የአክሱም ስልጣኔ ባላቤቶች እነ ማን እንደሆኑ ዛሬም ድረስ የሚገኙ የልዩ ልዩ ነገዶች ስም ተጠቅሰዋል።

በዚህ የነገዶች ስም ዝርዝር ውስጥ ትግሬ ወይም ትግራይ የሚል የነገድም ሆነ የአካባቢ ስምና ዝርዝር የለም።

በሃይማኖት ስም መግለጫ ያወጡት “የሀገረ ትግራይ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን” ካድሬዎች ትግሬንና ትግራይን የአክሱም ስልጣኔ ብቸኛ ወራሽ ሲያደርጉ በማይዋሽበት ዘመን እየኖሩ አክሱም ውስጥ የቆሙት የድንጋይ ላይ ጽሑፎችና ተቆፍረው የተገኙ ሳንቲሞች ያስተዛዝቡናል ብለው ለመጠንቀቅ ባይሞክሩ እንኳን ያን ያህል ውሸት መድፈራቸው በፈጣሪያቸው ዘንድ ያስጠይቀናል ብለው የማይፈሩ ግብዞች ናቸው።

የአክሱምን ስልጣኔ ጨምሮ የትኛውም የኢትዮጵያ ሥልጣኔ የየትኛውም ነገድና ሃይማኖት አይደለም። የኢትዮጵያ ስልጣኔ ሁሉ ባለቤቱ ከአንድ ነገድና ሃይማኖት በላይ ነው።

የትኛውም ነገድና ሃይማኖት የትኛውምንም የኢትዮጵያን ሥልጣኔ በብቸኛነት የራሱ የሚያደርግበት የታሪክም ማስረጃ ሊያቀርብ አይችልም። በሌላ አነጋገር የኢትዮጵያ የሆነ ሁሉ ባለቤቱ ከአንድ ነገድና ሃይማኖት በላይ ነው።

የአክሱም ታሪክና ስልጣኔ በነገድ ይከፋፈል ቢባል የማይሆነው የትግሬና የትግራይ ብቻ ነው።

ተጨማሪ ያንብቡ:  እውን ፕሮፌሰር ኤፍሬም ይሳቅ በኢትዮጵያ ላይ እያሴሩ ነው? - ሰርፀ ደስታ

ማዕከሉን አክሱም ያደረገው የኢትዮጵያ ጥንታዊ ሥልጣኔ በብቸኛነት ከትግሬም ሆነ ከትግራይ ጋር የሚያገናኘው አንዳች ነገር የለም።

ማዕከሉን አክሱም ከተማ ያደረገው የኢትዮጵያ መንግሥት በነበረበት ወቅት ዛሬ ትግራይ ተብሎ የሚታወቀው አካባቢም ሆነ ትግራይ ተብሎ በሚታወቀው አካባቢ ትግሬ የሚባል ሕዝብ አልነበረም።

በነገራችን ላይ የአክሱም ታሪክ የትግሬ ሥልጣኔ እንደነበር የሚያሳይ አንድ እንኳን ብጣሽ የታሪክ ማስረጃ [የድንጋይ ላይ ጽሑፍና በቁፋሮ የተገኘ የአርኪዮሎጂ ማስረጃ] አለኝ የሚል የትግሬ ብሔርተኛ ፕሮፈሰርና ዶክተር ቢኖር ውለታ ከፋይ መሆናችንን ከወዲሁ ማሳወቅ እንወዳለን!

በቤተ ፋሽስት ወያኔ ነውር የሚባል ነገር ስለሌለ የፋሽስት ወያኔ የሃይማኖት ክንፍ የግዕዝን ስነ ጽሑፍ የትግሬና የትግራይ ሊያደርገው ይቃጣዋል።

ትግርኛ የግዕዝ ፊደል ከተፈጠረ ከሺ ዓመታት በኋላ የግዕዝን ፊደል ተጠቅሞ መጻፍ የጀመረ ቋንቋ ነው። እንደ አማርኛ ሁሉ ትግርኛም ከግዕዝ ፊደል ተውሶ ስለሚጽፍ ግዕዝን ትግሬ የፈጠረው አያደርገውም።

በስነ ልሳን ረገድም ከትግርኛ ቋንቋ ይልቅ ኤርትራው ውስጥ ዛሬም ድረስ የሚነገረው ትግረ ቋንቋ ለግዕዝ ይቀርባል። በቤተ ወያኔ እሳቤ መሰረት ግዕዝ የነገድ ቅርበት ይሰጠው ከተባለ ኤርትራ ውስጥ ላለው ትግረ [ትግሬ አላልኹም] እንጂ ኢትዮጵያ ውስጥ ላለው ትግሬ አይቀርብም።

እንግዲህ! የፋሽስት ወያኔ የሃይማኖት ክንፍ የኢትዮጵያን ስልጣኔ የአክሱም ስልጣኔ ብቸኛ ባለቤት ያደረገው ትግራይና ትግሬ ያዋሰው አድርጎ ያቀረበው ትግሬም ሆነ ትግራይ የአክሱም ስልጣኔ በነበረበት ወቅት ባልነበሩበት ነው።

ጥያቄው የፋሽስት ወያኔ የሃይማኖት ክንፍ ካድሬዎች ኢትዮጵያዊ አይደለንም ብለው “የሀገረ ትግራይ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን” ከመሰረቱ የኢትዮጵያን ስልጣኔ፣ የኢትዮጵያን ፊደል፣ የኢትዮጵያን ቤተ ክርስቲያን ሥርዓተ ሃይማኖት ለምን አብረው አይጠሉትም?

ተጨማሪ ያንብቡ:  ለኢትዮጵያ የሃይማኖቶች ተቋማት ጉባኤ፡- ‹የጾም ወራት የተኩስ አቁም/the Fasting Truce› ስለምን አይታወጅም?!

ሌላው “የሀገረ ትግራይ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን” በሚል ስም በወጣው መግለጫ ከምናገኛቸው አስቂኝ ጥያቄዎች አንዱ ኢትዮጵያን ምግብ፣ መድኃኒት፣ የስልክ፣ የውኃ፣ የመብራትና የባንክ አገልግሎት ባስቸኳይ ለ[ሀገረ] ትግራይ እንድታቀርብ የጠየቁበት ማስጠንቀቂያ አዘል ጥያቄ ነው።

ኢትዮጵያዊ አይደለንም ብለው ከኢትዮጵያ በመገንጠል የራሳቸው የሆነን “የሀገረ ትግራይ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን” ካቋቋሙ አገራቸው ያልሆነችውን ኢትዮጵያን ምግብ፣ መድኃኒት፣ የስልክ፣ የውኃ፣ የመብራትና የባንክ አገልግሎት ባስቸኳይ ለ[ሀገረ] ትግራይ እንድታቀርብ ለምን ይጠይቃሉ?

ባጭሩ የፋሽስት ወያኔ የሃይማኖት ክንፍ ካድሬዎች “የሀገረ ትግራይ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን” ካቋቋሙና ኢትዮጵያን ከጠሉ ሁሉን መጥላት እንጂ ኢትዮጵያን እየጠሉ “ከፍትፍቱ አጉርሱኝ ፤ ከመረቁ [ግን] ጾመኛ ነኝ” እንዳለው አይነት ቂላቂልነት የኢትዮጵያ የሆነውን ለምን ይወዳሉ? የተለየን ነን ብለው ኢትዮጵያ ከጠሉ የኢትዮጵያ የሆነውን ሁሉ አብረው ለምን አይጠሉትም? ኢትዮጵያን ከጠሉ የኢትዮጵያን ነገር ለምን ይወዱታል? እስቲ ጠይቁልን?!

4 Comments

  1. እዉነትም አቻምየለህ እዚህ ላይ ፕሮፌሰር ሐይሌ ላሪቦ ማጠናከሪያ ቢሰጠው የገ/ኪዳን ደስታ ተረት ከእርሱ ጋር የቀበር ነበር። ምነው ተው የሚል ከትግሬ ጠፋ? ኳስ አበደች ነገር ሆነ እኮ እነሱ አካባቢ። ፕሮግራም ተደርገው እንደተላኩ ሁሉ ቆም ብሎ ማሰብን ጠሉ ከእውነት ይልቅ ሃሰትን አፈቀሩ ይህ ምን ይባላል? ሰው እድሜ ልኬን እየሰረቅሁ እየገደልኩ ካልኖርኩ ብሎ ድርቅ ይላል? መጥኔ ለነሱ

  2. በብርስ ለምን ይጠቀማሉ ቀላሉ በእሱ መጀመር ነው::ወገኞች ! ሀይማኖትም እምነትም ንግድ ሲሆን ያሳዝናል

  3. ከትግራይ ደናቁርት ፖለቲከኖች ከዚህም በላይ አያሌ ክህደቶችንና ማመሰሎችን ብቻ እንጅ እውነትን ታሪክንና ሀቅን መጠበቅ ሞኝነት ነው የሚሆነው፡፤ ወያኔወች የአክሱም ስልጣኔን ብቻም ሳይሆን የአድዋ ድልንም የእኛ የብቻችችን ድል ነው ብለው ደፍረው የሚናገሩ ሀፍረት የሚባል ነገር ያልፈጠረባ`ቸው የታሪክ ድኩማኖች ናቸው፡፡እነዚህን የሰላቶ ተላላኪ የልጅ ልጆች የአክሱም ስልጣኔና የአድዋ ድል የእኛ ብቻ ነው ከማለትም ባሻገር እጅግ በሚያሳፍሩ ክህደቶች ሌሎች አያሌ ክህደቶችም መዋጣቸው ለዚህ ሁሉ ተረት ተረት አብቅቷቸዋል፡፡
    ለዛሬው ከነዚሁ ክህደቶቻቸው ውስጥ አንዱን ብቻ ልጥቀስ፡፡ ከቅርብ አመታት ወዲህ የአድዋ ባንዳ ውላጆች ተሰባስበው የፈጠሩት ተጋሩ የሚል ጉደኛ ቃል በሰፊ እየተሰራጨ ይገኛል፡፡ የታሪክ ከሀዲወቹ ለዚሁ ምክንያታቸው በአጭሩ ትግሬ የሚለውን ቃል ለመሸሽ የፈጠሩት ዘዴ ነው፡፤ ትግሬ የሚለው ቃል እስከ 14ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ በአድዋ አውራጃ የአንድ ወረዳ የማንነት መለያ ስም ነበር፡፡ ይህ ወረዳ አሁን በአድዋ አውራጃ ውስጥ እንባ ሰነይቲ ወይንም እዳጋ አርቢ ያለው ብሄረሰብ መጠሪያው ነበር፡፡ ይህ ብሄር ባካባቢው ካሉት ከእንደርታ፣ ተንቤን አጋሜ አክሱም ይልቅ ከማእከላዊ ነገስታቱ ጋር የተሻለ ቅርበት በመፍጠሩ ከሌሎቹ የበላይነትን ወሰደ፡፤ በዚህም ትግሬ የሚለው ቃል በስፋት የአካባቢው መጠሪያ ተደርጎ ተወሰደ፡፡ ከዚሁ ጋርም ተያይዞ ትግረኛ ቋንቋ ዋጀርኛን፣ አማርኛንና ሳሆኛን ቋንቋወች እየዋጣቸው መጣ፡፡ የአደዋ እንባ ሰነይቲ ትግሬ ማንነት የበላይ ተደርጎ በመወሰዱም በወያኔ የስልጣን እርከን ላይ ቅደሚያን ወሰደ፡፡ ለዚህ ነው አብዛኛው የወያኔ ስልጣን በአንድ የአደዋ ብሄር የተሞላው፡፡ ለዚህ ነው እንዳንዶች ይህንን የትግሬ ማንነት እውነትነቱን ከመቀበል ይልቅ ተጋሩ የሚል ሌላ ማንነት በመፍጠር ላይ ተሰማርተው የሚገኙት፡፡ የወያኔ ቅል ራሶች ሆይ፦ሰባ እንደርታ የሚለውን የነብዮ ስሁልን መጸሀፍ ተመልከቱ፡፡ ታሪክን መካድ/መሸሽ አይቻልም፡፡እናንተ አሁን ብትክዱት በክልል አንድ ውስጥ ትግሬና ትግረኛ የሚባለው ማንነት የአንድ ወረዳ ማንነት መሆኑን ታሪክ ኣይዘነጋውም፡፡
    በወያኔ አሰራር መሰረት በትግራይ ክልል (ክልል አንድ) የሚኖሩ ብሄር ብሄረሰቦች ስብጥር የሚከተለውን ይመስላል፡፡1) ኢሮብ / ሳሆ 2) ዋጅራት 3) ኩናማ 4) እንደርታ 5) ተንቤን 6) አክሱም /አማራ 7) ትግሬ / ተጋሩ / አድዋ ናቸው፡፡ወያኔ ሽንጡን ገትሮ የሚታገለው በክልሉ ስላሉት ለእነዚህ ብሄር ብሄረሰቦች የባህል፣ የማንነት፣ራስን በራስ የማስተዳደር ጉዳዮች እድገት ሳይሆን በተጋሩ ስም ሁሉንም ለመደፍጠጥ ነው፡፡ ከዚህም አልፎ በአማራ ክልል ውስጥ በተሻለ ራስን በራስ የማስተዳደር መብትን ስለተጎናጽፉት የቅማንት፣ የአርጎባ፣ የኦሮሞና የአገው ብሄር ብሄረሰቦች ጭቆና ነጻነት በመጮህ ላይ ተተምዷል፡፡ በተለይ ቅማንትን በሚለከት ተቃዋሚ ተብየወችን አደራጅቶና በመቀሌ ቢሮ ከፍቶ ቅማንትን በእጅ አዙር ወደትግራይ ለመጠቅለል የማያደርገው ነገር የለም፡፤ ከንቱ ድካም!! ወያኔወች ይህን ሁሉ የምትደክሙት በቅማንት አስተዳደር ወሽመጥ ላይ ተረማምዳችሁ በእጅ አዙር ወደ ሱዳን ድንበርተኝነትና ብሎም ወደ ታላቁ ህዳሴ ግድብ ባለቤትነት ጠጋ ለማለት ነው፡፤ አይ ቅዠት!! የወልቃይትና የራያ ለም የአማራ መሬቶችን ከአማራው ነጥቆ በመውሰድ ታላቋ ትግራይን የመመስረት የማይሳካ ህልማችሁ ቅዠት ሆኖባችሁ እንደቀረው ሁሉ የቅማንት መረማመጃ ውሽመጥንም የመመኘት ቅዠታችሁ ወሽመጣችሁን ቆርጦት ይቀራል እንጅ ምንጊዜም አይሳካላችሁም፡፡
    በመጨረሻም አንድ ነገርን አስረግጠን እናሳውቃችሁ፡፤ የአክሱም ስልጣኔና የታላቁ አድዋ ድል ባለቤትነት የሁሉም ኢትዮጵያዊ አሻራ ያለበት ሲሆን ይህንኑ እውነታም ታሪክ መዝግቦ ይዞታል፡፡ሁሉም የትግራይ ክልል ተወላጅ ሁሉ ተጋሩ እንዳልሆኑ አውቃችሁ ከላይ ከ1 እስከ 6 የተዘረዘሩትን ብሄር ብሄረስቦች ማንነት በተጋሩ ስም ለመጨፍለቅ ከመሞከርም ብትቆጠቡ ያዛልቃችሁ ይሆናል፡፡ በቅዠት ውስጥና በስሜት ውስጥ ሆናችሁም የሌላውን ማንነት ለመደፍጠጥና ለም የአማራም ሆነ የአፋር መሬቶችን ለመውሰድ ድጋሜ እንዳታስቡትም እንዳትመኙትም፡፡
    ታሪክና እውነት በስሜት ወይንም በፍላጎት አይለወጥም፡፤ ታሪክም ታሪክ ነው እውነትም እውነት ነች!!

  4. እውነቱ ቢሆን
    ይህች ከግርጌ ተቀርቅራ የተሰጠች ትልቅ አስትያየትህ እራስዋን ችላ ዋናው አምድ ላይ ብትለጠፍ ለታሪክ መስተካከል ትልቅ እገዛ ከማድረጓም በላይ አላዋቂዎች በስሜት ተገፋፍተው የማይሆን ስህተት እንዳይሰሩ ከማድረጉም በላይ የትግሬም ወጣት የእሱ ባልሆነው ታሪክ ተታልሎ ወደተሳሳተ መንገድ እንዳይሄድ ያደርጋል። መልከ ጥፉን ሴት ቆንጆ ነሽ ቢሏት እሩቅ ኡያስኬድም መስታወት ስላለ።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share